• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሕዝብ ደም የሥልጣን ዕድሜ ማርዘም!

June 21, 2016 12:34 pm by Editor Leave a Comment

በዓለም ላይ ከሚታዩት መንግሥታት ውስጥ ሁለት ዓይነት መንግሥታት ጎልተው የሚታዩ ሲሆን፤ ሁለቱም ወደ ሥልጣን እርካብ የሚወጡበት መንገድ የተለያየ ነው።

አንደኛው በሕዝብ ምርጫና ፍላጎት፣ በዴሞክራሲ መንገድ ሥልጣኑን ለተወሰነ ዓመት የሚረከብ ሲሆን ሌላው ደግሞ በራሱ ፍላጎትና ውሳኔ፣ የሕዝብን ድምፅና ፍላጎት ሳይሰማና ሳይጠይቅ በመሣሪያ ኃይል አስፈራርቶና ደምስሶ የሥልጣኑ ባለቤት የሚሆን ነው።

የመጀመሪያውን የስልጣን ባለቤትነትን የሚከተል የግድ የዲሞክራሲን ሕግና ባህል የተቀበለና በዛም የሚያምን መሆንን፣ ችሎታንና ሕዝባዊነትን፣ አገር ወዳድነትን ይጠይቃል። በሁለተኛው የስልጣን አወጣጥ ግን ሃይልን፣ ማንአለብኝነትን፣ የተከተለ ጭካኔን ብቻ የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም አምባገነንና ፈላጭ ቆራጭ ተብለው ይጠራሉ ወይም ይመደባሉ።

አገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት ዘመናት በሁለተኛው ዓይነት በስልጣን ላይ በተቀመጡ አምባገነኖች በሚከተሉትና በሚያሰፍኑት ስርዓት ስር ስትማቅቅ የኖረች አሁንም እየማቀቀች የምትገኝ አገር ነች።ሌሎቹም የቅርብና የሩቅ የጎረቤት አገሮች እንደዚሁ በአምባገነን በሆኑ በተመሳሳይ ዓይነት ስርዓቶች ስር የሚማቅቁ ናቸው።

የአምባገነን መንግሥት ወይም ስርዓት የስልጣን ዘይቤ አመጽና ጦርነትን መሰረት ያደረገ ነው። በዚህ አስተሳሰብ የተለከፉት በጦርነትና በሃይል ስልጣን ይይዛሉ፣በጦርነትና በሃይልም የስልጣን ዕድሜያቸውን ያራዝማሉ። ለእነሱ ሰላምና የሕዝብ መረጋጋት አጥፊያቸው ነው። ሰላም የማይኖርበትን መንገድ ይፈጥራሉ፤ ሁልጊዜ ሕዝብ በስጋትና በፍርሃት እያደረ ወደ እነሱ አጥፊ ስርዓት ፊቱን እንዳያዞርና የትግል ስሜቱ እንዲኮላሽ ያደርጋሉ። ከነዚህም ዋናውና አንዱ ስልታቸው በአገር ውስጥና በጎረቤት አገር ሽብርና ጦርነት የሚነሳበትን መንገድ መፍጠርና “አገርህ በውጭ ወራሪ ሃይል ተከበበች ወይም ተወረረች” የሚለው የክተት ጥሪ ማወጅ ይሆናል።በራሳቸው አናት ላይ ያለውን ሸክምና አደጋ በሕዝቡ ትከሻ ላይ ለመወርወርና ትኩረቱን ለመቀየር የማይገለብጡት ድንጋይ የለም።

ይህን የጥፋት መልእክት የሚቃወሙትን በመግደል፣ እምቢ ያሉትን አፍሶ በማስገደድ የጦር ሜዳ ጭዳ ያደርጉታል። ስልጣን ሲይዙ የሕዝቡን ደም በማፍሰስ እንደሆነው ሁሉ በሥልጣንም ላይ ለመቆየት እንዲሁ ሕዝብ ደሙን እንዲያፈስላቸው በማስገደድና በማታለል ሰፊ ዘመቻና ዝግጅት ያደርጋሉ። በጦርነቱም ጊዜ ሆነ ማግስት ለሕዝቡ የሚተርፈው ነገር ቢኖር፣ በጦር ሜዳ መሞት፣ መቁሰል፣ አካለጎደሎ መሆን፣ የንብረት መውደም፣ መፈናቀል፣ በስንቅና ትጥቅ የግልና የአገሪቱን ሃብት ማባከን ነው። ከዚያም በላይ ጦርነቱ ሲያልቅ በሕዝብ መካከል የማይከስም የእርስ በርስ ጥላቻና ቋሚ ጠላትነት መፍጠር ይሆናል።

የሰሞኑም በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ተከሰተ የተባለው ግጭት በሥልጣን ላይ የተቀመጡት ሁለት አምባገነኖች የሚጫወቱት የዚሁ የሥልጣን አድን ቲያትር ውጤት ነው።ያለፈውም ሆነ በየጊዜው የሚነሳው ውጥረትና ግጭት የወያኔና የሻእብያ የጥቅም ግጭት እንጂ የሕዝብ ግጭት አይደለም። ሁለቱም አምባገነን ሥርአቶች በሕዝብ የተጠሉ ናቸው። ሁለቱም መንግሥት ነን ባይ ቡድኖች እጃቸው በንጹሃን ደም የጨቀዬ ነው። በሁለቱም ስርዓቶች ስር የሚኖረው ሕዝብ ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚያደርገው ትግል እያደገ በመሄድ ላይ ነው። ይህንን ሕዝባዊ አመጽና ትግል ለማፈንና ለማቀዝቀዝ ያላቸው አንዱና ቀሪው መሳሪያ “አገርህ ተወረረች” በሚል ጩኸት ማደናገርና በእነሱ ላይ ያነጣጠረውን ፍልሚያ ለጊዜው እንዲረሳና ወደ አላስፈላጊ ጦርነት ገብቶ እርስ በርሱ እንዲተላለቅ ማድረግ ነው። የዚህ አይነቱ ስልት የዛሬ አስራ ስድስት ዓመት የተጠቀሙበት ሲሆን የብዙ መቶ ሽህ ንጹሃን ደምና የአገር ሃብትና ቅርስ ወድሞ እስከ አሁንም በሥልጣን ላይ ለመቆየት እረድቷቸዋል። የሰሞኑም ተንኳሽ ግጭት ከዚያ የተለየ አይደለም። ያለፈው ጦርነት ለሕዝብ አለመተማመንና መራራቅ እንዳገለገለ ሁሉ ያሁኑም በሁለቱም ተንኳሽነት የሚካሄደው ግጭት ወደ ከፍተኛ ጦርነት ቢያመራ ከሚያደርሰው የሕይወትና የሃብት ጥፋት በላይ ከዚያ ለከፋ ለከባቢ ቀውስና ለሕዝብ ቋሚ ጠላትነት የሚዳርግ ይሆናል።

ህወሃት/ኢሕአዴግ ባለፈው ጊዜ ከሻእቢያ ጋር ባደረገው ጦርነት የኢትዮጵያን መብት፣ ክብርና ዳር ድንበር እንዳላስጠበቀና እንደውም ጎጂ በሆነ ውልና መደራደር የአገራችንን ጥቅም አሳልፎ የሰጠ፣ የአገር ክህደት የፈጸመ፣ ለውጭ ሃይሎች ጣልቃ መግባትና በሰላም ፈላጊነት ሽፋን ከመጠቀም ሌላ ያመጣው ጥቅም የለም። አሁንም የዚህ የጦርነት አዝማሚያ ለቀጣይ የሁለት አምባገነኖች እርቅና ድርድር መንደርደሪያ ሊሆን ይችላል። ከድርድር በዃላም የሚገኘው ውጤት የኢትዮጵያን ህልውናና ታሪካዊ መብት የሚያፈርስና አሳልፎ የሚሰጥ እንጂ የሚያረጋግጥና የሚያስከብር አይሆንም።

በኤርትራ የሰፈነው ሥርዓትና መንግስት ለኢትዮጵያ ቅንጣት ያህል አይጨነቅም፤ሙሉ ለሙሉ ተበታትናና ተዳክማ ብትኖር ፍላጎቱ ነው። ጠንካራ ኢትዮጵያ፣ አንድነቷን የጠበቀች ኢትዮጵያ፣ ዴሞክራሲ የሰፈነባት ኢትዮጵያ ለእሱ መኖር አደጋ ነው። ለጊዜው ከህወሃት መራሹ ኢሕአዴግ የተጣላ ቢመስልም፣ እንደ ህወሃት መራሹ ቡድን ሊያገለግለው የሚችል ሌላ ቡድን ካልፈጠረ በስተቀር ኢትዮጵያን በማፈራረሱ ደረጃ ከወያኔ የተሻለ አጋር ሊኖረው እንደማይችል ያውቀዋል። ህወሃት/ኢሕአዴግም እንደዚሁ። የአሁኑም እሰጥ አገባ የሁለት ወዳጆች ጊዜያዊ ጠብ ነው።አህያ ላህያ ቢራገጥ ጥርስ አይሳበርም!!እንዲሉ። ይህን ሁሉ ስናገናዝብ ጦርነቱ የሕዝብን ጥቅም የሚያስከብር ሳይሆን አምባገነኖች ለሥልጣናቸው መራዘም የሚገለገሉበት መሣሪያ ሆኖ እናገኘዋለን።

ሕዝብ በሰላምና በመቀራረብ፣ ሊኖር የሚችለው ጦር ሰባቂ የሆኑ አምባገነን ሃይሎችና መንግሥታት ሲወገዱና በዴሞክራሲ ስርዓት ሲተኩ ብቻ ነው። ለዚያ ደግሞ በአምባገነኖች የሚጎሸመውን የጦርነት ነጋሪትና አዋጅ ሳይቀበሉ ተባብረው የጋራ ጠላታቸው የሆኑትን የአምባገነን ስርዓቶች ለማሶገድ ሲነሱ ነው።የሻእቢያን ስርዓት የሚቃወሙም ሆነ የህወሃት/ኢሕአዴግን የሚቃወሙ ማወቅ የሚገባቸው አንዱን አምባገነን ተጠግቶ ሌላውን አምባገነን ማሶገድ እንደማይቻል ነው። የሚታገሉት ለዴሞክራሲ ስርዓት ከሆነ እነዚህ በስልጣን ላይ ያሉት አምባገነኖች ጠላቶቻቸው ናቸው። የትም ይሁን የትም አምባገነን አምባገነን ነው፡፤ ለዲሞክራሲ የቆመ ሃይል ከሁለት አንዱን አይመርጥም። “ከጅንጀሮ ቆንጆ ምን ይመራርጧል” ነው። ጅንጀሮ ጅንጀሮ ነው አምባገነንም አምባገነን!!

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) አሁን በኤርትራና በቀረው ኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የተቀመጡት ሁለት አምባገነን ቡድኖች የቀውስና የጦርነት ተጠያቂዎች እንደሆኑ ያምናል፡፤ሕዝብ እነዚህ ጦረኛ፣ አምባገነንና ዘራፊ ቡድኖች ለዘረጉት የዕድሜ አርዝም የጦርነት ጥሪ ጆሮውን እንዳይሰጥ፣ ደሙን እንዳያፈስ እያሳሰበ ብሎም ሃይሉን አስተባብሮ እነዚህን አምባገነኖች ለማሶገድና በሰላም ለመኖር የሚችልበትን መንገድ እንዲፈጥር ተባብሮ እንዲነሳ ጥሪ ያደርጋል። ሻእቢያና ህወሃት መራሹ ኢሕአዴግ በሥልጣን ላይ እስካሉ ድረስ የኢትዮጵያና የኤርትራ ኑዋሪ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የከባቢው ሕዝብ በሰላም አይኖርም።

በጦርነት ሰበብ አድርጎ ድርድር በመክፈት የአገርን ጥቅምና መሬት አሳልፎ ለመስጠት የሚደረገውን የብልጦች አስመሳይ እሩጫና ዝግጅት ሁሉም ሊያውቀውና ሊታገለው ይገባል። በኢትዮጵያዊነታቸው የሚያምኑ፣ ለአገራቸው ጥቅም እንቆማለን የሚሉ የገዝው ቡድን ደጋፊወች ጭምር ከሌላው አገር ወዳድ ጋር ተባብረው በስማቸው የሚፈጸመውን ክህደትና አገር ጎጂ ተግባር ሊቃወሙት ይገባል። ያለፈው ይብቃ !ብለው መነሳት ይጠበቅባቸዋል።

በውጭ የሚኖረውም ዜጋ ጦርነቱን እንዲያወግዝና ሁለቱም አምባገነን ስርዓቶች እንዲወገዱ በጋራ እንዲታገል ጥሪያችንን አሁንም እናቀርባለን።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ)
Ethiopian People’s Congress for United Struggle (Shengo)
www.ethioshengo.org
shengo.derbiaber@gmail.com
Tel: 44 7937600756
+1 9168486790
E-mail : shengo.derbiaber@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule