* “ብልጡን ባለ ራዕይ መሪ” ክፉኛ ናፍቋል! የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር /ህወሃት/ አመራሮች ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ከመግደልና ከማስገደል እንዲታቀቡ ታዘዋል። ግድያው የሚቀጥል ከሆነ ከወትሮው በተለየ ርምጃ እንደሚወሰድ ተነግሯቸዋል። “ወልቃይትን ለባለቤቱ ህዝብ ብንመልስ ይሻላል” በሚሉና “አንመልስም” ሲሉ በሚቃወሙ መካከል ክርክር የጀመረው ህወሃት ስምምነት ሊደርስ አልቻለም። ሁኔታው መለስን ከመቃብር ቀስቅሷል። አባይ ጸሃዬ፣ ሳሞራ የኑስና ሌሎች ባለስልጣናት አሜሪካ እንደነበሩ ለጎልጉል ጠቁመው የነበሩት የመረጃው ምንጮች እንዳሉት ባለስልጣናቱ ግድያ እንዲያስቆሙ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ተቀብለዋል። በአማራ ክልል የተነሳው ተቃውሞ ያሳሰበው ህወሃት በተመሳሳይ አሜሪካ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ወደ ሰላማዊ ድርድር እንዲመጡ ጫና እንድታደርግ ጠይቀዋል። ለዚህም ይመስላል በአሜሪካ በኩል የተቀናቃኝ … [Read more...] about ወልቃይትን ለባለቤቱ ህዝብ ለመመለስ ህወሃት እየመከረ ነው
Uncategorized
“የማን ተጋድሎ ነው…?”
ወያኔ ኢትዮጵያን እያፈራረሰና ህዝቡን ‘ርስ በርስ እያባላ ያለው ብቻውን አይደለም። የሀገሪቱ ጠላቶች፣ ሆድ-አደሮች፣ መሀል-ሰፋሪዎች፣ ግብዞችና የመሳሰሉ ሁሉ አጋጣሚውን ይጠቀማሉ። ሲጠቀሙም ኖረዋል። ወያኔና ግብረ–አበሮቻቸው እኮ ኢትዮጵያን የማፈርስረሱን መረሀ-ግብር የተቀበሉት ከምዕራቡና ከዐረቡ ዓለም ነው። መርሳት የሌለብን ወያኔ ከዚህ ደረጃ እንዲደርስ የኛ አስተዋ’ጾ መሆኑን መቀበል አለብን። ማርቲን ሉተር ይመስለኛል፤ "ካልተጎነበስክላቸው እነሱ ከአንተ ጀርባ ላይ አይወጡም!" ያለው። ቁምነገሩ ካለፈው መማር መቻላችን ላይ ነው። በርግጥ አሁን ብዙሀኑ የወያኔን “አሪወሳዊነት” ከማንኛውም ግዜ በበለጠ የተረዳበትና የ40 ዓመት የከፈፍለህ የቤት ስራ "ፉርሽ" የሆነበት ነው። ይሁን እንጂ ብዙ ድህረ-ገጾች፣ ዜና – ዘጋቢዎች፣ ዘፋኞች፣ ሰላማዊ … [Read more...] about “የማን ተጋድሎ ነው…?”
ቅኝ ተገዥነቱን ያወቀ ሕዝብ በከፊል ነፃ ነው!
የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሬ ወያኔ ቅኝ ተገዥ ከሆነ ድፍን 25 ዓመት ሆነው። በእነዚህ ረጅም ዓመታት፣ የተማሩትም ሆነ ያልተማሩት ዜጎች፣ በቅኝ ተገዥነት መያዛቸውን ያወቁትም ሆነ ለማወቅ የጣሩት በጣም ጥቂቶች ናቸው። እነዚህ በቅኝ ተገዥነት ተይዘናል ያሉት የጥቂቶቹ ድምፅ፣ በብዙኃኑ፣ ከሁሉም በላይ በጎሣ ፖለቲከኞቹ ድምፅ ተውጦ፣ ወያኔ፣ ያላንዳች ሀግ ባይ፣ ሩብ ምዕተ ዓመታት የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት በእጅጉ የጎዱ ሥራዎችን እንዲሠራ ሠፊ ዕድል ሰጠው። በመሆኑም የኢትዮጵያዊነት አያያዥ ማገርና ወራጅ፣ መሠረትና ጭምጭም የነበሩትን፣ የኢትዮጵያዊነት ዕሴቶቻችን ከሥራቸው ነቀላቸው። ሕዝቡን በነገድ ከፋፍሎ እሣትና ጭድ አደረጋቸው። የኢትዮጵያ ነገዶች ሙጫ በመሆን ከሌሎች ነገዶችና ጎሣዎች ጋር ሰምና ፈትል ሆኖ፣ ኢትዮጵያዊነትን ሲገነባ የኖረውን የዐማራ ነገድ፣ በዘር ጠላትነት … [Read more...] about ቅኝ ተገዥነቱን ያወቀ ሕዝብ በከፊል ነፃ ነው!
በሕዝብ ደም የሥልጣን ዕድሜ ማርዘም!
በዓለም ላይ ከሚታዩት መንግሥታት ውስጥ ሁለት ዓይነት መንግሥታት ጎልተው የሚታዩ ሲሆን፤ ሁለቱም ወደ ሥልጣን እርካብ የሚወጡበት መንገድ የተለያየ ነው። አንደኛው በሕዝብ ምርጫና ፍላጎት፣ በዴሞክራሲ መንገድ ሥልጣኑን ለተወሰነ ዓመት የሚረከብ ሲሆን ሌላው ደግሞ በራሱ ፍላጎትና ውሳኔ፣ የሕዝብን ድምፅና ፍላጎት ሳይሰማና ሳይጠይቅ በመሣሪያ ኃይል አስፈራርቶና ደምስሶ የሥልጣኑ ባለቤት የሚሆን ነው። የመጀመሪያውን የስልጣን ባለቤትነትን የሚከተል የግድ የዲሞክራሲን ሕግና ባህል የተቀበለና በዛም የሚያምን መሆንን፣ ችሎታንና ሕዝባዊነትን፣ አገር ወዳድነትን ይጠይቃል። በሁለተኛው የስልጣን አወጣጥ ግን ሃይልን፣ ማንአለብኝነትን፣ የተከተለ ጭካኔን ብቻ የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም አምባገነንና ፈላጭ ቆራጭ ተብለው ይጠራሉ ወይም ይመደባሉ። አገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት ዘመናት በሁለተኛው ዓይነት … [Read more...] about በሕዝብ ደም የሥልጣን ዕድሜ ማርዘም!
“[እምቢ ካሉ] አጠቃላይ የትምህርት ሥርዓቱን የሚያሽመደምድ ስልት አለን”
ህወሃት ኦህዴድን ለማጽዳት በሚል ከ800 የሚበልጡ ሃላፊዎችን በየእርከኑ ቢያሰናብትም ለውጥ የሚታይ አልሆነም። ይልቁኑም የተጠኑ በሚመስሉ ማህበራዊ ጉዳዮች መናጡ እየተባባሰ ነው። አቶ ጃዋር መሐመድ ኢህአዴግ የቀረበለትን “የምክር ሃሳብ” የሚሰማ ካልሆነ አጠቃላይ የትምህርት ስርዓቱን የሚያሽመደምድ ስልት አለን ማለታቸው “እንዴት” የሚል ጥያቄ ቢያስነሳም ጆሮ ያገኘ ወሬ ሆኗል። ይህንኑ ተከትሎ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ጉዳዩን ከተወዳጁ ደራሲ በአሉ ግርማ ትንቢታዊ ድርሰት ጋር በማያያዝ “የኢህአዴግ ኦሮማይ እየተቃረበ ነው” ሲሉ በድፍረት ተናግረዋል። በትላንትናው እለት የቪኦኤ አማርኛ ክፍለ ጊዜ ካቀረበው ቃለ ምልልስና ካጠቃላይ እውነታዎች ለመረዳት እንደተቻለው ኦሮሚያ ውስጥ የተጀመረው “ሰላማዊ” ትግል እየበሰለ የሄደ ይመስላል። ቀደም ሲል በተደረጉ የድርጅትና የውስጥ ግንኙነቶች የኦሮሞዎች … [Read more...] about “[እምቢ ካሉ] አጠቃላይ የትምህርት ሥርዓቱን የሚያሽመደምድ ስልት አለን”
The treasonous May criminals and their bloody police state
Wincing in terror and shedding tears of blood, more than 85 million disillusioned Ethiopians are this week solemnly remembering how their beloved nation, nicknamed Africa’s Yugoslavia, was stripped of sovereignty to a degree not seen in Africa or elsewhere since the end of the Second World War. It happened 25 years ago in May 1991, and after being dismantled, the impoverished East African nation was permanently placed under brutal Tigre regency in the hands of melancholic secessionist Tigre … [Read more...] about The treasonous May criminals and their bloody police state
«የእሣት ልጅ አመድ» የሆነው የዘመኑ ኢትዮጵያዊ ታሪካዊ ማንነቱን ያስከብር!
ከዛሬ ሰማኒያ ዓመታት በፊት የነበሩት ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን እና እናቶቻችን፣ ከትግራይ እና ከኤርትራ ምድር በበቀሉ ባንዶች አጋዥነት በፋሽስት ጣሊያኖች ጦር ማይጨው ላይ ድል ሲመቱ «እሺ፣ አሜን፣ እንገዛለን» ብለው እጃቸውን አጣጥፈው አልተቀመጡም። ራሣቸው ፋሽስቶችም እንዳመኑት፥ በተለይ በሰሜን ሸዋ፣ በጎጃም፣ በጎንደር፣ በወሎ፣ በጉራጌ፣ በጅባት እና ሜጫ እንዲሁም በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች የነበሩት አርበኞች በመረጧቸው የጎበዝ አለቆቻቸው እየተመሩ፣ ለአምሥት ዓመታት የፋሽስት ጣሊያንን ጦር ከእነ ባንዳ ግሣንግሱ መውጫ መግቢያ አሣጥተውታል። ከዚያም ከየካቲት 1933 ዓም ጀምረው ጀግኖች አርበኞቻችን ባደረጉት የተቀነባበረ የጥቃት ዘመቻ ልክ የዛሬ 75 ዓመት ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓም በቀዳማዊ ኃይለሥላሤ መሪነት በድል አድራጊነት ዋና ከተማችንን አዲስ አበባን ለመቆጣጠር … [Read more...] about «የእሣት ልጅ አመድ» የሆነው የዘመኑ ኢትዮጵያዊ ታሪካዊ ማንነቱን ያስከብር!
Shengo’s Press Release Regarding the US Senate Resolution
Following the European Parliament’s Resolution of January 21, 2016 on the situation in Ethiopia “strongly condemning the recent use of excessive force in Oromia and in all Ethiopian regions,” Shengo expressed its appreciation to the EU and called upon the Congress of the United States to take a similar stand. In this regard, we recognize the concerted and relentless campaign made by Ethiopian civil society, political, spiritual and professional groups as well as individuals. The United States … [Read more...] about Shengo’s Press Release Regarding the US Senate Resolution
የመተማመን መትነን (Trust Evaporation)
በመጀመሪያ ደረጃ መተማመን (Trust) ስንል የአንድ ህብረተሰብ የጋራ ሃብት ወይም የማህበራዊ ካፒታል ዋና ኣካል መሆኑን እናንሳ። በአጠቃላይ ማህበራዊ ካፒታል ስንል ደግሞ ልክ እንደሌሎቹ የሰው ልጆች ካፒታል የሚታይ ነው። ለምሳሌ የገንዘብ ካፒታል፣ የሰው ካፒታል (Human capital) እንደምንለው ማህበራዊ ካፒታልም ካፒታል ይባላል። ካፒታል ነው እንደንል የሚያስችለን ምክንያት ኣንድም ልክ እንደሌሎቹ ካፒታሎች የሚመረት (Produce የሚደረግ) መሆኑና ለተለያዩ የማህበረሰብ ልማቶች ኢንቨስት የምናደርገው ሃብት በመሆኑ ነው። እነዚህ ተፈጥሮዎቹ ከሌሎች ካፒታሎቻችን ጋር ያመሳስሉታል። የሰው ልጅ የሚያመርተውና ለተለያየ ልማቱ የሚጠቀምበት ይህ ማህበራዊ ካፒታል ልክ ሌሎች ሃብቶችን ለማምረት አቅደን እንደምንሰራው ተጠንቅቀን ልናሳድገውና ልንይዘው በኣስፈላጊው ቦታና ጊዜ ሁሉ … [Read more...] about የመተማመን መትነን (Trust Evaporation)
ህወሃት ራሱን “ሳያጸዳ” በሌላው ዘምቷል
“የኢህአዴግን መርህ እስከተከተለ ድረስ መሃይምም ቢሆን ሚኒስትር እናደርጋለን” ያሉት መለስ ዙሪያቸውን “የበታች” በሆኑ ሹሞች አስከብበው የቆዩት ያለምክንያት አልነበረም፡፡ “አዋቂ፣ ጠቢብ፣ ባለራዕይ፣ ምንተስኖት፣ …” የሚሉ “ማዕረጎችን” አስገኝተውላቸዋል፡፡ ከዚህ አንጻር የፈለጉትን ሥልጣን ላይ ያስቀምጣሉ፤ ከዚያ በሙስና ያበሰብሳሉ፤ ከዚያም ወደ “ቆሻሻ ቅርጫት” ይጥላሉ፡፡ በሕይወት ለቆዩት “ቅርጫቱ” ትልቅ መድህን ሲሆን ለዚያ ያልታደሉት ግን ትርጉሙ ሌላ ነው፡፡ ይህ የመለስ አሠራር የህወሃት መመሪያ ሆኖ ቆይቷል፤ አሁንም እየተሰራበት ነው፡፡ በኦሮሞ ከተሞች በተነሳው ሕዝባዊ ንቅናቄ የተደናገጠው ህወሃት ከረፈደ “ጽዳት” ጀምሯል፡፡ የችግሩ መንስዔ ራሱ ሆኖ “ልክ መግባት” ሲገባው ለህዝብ “ሥራ ላይ ነን” ለማለት “የኦህዴድን አመራሮች” ማንሳቱ አስታውቋል፡፡ የጎልጉል እማኝ … [Read more...] about ህወሃት ራሱን “ሳያጸዳ” በሌላው ዘምቷል





![“[እምቢ ካሉ] አጠቃላይ የትምህርት ሥርዓቱን የሚያሽመደምድ ስልት አለን”](https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2016/06/students-exam1-e1465002659834-300x148.jpg)



