• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“[እምቢ ካሉ] አጠቃላይ የትምህርት ሥርዓቱን የሚያሽመደምድ ስልት አለን”

June 4, 2016 04:32 am by Editor 4 Comments

ህወሃት ኦህዴድን ለማጽዳት በሚል ከ800 የሚበልጡ ሃላፊዎችን በየእርከኑ ቢያሰናብትም ለውጥ የሚታይ አልሆነም። ይልቁኑም የተጠኑ በሚመስሉ ማህበራዊ ጉዳዮች መናጡ እየተባባሰ ነው። አቶ ጃዋር መሐመድ ኢህአዴግ የቀረበለትን “የምክር ሃሳብ” የሚሰማ ካልሆነ አጠቃላይ የትምህርት ስርዓቱን የሚያሽመደምድ ስልት አለን ማለታቸው “እንዴት” የሚል ጥያቄ ቢያስነሳም ጆሮ ያገኘ ወሬ ሆኗል። ይህንኑ ተከትሎ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ጉዳዩን ከተወዳጁ ደራሲ በአሉ ግርማ ትንቢታዊ ድርሰት ጋር በማያያዝ “የኢህአዴግ ኦሮማይ እየተቃረበ ነው” ሲሉ በድፍረት ተናግረዋል።

በትላንትናው እለት የቪኦኤ አማርኛ ክፍለ ጊዜ ካቀረበው ቃለ ምልልስና ካጠቃላይ እውነታዎች ለመረዳት እንደተቻለው ኦሮሚያ ውስጥ የተጀመረው “ሰላማዊ” ትግል እየበሰለ የሄደ ይመስላል። ቀደም ሲል በተደረጉ የድርጅትና የውስጥ ግንኙነቶች የኦሮሞዎች ትግል አንድ ደረጃ ከፍ ሊል ያልቻለው “ኦሮሚያን የሚያስቀድም ሚዲያ ባለመኖሩ ነው” ከሚል ድምዳሜ ተደርሶ ነበር። በዚህ ውሳኔ መነሻ ይሁን በሌላ አቶ ጃዋር መሐመድ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ የተሰኘውን ሚዲያ በሃላፊነት በመምራት ይፋ ወጡ።jawar m

አቶ ጃዋር የሚመሩት ይህ ሚዲያ ለስድስት ወራት ያህል በኦሮሚያ ሲካሄድ የነበረውንና አሁን ድረስ እሳቱ ያልተዳፈነውን ተቃውሞ ዝርዝር ጉዳዮችን በማቅረብ፣ ትኩስ ምስሎችንና ቪዲዮዎችን በማሰራጨት ግንባር ቀደም ሆኖ ታይቷል። ኦሮሚያ ላይ ሲካሄዱ የቆዩትን ተቃውሞዎች በማስተባበር ግንባር እንደሆኑ በመግለጽ ፊት መስመር የወጡት አቶ ጃዋር፣ “ጽንፈኛ፤ አክራሪ” በሚል የሰላ ተቃውሞ ቢሰነዘርባቸውም የዚያኑ ያህል ደጋፊና ተከታይ ስለማፍራታቸው ብዙም ክርክር የማያስነሳ ሃቅ ሆኗል።

በኦሮሚያ ፖለቲካው ግልጽ ያለ አቋማቸው ምን እንደሆነ በውል የማይታወቀው አቶ ጃዋር በሁሉም የኦሮሚያ ዞኖች ያላቸው ተቀባይነት እንዲሁም ኦሮሚያን መሰረት ካደረጉ ፖለቲከኞች ጋር አሁን የደረሱበት የግንኙነት ደረጃም የጠራ አይመስልም። ለዚህ ይመስላል አካሄዳቸውን በጥንቃቄ የሚመለከቱ የሚበረክቱት። ከዚህም በላይ የ“ሜንጫ” ስም ጠርተው የተናገሩት ዛቻ አዘል ንግግር ደግሞ በተዛተባቸው፣ የጎሳንና የቂም ፖለቲካን በሚጠየፉ ወገኖች ዘንድ የሚጠሉ አድርጓቸዋል።

ምንም ይሁን ምን ግን ኦሮሚያ ላይ ከወትሮው በተለየ የጋለና ረጅም ጊዜ የቆየ አመጽ መቀጣጠሉን ተከትሎ የተከሉት ስም ጃዋርን አጉልቶ አውጥቷቸዋል። አሁን ደግሞ የኦሮሚያን ተማሪዎች የወደፊት ህይወት ለመታደግ በሚል የተወሰደውን ብሔራዊ ፈተናን አስቀድሞ ይፋ የማድረግ ዘመቻ የመሩት እሳቸው መሆናቸውን በማስታወቅ ሃላፊነት መውሰዳቸው ጃዋርን ለጉዳዩ ፊትአውራሪ አድርጓቸዋል። እሳቸው እንደሚሉት የጉዳዩ ባለቤት ሙሉ በሙሉ እሳቸውና የሳቸው ኔትዎርክ ከሆነ፣ ድርጊቱ የሌሎች የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎችን ሚና እንዳያቀጭጨውና ጥያቄ ውስጥ ሊከታቸው እንደሚችል “ተግባር ናፈቀን” የሚሉ ይጠቁማሉ።

ከሁሉም በላይ የትምህርት ሚኒስቴር የፈተናውን መሰረዝና፣ ፈተናው እንደገና የሚሰጥበትን ቀን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ አቶ ጃዋር “ምክረ ሃሳብ” ለኢህአዴግ ሃላፊዎችና ለትምህርት ሚኒስትሩ መላካቸውን ሲናገሩ “ከእንግዲህ እምቢ ብለው የሚቀጥሉ ከሆነ ለሚመጣው ማንኛውም ዓይነት ኪሳራ ተጠያቂ ይሆናሉ” በሚል ማሳሰቢያ ሰጡ። ቀጥለውም “የትምህርት ስርዓቱን ሙሉ በሙሉ የሚያሽመደምድ ታክቲክና ስትራቴጂ አለን። አሁን እዚያ ዝርዝር ውስጥ መግባት አልፈልግም” ሲሉ አስጠነቀቁ። ይህንን ብልት ጉዳይ በተከታይ ጥያቄዎች ከማጠናከር ይልቅ የተኛችበት የቪኦኤ ቃለምልልስ አድራጊ ቢያንስ ለወደፊት በዚህ ጉዳይ ላይ እንደምትመለስበት ፍንጭ ሳትሰጥ ራስዋን አዳማጭ አድርጋ አልፋዋለች።

oromo1አቶ ጃዋር በዚህ አላበቁም በትምህርት ተቋማት ውስጥ ያለውን ቁጥጥር ሙሉ በሙሉ ሽባ የማድርግ ስራ እንደሚሰሩም ነው የዛቱት። “እንዴት” የሚለው ጉዳይ አሁንም የበርካቶች ጥያቄ ቢሆንም “በጎ ምላሽ እንጠብቃለን፤ እኛ በእልህ የምናደርገው ነገር የለም” ሲሉ ውሳኔ ሰጪዎች ራሳቸውን ከእልህ እንዲያጸዱና ተጨማሪ ውድመት ከማስከተል እንዲታቀቡ ተለሳልሰው ጥሪ አድርገዋል።

ከቪኦኤ ጋር ቃለምልልስ ያደረጉት አቶ ጃዋር በተደጋጋሚ ከፈተና አዘጋጆች ወይም ከፈተናዎች ኤጀንሲ፣ ከዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ ከባለሙያዎች፣ ከትምህርት ቢሮ ሰዎች ጋር በመመካከር ሃሳቡን እንዳቀረቡ ጠቁመዋል። በጥቆማው መሰረት ተማሪዎች የሁለት ወር ተጨማሪ ጊዜ ቢሰጣቸው እንደሚበቃ የማሳመን ስራ ተሰርቷል። እናም ይህ እሳቸው በጥናት ተሰርቶ እንደቀረበ ያመለከቱት ምክረ ሃሳብ ተቀባይነት ካላገኘና ፈተናው ለሁለት ወር ካልተራዘመ ቀጣዩ ስትራቴጂ ተግባራዊ ይሆናል። ኢህአዴግ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በህዝብ አመጽ አዋጅ መሻር፣ መመሪያ መቀየር፣ ህግን መገደብ፣ ወዘተ እየቀናው ስለሆነ ውሳኔው በጉጉት የሚጠበቅ ሆኗል። ፈተናው የሚሰጥበት ቀን የኢድ በዓል ዋዜማን ማግስት መሆኑም ሌላው ትኩሳት መሆኑ ከዚሁ ጋር አብሮ የሚነሳ ጉዳይ ነው።

በኦሮሚያ በአማካይ አራት ወራት ትምህርት አለመሰጠቱ፣ መጠነኛ ሰላም አለባቸው በሚባሉት አካባቢዎች ተማሪዎችና መምህራኖች መታሰራቸውን፣ መምህራን የማስተማሪያ መጽሃፍትን ግማሽ ድረስ እንኳን አለማስተማራቸው፤ ተማሪዎች የጠየቁት የአራት ወር ጊዜ ቢሆንም፣ ጃዋር “ከእኛ ጋር የሚሰሩ” ያሏቸው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለእረፍት ሲመለሱ የማካካሻ ክፍል ትምህርት እንደሚሰጧቸው ከመግባባት ላይ ተደረሶ ሁለት ወር እንዲጨመር መስማማታቸውን በቃለ ምልልሱ ወቅት ተነግሯል። dagnachew a

እዚህ መሃል አዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ በፖለቲካ ውሳኔ ያባረራቸው ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ አስተያየት ሰጠተዋል። እየሳቁና መገረማቸውን እየገለጹ ነበር የተናገሩት። የተማረና ያልተማረ አንድ ማዕድ ላይ እንዲቀርቡ ማድርግ ፍትሃዊ እንዳልሆነ አመልክተው “…አንድ አስተማሪስ እንዴት ያላስተማረውን ይፈትናል?” ሳቁና “ያሰቃል እኮ” ሲሉ ግርምት አሳዩ። ከዚያም የማይሆን ውሳኔ ተላልፎ ሲያበቃ “ፈተና ጠፋ ተባለ” ሲሉ ጉዳዩን የፖለቲካው ነጽብራቅ እንደሆነ ጠቆሙ።

“የኃይለሥላሴ ኦሮማይ ነበር፤ የደርግ ኦሮማይ ነበር፤ አሁን ተራው የኢህአዴግ ኦሮማይ ነው” በማለት ጉዳዩ የፖለቲካ ጥያቄ ስለመሆኑ አሰመሩበት። “ኢህአዴግ ቅንጅት ነው” ካሉ በኋላ ቅንጅቱ በመሰነጣጠቅ ላይ መሆኑን የሚያሳይ የሂደት ነጸብራቅ እንደሆነ በማከል “የኢህአዴግ ኦሮማይ” ሲሉ የጠሩት ጊዜ ስለመቃረቡ አስረዱ። አክለውም “አንድ ፈተና እንኳን ተቀናጅተው መፈተን አልቻሉም። አንድ ስርዓት ተቀናጅቶ በቀድሞ መልኩ መሄድ ካልቀጠለ ኦሮማይ ነው” ብለዋል፡፡

የተዘጋጁ ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው የስነልቦና ችግር ሊያጋጥማቸው እንደሚችል በማመልከት ሁሉንም አቻችሎ ማስኬድ እንደሚገባ የጠቆሙት ዶ/ር ዳኛቸው “እኛ የተናገርነው አይቀርም የሚለው አባባል ትክክል አይደለም” በማለት ነገሮችን ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ማየት አስፈላጊ እንደሆነ መክረዋል።

አስተያየት ሰጪ ተማሪዎች የፈተናው ቀን እንዲራዘም መደረጉ እንዳስደሰታቸው ጠቁመው፣ አሁንምም በተመሳሳይ በቀረበው የምክር ሃሳብ መሰረት ተግባራዊ ሊሆን እንደሚገባ ለቪኦኤ ሲናገሩ ተሰምተዋል። በሌላ በኩል ለፈተናው ዝግጅት ያደረጉ ደግሞ ሁኔታው የፈጠረባቸውን ኪሣራ በሕይወታቸው ላይ መቼም ሊስተካከል የማይችል ጉዳት ማድረሱን ይናገራሉ፡፡ የእንዲህ ዓይነቶቹን ተማሪዎች ምሬት በማጉላት የህወሃት ቅጥረኞች ድርጅታቸውን በከፍተኛ የሞራል ማማ ላይ ሰቅለው የሥነምግባር ጥያቄ ሲያነሱ መደመጣቸውን ተከትለው አስተያየት ሰጪዎች “ለረሃብተኛ በተላከ ገንዘብ መሣሪያ የሚሸምተው ድልድይ አፍራሹ ህወሃት ምነው ሃውዜንን ረሳው” ብለዋል፡፡

ኦህዴድ ለማፈንገጡ ዋና ምልክት መሆኑ የተነገረለት ይህ ክስተት ማቆሚያው የት እንደሚሆን ባይታወቅም “ህዝብ ለምን ይገደላል በማለት የጠየቁ ተባረዋል። እነዚህ ወገኖች ጥፋት የለባቸውም። የህዝብ ወገኖች ናቸው” በማለት ኦፌኮ የተባረሩትን የኦህዴድ አባላት ማወደሱ አይዘነጋም። OFC_Merera_Bekeleበተመሳሳይ ህወሃትን ከህዝባቸው በላይ በማስቀደም የሚያገለግሉትን መንቀፉ ይታወሳል።

ቀደም ሲል 23 የአስረኛ ክፍልና 12 የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የፈተና ጊዜ እንዲራዘም ሲወሰን ድርጊቱን የተቃወሙ እንደነበሩ ተሰምቷዋል። ሙሉ በሙሉ በአገር አቀፍ ደረጃ ፈተናው ሊቋረጥ እንደሚገባ አቋም የያዙ ክፍሎች “ዝም በሉ” እንደተባሉ መረጃዎች ያመለክታሉ።

በሌላ በኩል በድጋሚ የሚሰጠው ፈተና በልዩ ግብረሃይል ጥበቃ እንደሚከናወን ሪፖርተር ባለስልጣኖችን ጠቅሶ ረቡዕ እለት ዜና ሲያስነብብ “ልዩ ግብረኃይል” የማስፈተኑን ተግባር ተማሪዎችን በሜካናይዝድ ብርጌድ በማጀብ ወይም ብረት በማስለበስ ወይም የትምህርት ተቋማትን opdoበታንክ በማጠር እንደሚከውነው ያለው ነገር የለም። ሪፖርተር አቅለስልሶ ወሬ ያደረገው ይህ ዜና ሌሎች እያቀረቡ ስላለው የተጨማሪ ጊዜም የሰጠው ሃተታ የለም። ጉዳዩን ፖለቲካ ነው የሚሉ ወገኖች “ወደ አንድ ሺህ የሚጠጉ የኦህዴድ ሰዎች ከተባረሩ በኋላ ህወሃት አሁንም ኦህዴድ ውስጥ ያለውን መዋቅር ካላመነ ፈተናው ሊከናወን አይችልም የሚል ስጋት አለን፤ 25 ዓመት ሙሉ ሁሉንም ነገር በራሱ መነጽር ሲይይ የኖረው ህወሃት ቢያንስ አሁን እንኳን ቆም ብሎ ቢያስብ ይሻለዋል” ብለዋል።

“ሁሉን ትወዳለህ፣ በመጨረሻም ሁሉን ታጣለህ! ሴላቪ ኦሮማይ!”?


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    June 5, 2016 09:20 pm at 9:20 pm

    Foolish game !

    I believe EPRDF should mercilessly eradicate these human wastes when ever , wherever !

    Reply
    • Mario says

      June 9, 2016 06:13 pm at 6:13 pm

      @gud

      You wrote, “I believe EPRDF should mercilessly eradicate these human wastes when ever , wherever!”. Are you alright?

      That sounds like Nazi’s declaration to wipe out Jews and other unwanted peoples of Europe. Even if you are woyane or woyane-lover, you have no single reason to be that bitter like Hitler and his likes and advice EPDRF and its followers to “mercilessly eradicate” Oromos and other ethnic groups you hate to death. As a human being, your stupidity has no limit like the outer space.

      Stay calm and be cool-headed. You will never know what fate has in store for you.

      Reply
    • rasdejen says

      June 10, 2016 01:21 pm at 1:21 pm

      gud,

      Humans are higher creations. But gangs such as TPLF are wastes as you described it. Thus, we have to eradicate these wastes including you.

      Reply
  2. Rasdejen says

    June 9, 2016 09:20 pm at 9:20 pm

    Stop blaming Holy TPLF and enjoy watching these:

    1. https://www.youtube.com/watch?v=-pn6w5vvMO8

    2. https://www.youtube.com/watch?v=O-QmWORxnKQ

    3. https://www.youtube.com/watch?v=MxIZAjxMhHQ

    4. https://www.youtube.com/watch?v=e7wqbM4y_6M

    5. https://www.youtube.com/watch?v=je23QNfN8tA

    6. https://www.youtube.com/watch?v=miMBghOvrvo

    7. https://www.youtube.com/watch?v=czT4OtG48S8

    8. https://www.youtube.com/watch?v=czT4OtG48S8

    9. https://www.youtube.com/watch?v=0F93U9BQIfI

    10. https://www.youtube.com/watch?v=v0qSVRT17Xk

    11. https://www.youtube.com/watch?v=6S72PX8JxAQ

    12. https://www.youtube.com/watch?v=jZ0T9y6pumk

    13. https://www.youtube.com/watch?v=aCk-rMSr6ro

    14. https://www.youtube.com/watch?v=8kcJyCxylCM

    15. https://www.youtube.com/watch?v=9WNI6p-ue-A

    16. https://www.youtube.com/watch?v=0ZZRp5EMt1I

    17. https://www.youtube.com/watch?v=OfGVBh7-w6c

    18. https://www.youtube.com/watch?v=LVKCwedFU3w

    19. https://www.youtube.com/watch?v=7MtwMUTWzos

    20. https://www.youtube.com/watch?v=flsLGLkRgXY

    21. https://www.youtube.com/watch?v=dkdkZWKPJRI&list=PLEGZNjdn0MM658xCi5V4qFTmAswCEfxMx

    22. https://www.youtube.com/watch?v=n6t7dDhSPhI&list=PLjc6iyLtkLuT_HAqLAmyl4yfDS4KNVGHV

    23. https://www.youtube.com/watch?v=OuW4rzqLWOY

    24. https://www.youtube.com/watch?v=f90xVlV44cw

    25.https://www.youtube.com/watch?v=ZWhW34r0rNg

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule