
በአሜሪካ የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክትል ሊቀ መንበር ተደርጎ የተሾመው የቀድሞው የህወሃት ካድሬና የበረከት ስምዖን ታማኝ ኤርሚያስ ለገሰ መሰናበቱ ተሰማ። እስክንድር ነጋን የጠቀሱ የጎልጉል እማኞች እንዳሉት ኤርሚያስ መባረሩን አያውቅም። በዚህ ሳቢያ 360 እንደ ስሙ ዘመቻውን ያዞራል ተብሎ ይጠበቃል።
የእስክንድር ነጋን የአሜሪካ ጉዞ ተከትሎ በሰርግና ምላሽ የባለ አደራው ምክትል ሰብሳቢ የሆነው ኤርሚያስ ሹመቱን አስመልክቶ ስለ ቀጣዩ የትግል አቅጣጫ፣ የትግሉ ግብና አደረጃጀት እንዲሁም ኔትዎርክ ማብራሪያ ሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል። ተያዘውም ወደ ተፈለገው ዓላማ እንደሚደርሱ ምሎ ነበር።
ለድርጅቱ ሊቀመንበር እስክንድር ነጋ ቅርብ የሆኑና ይህ ውይይት ሲደረግ የነበሩ ኤርሚያስ ለገሰ በቅርቡ ከሃላፊነት መነሳቱ ይነገረዋል “የእሱ መሰናበት ያለቀ ነው። መጀመሪያም ትክክል አልነበረም” ሲል እስክንድር የተናገረውን ቃል በቃል የሰሙትን የጎልጉል እማኞች ተናግረዋል። ይህ ሲሆን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይስቅ ነበር።
ይህንኑ ዜና ተከትሎ ማየት የተሳነው የወያኔ መልዕከተኛ ቴዎድሮስ ጸጋዬ የሚመራው ርዕዮትና 360 የተሰኘው የዩቲዩብ የ”ዛሬ ምን አለ?” መድርክ በእስክንድር ነጋ ላይ ፊታቸውን እንደሚያዞሩ ይጠበቃል።
በህጋዊ የብሮድካስት ፈቃድና አገር ቤት ተመዝግቦ በሚሰራ አንድ ሚዲያ ባለቤት በስውር የሚደጎመው 360 የኤርሚያስን መሰናበት፣ ስንበቱ እሱ ሳያወቀው መደረጉን፣ እንዲሁም በሚስጢር መያዙን ሲሰማ “ዛሬ ምን አለ?” በሚለው የ360 የድራማ ክፍለ ጊዜ ላይ ምን ዓይነት ትንተና እንደሚሰጥ ከወዲሁ በጉጉት ይጠበቃል።
እስክንድር እግረ መንገዱንም ስንታየሁ ቸኮልን ጨመሮ ሹም ሽር እንደሚሚደረግ ፍንጭ ሰጥቷል።
በቅርቡ የአሜሪካ ዜግነት የተቀበለው ኤርሚያስ ለገሠ በምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ ወደ ምርጫ ውድድር የገባው ባለአደራ ምክትል ሆኖ እንዴት ሊሠራ እንደሚችል ጥያቄ የፈጠረ ጉዳይ ነበር። ኤርሚያስ ግን፤ የአሜሪካንን ዜግነት የተቀበልኩት ፕሬዚዳንት ትራምፕን ታግዬ ከሥልጣን ለማባረር ነው፤ በማለት በዚሁ የ360 ዩትዩብ ማስተላለፊያ ሲናገር ተደምጧል።
ድህረ ህወሓት/ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ለውጥ ሲመጣ ኤርሚያስ ወደ አገር ገብቶ በሹመት ለመሥራት መፈለጉን በመግለጽ ለጠ/ሚ/ር ዐቢይም በወቅቱ የአማራ ክልል መሥተዳድር ለነበሩት ገዱ ጥያቄ አቅርቦ እንደነበር፤ “የድሮው ብአዴን የአሁኑ አዴፓ ሚስጥራዊ ዶክመንቶች፣ ቪዲዮዎች ወዘተ በእጁ እንደሚገኙ፤ እነዚህን ለጠ/ሚው አሳልፎ መስጠት” ፍላጎቱ እንደሆነ፤ “ይህንን የሚያደርገው ጥሩ ሹመት፣ ቤት እና መኪና እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ሲሟሉለት እንደሆነ” በላከው ማስታወሻ መላኩ የሚታወስ ነው። ይህ ጥያቄው ተቀባይነት ካጣ በኋላ ምክንያት ዐልባ ጭፍን ተቃዋሚ ጎራ ራሱን እንዳስገባ “የኤርምያስ ለገሰ ቪዲዮዎች ፉከራ ሲጋለጥ” በሚል ርዕስ የታተመው ጽሁፍ ያስረዳል።
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።
የጎልጉል ድህረ-ገጽ በኤርምያስ ለገሰ ላይ ተደጋጋሚ ውግዘትና ውሸት የምታስተጋባው ለምን ይሆን ? ጎልጉል ድህረ-አብይ መሆንዋን በግልጽ እያየን ነው ማንኛውም ድህረ-ገጽም ይሁን ጋዜጣ ወይም መጽሔት ከገዥዎች ጋር ከወገነ መቆሸሹንና ርካሽ መሆኑን በግልጽ ያመለክታል ፥ እናንተም ከገዥው የኦሆዲድ -ኦነግ ጋር ተለጥፋችሁ የሰዎችን ስም በከንቱ የምታጠፉ ርካሾች ናችሁ ፥ ኤርምያስ ለገሰን ከምትወንጅሉ ይልቅ ከእናንተው ጋር ሀገሪቱን የሚመራው የኦሆዲዱ ሊ/መ ግራኝ አህመድ አሊ በፋሽስቱ ህወሃት ሥርዓት ቀንደኛ አገልጋይና የኦሮሞንና የአማራን ወጣቶች ሲያስገድልና ሲያሳስር የነበረ ሴረኛና ሻጥረኛ ግለሰብ ለምን አንድ አትሉሉም ? ሌላው የብልግናችሁ ጥግ ጋዜጠኛ ቲዎድሮስን “ማየት የተሳነው” ስትሉ በፍጹም ከአንድ ለሕዝብ ከሚቀርብ ጋዜጣ ዝግጅት የማይምጥን ዜሮ (0) መሆናችሁን አሳይታችሁዋል ፥ እርሱ ማየት ተሳነው እናንተ ግን ልባችሁ ከእርሱ ዓይን በበለጠ ታውሮዋል ፥ እኔ የቴዎድሮስም ሆነ የኤርምያስ ለገሰ ደጋፊም ሆነ የቅርብ ሰው አይደለሁም ፥ ሁለቱንም በቲቪ መስኮት በሚያስተላልፉት ታላቅ ቁም ነገር እከታተላለሁ ፥ ጎልጉል ሙጀሌ ይጎልጉል እንጂ ቁም ነገር የለውም ፥ የሀገሬ ሰው ሲናገር ” ማሽላው ሞረት ማማው ቅንብቢት” ይላል ፥ እናንተም ከኤርምያስ ጋር በምንም ዓይነት የማይገናኝ ትርኪ ምርኪ እየቃረማችሁ ትለጥፋላችሁ ፥ በእኔ እይታ ኤርምያስ ለገሰ ከባልደራስ ቢባረር ምን ይመጣል ? ድሮስ እርሱ የተሾመው የውጭውን ዲያስፖራ እንዲያስተባብር እንጂ አ/አ ሄዶ ሥልጣን ለመጋራት አይደለም ፥ ድሮም ኤርምያስ ፈልጎ ሳይሆን ራሱ እስክንድር ነጋ መርጦ ሾመው እንጂ ኤርምያስ በምልጃ ያገኘው ሹመት አይደለም ፥ እባካችሁ ከምታደርጉት ግለሰባዊ እይታ ወደ ዘርፈ ብዙው የሀገራችን ችግሮች ላይ ምልክታችሁ አድርጉ ፥ አሉባልታ የትም አያደርስም ፥ ራስን ያቀላል እንጂ !
ጎልጉል ባትሳሳት ደስ ይለኛል። “ኤርምያስ ለገሰ ተባረረ” የተባለው ስህተት ነው። ኤርምያስ ገና ስክንድር ነጋ ከሲቪክ ድርጅትነት ወደ ፖለቲክ ድርጅትነት ለመለወጥ ሲያስብ ውዲያውኑ ቀድሞ ባልደራሱ ወደ ፖለቲክ ድርጅትነት ከትለወጠ፤ ሃላፊነቴት እለቃለሁ ሲል በ360 ሲናገር ስምቸዋለሁ። ስለዚህ በፈቃዱ ለቀቀ ቢባል ትክክል ይሆናል። ከአክብሮት ጋር
ኤርምያስን እስክንድር ሾሞ ከሻረው፣ እስክንድርም መባረሩ አይቀርም። ኤርምያስም በሄደበት ሳይቆይ በተደጋጋሚ እየተባረረ ነው። ለምን ይሆን?
ይሄ ውሸት ግን የእውነቱ ወጥቶ ጎልጉል የተባለ የመረጃ መረብ ለማመን ይከብዳል
You are simply attacking some one because you have other agenda.The whole article a collection of gossips not a single fact in it.Now we know who you are !
Kotone said Kaffa.
Ermias ahun mekawem yefelgew yasebew altesakaletm Ethiopia chigr bifeter men endemitekem alawkem esu lemidia yemihon aydelem betkikel mebarer new yemigebaw