በወለጋ የንፁሃንን ጭፍጨፋ እየተፈፀመ ያለው በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ሃንጋሳ አህመድ ኢብራሂም ተናገሩ። አክለውም የኦሮሚያ ፕሬዘዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከስልጣናቸው እንዲነሱ ጠ/ሚ አብይ አህመድን በይፋ በፌስቡክ የቀጥታ ስርጭታቸው ጠይቀዋል። ከ 2 ቀናት በፊትም ጠባቂያቸው መገደሉን ተናግረዋል። አቶ ሀንጋሳ ትላንት ሁለት ሰዓት በፈጀውና ከ15 ሺህ በላይ ተመልካቾች በተከታተሉት የፌስቡክ የቀጥታ ስርጭት በኦሮምኛ (የተወሰኑ ቁልፍ ነገሮችን ደግሞ በአማርኛ) አስተላልፈዋል፡፡ የሚከተሉት ዋነኛ ነጥቦች ነበሩ: አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና እቅድና ተግባር ነው፣ አብዲ ኢሌ ሲነሳ ሶማሊያ ሰላም እንደሆነው ሁሉ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ በክልሉ ያሉ ባለስልጣናትን እስር … [Read more...] about “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ
Uncategorized
ትውስታ ዘ ዳንሻ – ታላቁ ጥቁር!
አምስተኛ መካናይዝድ ክፍለጦር ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ እንደ ወትሮው ከዋርድያዋች ውጭ ሁሉም ተኝቷል። አንድ ታላቅ ፣ ጥቀር የሌሊት ልብሱን እንደ ለበሰ መፅሃፍ ያነባል ድንገት የቶክስ ድምፅ ሰማ በአካባቢው ሁሌም የቶክስ ድምፅ መስማት የተለመደ ቢሆንም ወታደር ነውና ምልልስ ካለ ብሎ ለማዳመጥ ሞከረ ከሁለት አቅጣጫ መሆኑን ተረዳ። ስልኩን አነሳ ወደተለያየ ቦታ ደወለ ሁሉም አይሰራም ስልኩን አየው ኔትወርክ የለውም አሁን ችግር እንዳለ ተራዳ ካለበት ክፍል ግድግዳ እየታከከ ወደ በሩ ተጠጋና በሩን ሲከፍተው የተመታ ጓዱ ከነክላሹ በጀርባው ወደቀ ወዲያው የቶክስ ሩምታ ወደ በሩ አቅጣጫ ተከፈተበት እንደምንም ከወደቀው ጓዱ ካላሹን ተቀብሎ እየተኮሰ በቅርብ ቀን ወደተሰራች የብሎኬት ግቢ ዘሎ ገባ። በግቢው ውስጥ አንደ ገባ የራሱ ጓድ የሆነች ሴት ወታደር በብሎኬት አጥር ቀዳዳ … [Read more...] about ትውስታ ዘ ዳንሻ – ታላቁ ጥቁር!
አዲስ አበባን በፓርላማ የሚወክሏት ተመራጮች
አዲስ አበባ ከተማ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 23 መቀመጫዎች አሏት፡፡ ሰኔ 14፤ 2013 በተካሔደው ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ፤ ከ23 የፓርላማ መቀመጫዎች ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በ22 የምርጫ ክልሎች ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትላንት ቅዳሜ ምሽት አስታውቋል፡፡ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ያላቀረበበት ብቸኛ የአዲስ አበባ ምርጫ ክልል በሆነው ምርጫ ክልል 28 ደግሞ፤ የግል ተወዳዳሪው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ማሸነፋቸው ተገልጿል፡፡ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ናቸው፡፡ የምርጫ ውጤት ብልጽግና ፓርቲ በከፍተኛ ውጤት፣ አብላጫውን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበርን በማግኘት አሸንፏል። በዚህ መሰረት ብልጽግና ፓርቲ ከ436 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ 410 መቀመጫ ማግኘቱን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የአማራ … [Read more...] about አዲስ አበባን በፓርላማ የሚወክሏት ተመራጮች
ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተገኘ
በደብረ ማርቆስ ከተማ ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በአንድ ግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተከዝኖ ተገኘ። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ ዐ5 ልዩ ቦታው ኢንዱስትሪ መንደር ውስጥ በሚገኝ ለሙጫና እጣን ማቀነባበሪያ መጋዘን ውስጥ ከ6ሺ ኩንታል በቆሎ በላይ ተከዝኖ መገኘቱን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ገልጿል። የተገኘውን እህል በከተማው ለሚገኙ አስራ አራት ሸማች ህብረት ስራ ማህበራት እንደሚከፋፈል እና በዛሬው ዕለት ሁለት ሸማች ማህበራት ከአራት መቶ በላይ ኩንታል መውሰዳቸውን እና ለህብረተሰቡ እንደሚከፋፈል የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ብርሀኑ መኩሪያው ገልጸዋል። የወንጀሉ ጉዳይም ፖሊስ አስፈላጊውን ምርምራ እያጣራ መሆኑን አስረድተዋል። (የደብረ ማርቆስ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተገኘ
ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው
በሀገር መከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር በምትገኘው ማይጨው ከተማ ህዝቦቿ ወደሙሉ የዕለት ተዕለት ተግባራቸው ተመልሰዋል። (መረጃውን ለtikvahethiopia ያደረሰው አበበ ሰማኝ ከማይጨው ነው)። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው
“ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ
የወልቃይት፣ ጠገዴ እና ሰቲት ሁመራ ነዋሪዎች በዳንሻ ከተማ በመሰባሰብ በአማራ ክልል የመስተዳደር ጥያቄያቸው አፋጣኝ ምላሽ እንዲያገኝ በህዝባዊ ሰልፍ ጠይቀዋል። የወልቃይት፣ ጠገዴ እና ሰቲት ሁመራ ነዋሪዎች በዳንሻ ከተማ በመገኘት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ጥያቄያችን የህልውና ጉዳይ ነው ሲሉ አደባባይ በመውጣት ድምፃቸወን አሰምተዋል። ነዋሪዎቹ በህወሃት የግፍ አገዛዝ በጉልበት ወደትግራይ ክልል ተካለው ሲፈፀምባቸው የቆየው ግፍ ይበቃል ብለዋል። በዚህ የህልውና ጉዳይ በሆነው የህዝብ ትእይንት የተገኙት የወልቃይት ጠገዴ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሠብሳቢ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ መልእክት አስተላልፈዋል። ኮሎኔል ደመቀ ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጅ ሠጥተን አንጠይቅም ብለዋል። አሁንም ቢሆን በወልቃይት ጉዳይ ሌላ ጁንታ አይኖርም ብለን ሳንዘናጋ ሁላችንም … [Read more...] about “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ
በመቀሌ መከላከያ የማያውቀው የጦር መሳሪያ ዲፖ ተገኘ
በመቀሌ ከተማ የጥፋት ሃይሉን አባላትና የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል የቤት ለቤት ፍተሻ ተጀምሯል። በዚህም በከተማው የጥፋት ቡድኑ የጦር መሳሪያ ማከማቻ ዴፖ በብርበራ በሰራዊቱ ተይዟል። በወቅቱም ሶስት ኮንቴነር ጠመንጃ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ ጥይቶች፣ ክላሽንኮብ መሳሪያ፣ ስናይፐር፣ አድማ መበተኛ የጭስ ቦምብ እና ፈንጅዎች ተይዘዋል። በተጨማሪም የትግራይ ልዩ ሃይል መለዮና የአባላት መታወቂያዎች መያዛቸውም ታውቋል። ሰራዊቱ አሁን ላይ በሚያካሂደው የፍተሻና ብርበራ የጥፋት ሀይሉ ሊጠቀምባቸው የሚችሉ በርካታ የጦር መሳሪያዎች እንደሚያገኝም ይጠበቃል ነው የተባለው። ለዚህም የትግራይ ህዝብ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠይቋል። በተያያዘ ዜና ከቀናት በፊት በመከላከያ ሰራዊቱ ቁጥጥር ስር በዋለችው መቀሌ ከተማ በተወሰነ መልኩም ቢሆን … [Read more...] about በመቀሌ መከላከያ የማያውቀው የጦር መሳሪያ ዲፖ ተገኘ
በሁመራ ለሁለተኛ ጊዜ 37 ኩንታል አደንዛዥ እፅ ተገኘ
በሁመራ ከተማ በአንድ ሆቴል በተደረገ ፍተሻ ለሁለተኛ ጊዜ 37 ኩንታል አደንዛዥ እፅ ተገኘ። በከተማዋ ህግን የማስከበር ግዳጅ እየተወጡ የሚገኙ የአማራ ክልል ፖሊስ አባላት ህገወጥ ድርጊቶችን ለማስወገድ እና የህዝብን ሠላም ለማስጠበቅ እየሠሩ መሆኑን የከተማዋ ፖሊስ መምሪያ ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮማንደር ሙላት ማሞ ገልፀዋል። ከአደንዛዥ እፁ በተጨማሪ በአንድ ሰው ስም የተመዘገቡ 11 የቤት ካርታዎች እና በዚሁ ግለሠብ ስም ከፍተኛ ገንዘብ የተዘዋወረበት ቼክ ተገኝቷል። ከዚህ በተጨማሪም ገጀራዎች፣ መጥረቢያዎች እና ሌሎች መሳሪያዎች እንደተገኙ መናገራቸውን አብመድ ዘግቧል። ጎልጉል የድረጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በሁመራ ለሁለተኛ ጊዜ 37 ኩንታል አደንዛዥ እፅ ተገኘ
ህወሓት በማይካድራ በፈፀመው ወንጀል በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ተጠየቀ
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ሕወሓት ዘርን መሠረት አድርጎ በማይካድራ በፈፀመው የንጹሐን ዜጎች የግድያ ወንጀል መንስዔ በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ጠየቁ። አባላቱ ይህንን እና ሌሎች መሰል ወቅታዊ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቅርበዋል። የተደረገው ፍጹም ጭካኔያዊ እና አረመኔያዊ ድርጊት እጅግ እንዳሳዘናቸውም አያይዘው ገልጸዋል። ተግባሩም የጦር ወንጀለኝነት መሆኑንም አበክረው ተናግረዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት አክለውም፤ የሀገርን እና የህዝብን አደራ ተቀብለው ግዳጃቸውን እየተወጡ በነበሩት የሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን የወሰደው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊትም እጅግ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል። በየትኛውም የህግ መመዘኛ ተቀባይነት እንደሌለውም አስረድተዋል። የፓርላማ አባላቱ በተጨማሪም፤ የኢፌዴሪ የሀገር … [Read more...] about ህወሓት በማይካድራ በፈፀመው ወንጀል በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ተጠየቀ
ቀዩ መስመር ታልፏል
የሥራ አስፈጻሚው ከፍተኛው አካላት የሆኑት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅና ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ህወሃት ቀዩን መስመር ማለፉን አስታውቀዋል። ፕሬዚዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት። “የሰማሁት አሰቃቂ ግድያ ልቤን በእጅጉ ሰብሮታል። ንጹሀን ዜጎች በሌሎች እብደት ውድ ሕይወታቸውን የሚከፍሉበት ንብረታቸው የሚወድምበት መሄጃ አጥተው የሚንከራተቱበት ምንም ምክንያት የለም። የዛሬ ዓመት በ30/10/2019 የጻፍኩትን ትዊት ልድገመው። “ዘርና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሀን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል። ለቅሶ፣ ድንጋጤና ሥጋት የብዙዎችን በር አንኳኩቷል ሃዘናቸው ሃዘኔ/ሃዘናችን ነው። “ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል … [Read more...] about ቀዩ መስመር ታልፏል