የሚዲያው ዝምታ ለምን ይሆን? የኮሮና ቫይረስ በቻይና ከመከሰቱ በፊት በአሜሪካ በቫይረሱ ተጠቅተው የሞቱ መኖራቸው ተረጋገጠ። ይህንን ያረጋገጡት የአሜሪካ የበሽታ ቁጥጥር ማዕከል (CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሮበርት ሬድፊልድ ናቸው። ዳይሬክተሩ እንዳሉት ይህ የታወቀው በኢንፍሉዌንዛ በሞቱ ሰዎች ላይ በድጋሚ በተደረገ ምርመራ ነው። በተለያዩ የሚዲያ ዘገባዎች በተደጋጋሚ ሲነገር እንደቆየው የኮሮና ቫይረስ የተጀመረው በቻይና ዉሃን ከተማ እንደሆነ ነበር። ለበሽታው መነሻም የተለያዩ መላምቶች ሲሰጡ ቆይተዋል። አንዱ መላምት ከእንስሳት ወደ ሰው ነው የተላለፈው የሚል ነው። ለዚህም እንደ ማስረጃነት የሚቀርበው ቻይናውያኑ የሚበሉት፣ “እርጥብ ገበያ” (wet market) ተብሎ በሚጠራው ቦታ ከባህር የሚገኙ ማንኛውም የአሣ ዝርያ እስከ የሌሊት ወፍ፣ እባብ፣ ውሻ፣ ሸለምጥማጥ፣ … [Read more...] about ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል
Slider
ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ
በአሜሪካ የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክትል ሊቀ መንበር ተደርጎ የተሾመው የቀድሞው የህወሃት ካድሬና የበረከት ስምዖን ታማኝ ኤርሚያስ ለገሰ መሰናበቱ ተሰማ። እስክንድር ነጋን የጠቀሱ የጎልጉል እማኞች እንዳሉት ኤርሚያስ መባረሩን አያውቅም። በዚህ ሳቢያ 360 እንደ ስሙ ዘመቻውን ያዞራል ተብሎ ይጠበቃል። የእስክንድር ነጋን የአሜሪካ ጉዞ ተከትሎ በሰርግና ምላሽ የባለ አደራው ምክትል ሰብሳቢ የሆነው ኤርሚያስ ሹመቱን አስመልክቶ ስለ ቀጣዩ የትግል አቅጣጫ፣ የትግሉ ግብና አደረጃጀት እንዲሁም ኔትዎርክ ማብራሪያ ሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል። ተያዘውም ወደ ተፈለገው ዓላማ እንደሚደርሱ ምሎ ነበር። ለድርጅቱ ሊቀመንበር እስክንድር ነጋ ቅርብ የሆኑና ይህ ውይይት ሲደረግ የነበሩ ኤርሚያስ ለገሰ በቅርቡ ከሃላፊነት መነሳቱ ይነገረዋል "የእሱ መሰናበት ያለቀ ነው። መጀመሪያም ትክክል አልነበረም" … [Read more...] about ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ


