ከ27 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትር የስብሰባ አዳራሽ የተገኙት ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም፤ ዶ/ር ዐቢይ የዕለቱን የመወያያ አጀንዳ ከገለጹ በኋላ እና የስብሰባው ተሳታፊዎች አሳባቸው እየገለፁ ባሉበት ወቅት ነው፤ የኔታ ወደ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ የገቡት። ዶ/ር ዐቢይን ጨምሮ በአዳራሽ ውስጥ የነበሩ ተሰብሳቢዎች የኔታ የመቀመጫ ወንበራቸውን እስኪይዙ ድረስ የተሰብሳቢው ዓይን በፍቅርና በአክብሮት እሳቸው ላይ ነበር ያረፈው። የተጀመረው ውይይት በተሰብሳቢዎች በሚነሱ ጥያቄዎችና አስተያየት ቀጥሎ ለሻይ ዕረፍት ስብሰባው ተቋረጠ። ሁላችንም ሻይ እና ቡና ወደተዘጋጀበት ቦታ አመራን፤ ዶ/ር ዐቢይ ለሻይ በወጣንበት ወቅት የቱ ጋር እንዳሉ እኔ ልብ አላልኩም፤ ይልቁንም ለየኔታ ትኩስ ነገር ምን ላምጣሎት ብዬ ስጠይቃቸው፤ “አንድ ሲኒ ቡና ትንሽ ስኳር ጨምረ አመጣልኝ፣ ከዚያ … [Read more...] about የኔታ እና ዶ/ር ዐቢይ፤ የኔታ ምን አሉ?!
Uncategorized
ሁለቱ ጄኔራሎች
ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ እና ሜ/ጀኔራል አለምሸት ደግፌ ከመከላከያ ሰራዊቱ በተለያየ ጊዜ “የመከላከያ ሪፎርም አደናቃፊ” በሚል ማዕረጋቸው ተገፍፎ የተሰናበቱ ወታደራዊ መኮንኖች ናቸው። ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ የቀድሞ የጦር ሠራዊት አባል የነበረና በ1978 ዓ.ም ኢህዴንን የተቀላቀለ ጀግና አዋጊ እንደሆነ የኢህዴን ጓዶቹ ሳይቀር ይመሰክሩለታል። ድህረ-ደርግ በሲቪል አስተዳዳሪነት የላስታ ወረዳ አስተዳደር ቀጥሎም የሰሜን ወሎ ዞን አመራር ሆኖ ሰርቷል። የባድመ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ ወደ ወታደራዊ አመራርነት የተመለሰው አሳምነው ጽጌ፣ የቀደመ የትግል ልምዱን መነሻ በማድረግ ያለአንዳች ማዕረግ በጦርነቱ ውስጥ በባድመ የጦር ግንባር 22ኛ ክፍለ ጦርን እየመራ ተዋግቷል። ባድመ ላይ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ሲውለበለብ ከነበሩት ጥቂት አመራሮች አንዱ አሳምነው ጽጌ ይገኝበት … [Read more...] about ሁለቱ ጄኔራሎች
ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከራሳቸው ማዳን!
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ተስፋን-በጥንቃቄ (cautious optimism) ካነገቡት ሰዎች አንዱ ነኝ። የተስፋዬ መሠረቶች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ሥልጣን የመጡበት መንገድ፣ የገቧቸው ቃልኪዳኖች እና አሁን የታየው መረጋጋት ናቸው። አሁን የታየው መረጋጋት ስል የቄሮዎች የአደባባይ ተቃውሞ መቆሙን ማለቴ አይደለም። ተቃዋሚዎችን እያሳደዱ መከታተል፣ ማዋከብ እና ማሰር ርቀን ሳንሔድ አምና ከነበረው አንፃር እንኳ ልዩነቱ የትየለሌ ነው። ለዚህ የራሴን ስሜት እና ተሞክሮ ነው በምሳሌነት የማቀርበው። በፊትም አሁንም ሐሳቤን በነጻነት እገልጻለሁ። ነገር ግን አምና እና ካቻምና ከያንዳንዱ ጽሑፎቼ/ንግግሮቼ ቀጥሎ እስር ይመጣል እያልኩ እየሰጋሁ ነበር የማደርገው። አሁን ምን ያክል ይዘልቃል የሚለው ቢያሰጋኝም እታሰራለሁ እያልኩ በየደቂቃው አልባትትም። በፊት ሲያስሩ፣ ሲያዋክቡ እና ሲከስሱ ከነበሩት … [Read more...] about ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከራሳቸው ማዳን!
ይድረስ የፈጣሪን ስም ለጠሩ ዶ/ር አብይ አህመድ
በ 44 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ መሪ በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ “ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” እያሉ ንግግርዎን ሲያሳርጉ አይቶ ሕዝበ ኢትዮጵያ በደስታ ተሞልቷል። እኔ ግን እያሉ ያሉት ይህ የማሳረጊያ ቃል በሕዝብ ፊት ብቻ ሳይሆን በአምላክ ፊት ምንና ምንን በሃላፊነት ሊያስጠይቅዎ እንደሚችል የነገሩ ክብደት እጅግ አሳስቦኛል። የፈጣሪ ስም ከተነሳ ዘንዳ፥ ይህ ፈጣሪ የሚሰጠን በረከት ምንነት ይታወቅ ዘንድ ያስፈልጋል። “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” ሲባል ዝንተ አለም አሳልፈን ዛሬን ደረስን። እስከ ዛሬ “ትዘረጋለች” ከማለት አልፈን “ዘረጋች” ወደማለት ሳንሸጋገር ሦስት ሽህ ዓመታት ጠበቅን። በዚህ ፅሁፌ ይህ 3000 ዓመታት ያስቆጠረው ትንቢት ተፈፀመ የሚያስብለው ሁኔታ ምን እንደሆነና፤ የፈጣሪን በረከት የጠየቁት እርስዎ ስለዚህ በረከት ሊኖርዎት … [Read more...] about ይድረስ የፈጣሪን ስም ለጠሩ ዶ/ር አብይ አህመድ
የቄሮ ማንነት ላልገባቸው
ሰሞኑን “ቄሮ ቃር እንዳይሆን” በሚል ርዕስ አቶ ሽሽጉ በሚባሉ ግለሰብ የተጻፈ ማስታወሻ በአይጋ ፎረም ላይ ታትሞ በጥሞና አንብቤ ነበር። አቶ ሽሽጉን በዚች ቀውጢ ሰዓት እንደዚህ ዓይነት ጽሁፍ ለማውጣት የገፋፋቸው አንዳች ዓይነት ምክንያት ቢኖር ነው ብዬ ስለገመትሁ፣ የግል አስተያየታቸውን የመሰንዘር ህገ መንግሥታዊ መብታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ከቅንነት ተነስተው የተሰማቸውን ለሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ለማሳወቅ ካላቸው በጎ ግምት ተነስተው ነው እንደዚህ ዓይነት ድምዳሜ ላይ የደረሱት ብዬ ለማለፍ ሞከሬ ነበር። ግን ደግሞ፣ በኔ ግምት ድምዳሜያቸው የተሳሳተ ስለሆነ፣ ይህንን የተሳሳተ ግምታቸውን በቅንነት ላይ የተመሰረተ ዕርምት ለማድረግና ለሌሎችም ጉዳዩን በደንብ ላልተረዱ ዜጎች ዕውኔታውን በትክክል ለማስቀመጥ ወሰንሁ። ይህ እንግዲህ አቶ ሽሽጉ ስለቄሮ የጻፉትና አንዳች ዓይነት ድምዳሜ ላይ … [Read more...] about የቄሮ ማንነት ላልገባቸው
ሕዝባዊ ጽናትና የHR 128 ጡንቻ “እስረኞች”ን አስፈቱ
አገሪቱን ከሁሉም አቅጣጫዎች ለዓመታት ሲያናውጥ የቆየው ሕዝባዊ ዓመጽ ከHR 128 ጋር ተዳምሮበት ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ የገባው ህወሓት/ኢህአዴግ “አሸባሪ” እያለ በግፍ ያሰራቸውን እየፈታ ነው። የተፈቱት ተመልሰው ላለመታሰራቸው ምንም ዋስትና የለም ተብሏል። ዶናልድ ትራምፕ የፕሬዚዳንትነቱን መንበር ከተረከቡ ጊዜ ጀምሮ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) የተባለው አሸባሪ የበረሃ ወንበዴዎች ቡድን ስሉሱ እንደዞረበት አስተውሎ የራሱን ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል። በጣም ይተማመንባቸው የነበሩትን “ነጭ ወያኔዎች” ህወሓት መናፈቅ የጀመረው ኦባማ የሥልጣን መንበሩን በሚያስረክቡበት የመጨረሻ ዓመት መገባደጃ ላይ ነበር። ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ October 3, 2017 ባቀረበው የዜና ዘገባ ላይ ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ይህንን ማለቱ ይታወሳል፤ ባራክ ኦባማ የሥልጣን ዘመናቸውን … [Read more...] about ሕዝባዊ ጽናትና የHR 128 ጡንቻ “እስረኞች”ን አስፈቱ
WHAT KIND OF LEADERSHIP IS NEEDED IN ETHIOPIA TO AVERT ETHNIC VIOLENCE AT THIS TIME OF CRISIS?
Is the TPLF willing to take the country down with them, thinking they could simply secede from the country as an escape plan and leave the rest with chaos? Allegedly, the TPLF and some of the people of Tigray are seriously considering seceding from Ethiopia, believing they can no longer safely “lead” the country due to the rising opposition and ethnic-based resentment from large numbers of Ethiopians. They may have been shaken by the recent outburst of destruction of Tigrayan or TPLF government … [Read more...] about WHAT KIND OF LEADERSHIP IS NEEDED IN ETHIOPIA TO AVERT ETHNIC VIOLENCE AT THIS TIME OF CRISIS?
The Greedy TPLF Chooses to Master Deceit Rather than Democracy
The Ethiopian majority believes TPLF is autocratic, too primitive and has never measured up to leading the populous and historically significant African country of Ethiopia. It never measured up to the good people of Tigray either. While its ethnocentricity was known of from the beginning, there was some hope by most Ethiopians that it would learn, change overtime and work towards improving the country for all Ethiopians. However, that dream of the majority was quelled immediately and replaced … [Read more...] about The Greedy TPLF Chooses to Master Deceit Rather than Democracy
Elias Wondimu the bridge builder
Whenever and wherever he pauses to communicate, be it in interviews, friendly chats, academic discussions, or in speeches he delivers, Elias Wondimu returns to a common phrase: building bridges. It is like a mantra for him. For all his focus on bridges, he is not a civil engineer in the traditional sense of the word, but he an engineer of a different kind—one who builds bridges with words between generations, ideologies, continents: Elias Wondimu the bridge builder. On February 25, at the Army … [Read more...] about Elias Wondimu the bridge builder
ታጋይ ጎቤ መልኬ በአዴት ጦርነት ተሰዋ፤ “የህወሃት ወራሪ ሃይል ጉዳት ደርሶበታል”
“ጎቤ ሲሰዋ አዳዲስ ጎቤዎች ትግሉን ተቀላቅለዋል’’ “አርበኛ ጎቤ መልኬ ተሰዋ” ሲሉ በአካባቢው የሚገኙ የጎልጉል መረጃ አቀባዮች ገለጹ። ህወሃት የሚመራው ሰራዊት ክፉኛ ጉዳት ደርሶበታል። ዜናው ኢህአዴግ በሚያስተዳድራቸውም ሆነ በሚደጉማቸው መገናኛዎች ይፋ አልሆነም። ለነጻነት ሃይሎች ጋር ግንኙነት አላቸው የሚባሉ አካላትም ይህ ዜና እስከታተመበት ድረስ በግልጽ ያሉት ነገር የለም። አርበኛ ጎቤ እራሱን እንዳጠፋም የሚገልጹ አሉ። በሰሜን ምዕራብ ቆላማዉ ክፍል የደፈጣ ተዋጊዎችን የሚመራዉ ታዋቂዉ አርበኛ ታጋይ ጎቤ መልኬ በህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ዕዝ ስር ባለዉ “አንገረብ” እየተባለ በሚጠራዉ የስለላ ቡድንና በ“ጸረ-ሽብር ግብረ ኃይል ቡድን” የጋራ ዘመቻ በጠገዴ ወረዳ ልዮ ስሙ “አዴት” በተባለ በርሃማ ቦታ ትላንት ማምሻዉን በተካሄደ ዉጊያ ነው “ጎቤ ተሰዋ” … [Read more...] about ታጋይ ጎቤ መልኬ በአዴት ጦርነት ተሰዋ፤ “የህወሃት ወራሪ ሃይል ጉዳት ደርሶበታል”