• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የማን ተጋድሎ ነው…?”

August 16, 2016 12:15 am by Editor Leave a Comment

ወያኔ ኢትዮጵያን እያፈራረሰና ህዝቡን ‘ርስ በርስ እያባላ ያለው ብቻውን አይደለም። የሀገሪቱ ጠላቶች፣ ሆድ-አደሮች፣ መሀል-ሰፋሪዎች፣ ግብዞችና የመሳሰሉ ሁሉ አጋጣሚውን ይጠቀማሉ። ሲጠቀሙም ኖረዋል። ወያኔና ግብረ–አበሮቻቸው እኮ ኢትዮጵያን የማፈርስረሱን መረሀ-ግብር የተቀበሉት  ከምዕራቡና  ከዐረቡ ዓለም ነው። መርሳት የሌለብን ወያኔ ከዚህ ደረጃ  እንዲደርስ የኛ አስተዋ’ጾ መሆኑን መቀበል አለብን። ማርቲን ሉተር ይመስለኛል፤ “ካልተጎነበስክላቸው  እነሱ  ከአንተ  ጀርባ  ላይ  አይወጡም!” ያለው። ቁምነገሩ ካለፈው መማር መቻላችን ላይ ነው።

በርግጥ  አሁን  ብዙሀኑ  የወያኔን  “አሪወሳዊነት”  ከማንኛውም  ግዜ  በበለጠ  የተረዳበትና  የ40 ዓመት የከፈፍለህ የቤት  ስራ “ፉርሽ” የሆነበት ነው። ይሁን  እንጂ  ብዙ  ድህረ-ገጾች፣  ዜና – ዘጋቢዎች፣ ዘፋኞች፣  ሰላማዊ ሰልፎኞች፣ የፓለቲካ ተንታኞች፣ መግለጫዎችና የመሳሰሉት በሚያሳዝንና በሚያሳፈር ሁኔታ ከወያኔ የጎሳ ወጥመድ ያለመላቀቃችን፤ “አንድ ‘ርምጃ  ወደፊት፣  አንድ ‘ርምጃ ደግሞ  ወደ  ኋላ” መሆኑ  በግዜ  ሊታሰብበትና ሊታረም የሚገባ ጉዳይ ነው። እናም  የምንናገረውንና  የምንጽፈውን  በጥንቃቄ መመርመርና፤ ወያኔ  የማይቆፍረው  ጉድጎዳ፣ የማያፈሰው  ደም እንደሌለ ከምንግዜውም  የበለጠ አሁን  መረዳት  ያስፈልጋል።

  • “የአማራ ተጋድሎ!….. የኦሮሞ ተጋድሎ!….. የመሳሰሉ ዜናዎችና  መፈክሮች   የሚያመለክቱት አሁንም   ደም እንደጎርፍ  እየፈሰሰና ምድራዊን ስቃይ እየተቀብለን፣ ወያኔ ካሰመረልን የጎሰኝነት  ስሜት  ያለመውጣታችን የሚያመለከት ነው። ለምንድን ነው “የኢትዮጵያኖች ተጋድሎ!” የማንለው?…..እድግመዋለሁ፤ “የኢትዮጵያዊኖች ተጋድሎ!”። አማሮች እንዲህ… አድረጉ… ኦሮሞዎች እንዲህ ሆኑ… አደረጉ…. ወዘተ…. እያልን፤ በአንድ  አካባቢ  አንድ  ወጥ  ህዝብ   እንዳለ  አድርገን  ማቅረባችንና  መዘገባችን  ይቁም። በተለይም ኢሳት (ቲቪና  ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ህዝብን ዓይና ጆሮ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በዚህ ጉዳይ ግን ቢያስብበት መልካም ነው እላለሁ።

በዚች ሰዓት ጋምቤላዎች  የከፍሉት መሰዋ’ትነና  እየከፈሉት  ያለው  ተጋድሎ፣  የኦጋዴኖችና  አንዲሁም  በተለያየ ግዜ በተለያዩ የሀገሪቱ  ግዛቶች  ከወያኔ ጋር የሚተናናቁት ሁሉ የኢትዮጵያኖች ያውም  የዚህ ኢትዮጵያዊ ትውልድ ተጋድሎ እንጅ የማን ሊባል  ይችላል? ካላያማ ከወያኔ በምን ተለየን? የተጀመረውን የጸረ-ወያኔ  የጎሳ ከፋፍለህ  ግዛው እንዴት ነው  የምናከሽፈው? “የዚያ  ጎሳ  ተጋድሎ!.. የዚህ ጎሳ ተጋድሎ!….” እያልን  እንዴት  አድርገን  ነው  ትግሉን ለህዝባዊ ፣ ለሁሉም  ኢትዮጵያዊ  ድል  የምናበቃው?

  • ሌላው የስሞኑን ህዝባዊ አመጽ ያቀጣጠለው የወልቃይት ጉዳይ  ነው። የወልቃይት ጥያቄ የሁሉም  ኢትዮጵያዊ ጥያቄና  ትግል  ነው። ኢትዮጵያዊ  ዜጋ  ነኝ  የሚል ሁሉ ይመለከተዋል። ይሁን እንጂ “ወልቃይት አማራ!…” የሚለው አባባል፣ መፈክርና ቀረርቶ የወያኔ የጎሳ ስራ መስራቱን ነው የሚያመለክተው። “ወልቃይት …  የጎንደር አንዱ ግማድ ነው፤ ለዚህም የህይወት መሰዋትነት ብቻ አይደልም፤ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመበት ያለ ህዝብ ነው። ያ ማለት ደግሞ “ወልቃይት – ጎንደር፤ ጎንደር – ኢትዮጵያ  ነው።” ይህም ማለት “ኢትዮጵያ ከሌለች – ወልቃይት – ጎንደር የለም”። ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚስማመው “በኢትዮጵያዊያን ተጋድሎ!….” ነው። ትግሉ የሁሉም ኢትዮጵያዊ  መሆኑ  በዚህ ሰዓት መዘንጋት  የሌለበት ጉዳይ ነው። ለመሆኑ የሌላው ኢትዮጵያዊ ተጋድሎና መሰዋትነት የት ሊጣል ነው? የአብሮነት ትግል ባላማካሄዳችን አይደልም ወይ፤ ወያኔና  ሆድ-አደሮቹ ሀገራችን የግላቸው እቃ አድርገው ህዝብን እንደቅጠል የሚያረግፉት።
  • ወያኔ ለኢትዮጵያ ጎሳዎች ብሎ   የጫነብን  ሰንደቅ –ዓላማ፤  በየተኛውም  ኢትዮጵያዊ ተቀባይነት  አለመኖሩ ብቻ  አይደለም፤ ነባሩ ሰንደቅ – ዓላማ የኢትዮጵያ ህዝብ የአንድነትና   የተጋድሎ  መግለጫ   መሆኑን እያስመሰከረ  ነው።  ስለዚህም  በህዝባዊ  አመጽ   ወቅት  የቡድን  ወይም  የድርጅት  ሰንደቅ  ዓላማ  ይዘን መውጣታችን ይከፋፍለናል እንጅ  አንድ  አያደርገንም። በርግጥ  በአንዳንድ  የደቡብ  ክፍል  የወያኔ ካድሪዎች የአንዳንድ ድርጅቶችን “ሰንደቅ  ዓላማ” ይዘው  በመውጣት  ህዝብን  ለመምታትና  ለመከፋፈል  እየተጠቅሙብት  ቢሆንም፤ እኛ ግን አንድነታችን  በተግባር  እናስመስክር። እየተከፈለ  ያለው  የህይወት መሰዋትነት  ነው።
  • ሰሞኑን  ከተቀሰቀሰው ህዝባዊ አመጽ ጋር  አንዳንድ  ዘፋኞች  ከትግሉ  ጋር  በተያያዘ   ነጠላ ”የቅሰቀሳና የውዳሴ”  ዜማ ለቀዋል፡:  በተለይም ስለ  “ወልቃይት-ጎንደር፣ …….ስለ ኦሮሚያ፣….  ወዘተ።  ይሁን  እንጂ  በ’ኔ እይታ ዜማዎቹ  በደንብ  የታሰበባቸው አይደሉም። “ኢትዮጵያዊ”  አንድምታ  የላቸውም። ተጋድሎውና ህዝባዊ  አመጹ የመላው  ኢትዮጵያዊ በመሆኑ  ዜማዎቹም  የሁሉንም  ኢትዮጵያዊያን አንድነትና  ጅግንነትን የሚያወድሱና የሚቀሰቅሱ   መሆን  ሲገባቸው  በአካባቢያቸው  ተወስነዋል።   የወያኔች  በጎሳ  ላይ  በተመሰረተ የጥላቻና  የግብዝነት  ከበሮ -ድለቃ ፤ የምን ያህል የወርዱና  የዘቀጡ ኅሊና ያልፈጠረባቸው መሆናቸውን የሚያመለክት ሆኖ ሳለ፤ የ’ነሱን  ፈለግ  መከተሉ “በአንድ  አፍ  ሁለት  ምላስ  …” ይሆንብናል። “ወልቃይት ብረሳሽ፣ ቀኜን ይርሳኝ!..!” ከማለት “ኢትዮጵያ … ብረሳሽ፣ ቀኜን  ይርሳኝ!” ብሎ ቢያንጎራጉር፤ ለአንድነታችንና ለትግላችን የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ ነው። ለወያኔም  የራስ  ምታት  ነው።  ኢትዮጵያ እንዳትኖርና  እንድትፈራርስ እኮ ነው  ወልቃይትና ሌሎችም አካባቢዎች  ለወያኔ  የተከለሉትና  ለሱዳን  እጅ መንሻ የሚቀርቡት። እናም በተቻለ መጠን የትግል ዜማችን የሁላችንም ሀገር ልናደርጋት መሰዋ’ት  ለምንከፍልላት  ኢትዮጵያችንና  ህዝባችን  ይሁን።

ያለፉትም ሆነ አሁን ያሉት “ጅግኖቻችን” የከፈሉት መሰዋትነትና እየከፈሉ ያሉት ለኢትዮጵጵያና ለኢትዮጵያዊያን ነው። ታዲያ እነዚህን የክብር የኢትዮጵያዊያን ጀግኖች ወደ መንደርተኛነት ማውረድ ምን ይሉታል?። ቢቻል በዚህ ሰዓት ዘፋኞች  በህብረት ለሁሉም ኢትዮጵያዊ  የሚሆን  በተለያዩ የሀገሪቱ ቋንቋዎች ዜማ ቢለቁ ለትግሉም ሆነ ለአንድነታችን የበኩላቸውን አስተዋ’ጾ ያደርጋሉ። በዚህ ጉዳይ ላይ በተለይም ባህር-ማዶ የምትገኙት እንደ አለምፀሀይ  ወዳጆና  ታማኝ  በየነ ያላችሁ፤ የጥበብ ሰዎችን እንደተለመደው  ብታሰተባብሩ ”ለቀባሬው ማርዳት” ባይሆንብኝም  መለዕክቴ  ይድረሳችሁ።

ፊልጶስ / ነሀሴ 2008 / E-mail: philiposmw@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule