• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት በኦሮሚያ ላፈሰሰው ደም 2.4 ቢሊዮን ብር ጉቦ ሰጠ

April 18, 2016 09:19 am by Editor 5 Comments

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ህወሃት) በኦሮሚያ ክልል የተነሳውን ሰላማዊ ተቃውሞ ተከትሎ ላፈሰሰው ደም 2.4 ቢሊዮን ብር ጉቦ በኦህዴድ አማካይነት መስጠቱ ይፋ ሆነ። ገንዘቡ የኦሮሚያ ሥራ አጥ ወጣቶችን ባለሃብት እንደሚያደርግ ሲገለጽ፣ ስራ አጥቶ ግብርና የተመለሰው ኢንጂነር በዳዳ ጋልቻ በህወሃት አንጋቾች የእርሻ ስራውን ጨርሶ ሲመለስ በጥይት ተደብድቦ ተገድሏል።

በዳዳ ገልቻ ማን ነው? ምን ደረሰበት?

በዳዳ እስከ አለፈው ማክሰኞ ድረስ ጉጂ ዞን፣ አዶ ሻኪሶ ወረዳ፣ መጋደር መንደር ነዋሪ ነበር። በምህንድስና ትምህርት ከዩኒቨርስቲ ተመርቆ ስራ ማግኘት ተሳነው። ስራ ፈለጋ ሲታከተው ትውልድ መንደሩ ተመለሶ በራሱ ስራ ፈጥሮ ለመስራት ጥያቄ አቀረበ። ያካባቢው አስተዳደር ጥያቄውን በውል ባልተገለጸ ምክንያት ውድቅ አደረገበት። ዲግሪውንና የስራ እቀዱን ወደ ጎን ትቶ ሙሉ በሙሉ ግብርና ላይ ተሰማራ።

ባለፈው ማክሰኞ ማሳው ላይ ደቦ ነበረው። ለደቦ ከጠራቸው ጋር ሆኖ ሲሰራ ዋለ። ደቦው ተጠናቆ ከማሳው ሲወጡ አወል የተባለ ሰው ወዴት እንደሚሄድ ጠየቀው። እሱም ወደቤት እንደሚሄድ ነገረው። ከዚያም ይህ ሰው ብርሃኑ ከሚባል ደህንነት ጋር ሆኖ መንገድ ላይ ጠበቁት። አጋዚዎችም አብረው ነበሩ። ከበዳዳ ጋር የነበሩት ሰዎች ሲደናገጡ “እናንተን አንነካም። የምንፈልገው ሰው አለ” በማለት በዳዳን “ቁም” አሉትና በጥይት ደበደቡት። ያካባቢው ህብረተሰብ ተኩስ ስምቶ ተሰበሰበ። ደጋገመው በመተኮስ የተሰበሰበውን ህዝብ አጋዚዎች በተኑት። ከዚያም ታርጋ በሌለው መኪና ጭነው አዶላ ሆዬ ሆስፒታል ወሰዱት።

ሆሰፒታል ከደረሰ በኋላ በዚያው ቀን ከምሽቱ 2፡30 አካባቢ ህይወቱ አለፈ። በዳዳ ኢህአዴግ 100 እጅ አሸነፍኩ ባለበት ምርጫ ኦፌኮን የወከለ እጩ ተወዳዳሪ ነበር። እሱ በተገደለበት ቀን ተቃውሞ አልነበረም። ከወር በፊት የሼኽ መሐመድ ሁሴን አልሙዲ የአኮቴ የወርቅ ፕሮጀክትንና የማስተር ፕላኑን በመቃወም ተካሂዶ የነበረውን ሰልፍ አስተባብሯል በሚል ግን ይጠረጠር ነበር። ቪኦኤ ዳንኤል ቦሩ እና ጋሪ ሱኔ የተባሉ የአይን ምስክሮችን ጠቀሶ አርብ ምሽት ካቀረበው የተወሰደ።

“የተቃውሞው ዋና መንስኤ ስራ አጥነት ነው” ኦህዴድ

የበዳዳን መገደል በጉያው አድርጎ የኦሮሚያን ሥራአጥ ወጣቶች ባለሃብት የሚያደርግ አስቸኳይ ፕሮጀክት መነደፉን ይፋ ያደረገው ኦህዴድ ፕሮጀከቱ በሁለት ሳምንት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል ብሏል። ሪፖርተር የጠቀሳቸው የክልሉ የኮሙኒኬሽን ጉዳይ ጽህፈት ቤት ሃላፊ 832 ሺህ ስራ አጦች “የዕድሉ ተጠቃሚ” ይሆናሉ ብለዋል።

ሰላማዊ ጥያቄ በማንሳታቸው በህወሃት ታጣቂዎች ወንድምና እህቶቻቸው የተሰዉባቸው ሥራአጥ የኦሮሚያ ወጣቶች ንጹህ ውሃ ማምረት ይጀምራሉ። የምግብ ማዘጋጃ ፋብሪካ ባለቤት ይሆናሉ። ማዕድን ማምረት ይጀምራሉ። ሪፖርተር እንዳለው ሥራአጥ የነበሩት የኦሮሚያ ወጣቶች “ባለሃብቶች” ይሆናሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው ከህዝብ ጋር በተደረገ ውይይት ዋና ቁልፍ ችግር ሥራአጥነት መሆኑ በመታወቁ ነው።

ህወሃት ለኦህዴድ ጉቦ?

የኦሮሚያን ሥራአጥ ወጣቶች ባለሃብት የማድረግ ፕሮጀክት ይፋ መደረጉን አስመልክቶ የጎልጉል የአዲስ አበባ መረጃ አቀባይ ወሊሶ፣ ነቀምት፣ አዳማ፣ አለለቱና አርሲ ኮፈሌ የሚገኙ ነዋሪዎችን ትዝብት የማግኘት እድሉ አጋጥሞት እንደነበር ያወሳል። ከ800 በላይ የተለያዩ አመራሮችን ከሃላፊነት ዝቅ ያደረገውና ያሰናበተው ኦህዴድ አሁን ያስቀራቸው ሃይሎች ለህወሃት ታማኝ የሆኑት ብቻ መሆናቸው በስፋት እንደሚነገር ይገልጻል።

አሁን ከህወሃት ጋር የሚቀጥለው የኦህዴድ ታማኝ ክፍል የህዝብ፣ በተለይም የወጣቱን ታማኝነት ለማግኘት ይችል ዘንድ ትግራይ ውስጥ በከፊል ተግባራዊ ተደርጎ የኖረውን አሠራር ተግባራዊ እንዲያደርግ ተፈቅዶለታል። ህወሃት በክልሉ ሃብታም ያደረጋቸው ታማኝ ወዳጆቹ እንደሚንከባከቡት ሁሉ ኦህዴድም እንደአቅሚቲ ባለሃብት ወጣቶችን እንዲያፈራ ተመከሯል። 2.4 ቢሊዮን ብርም ተመድቦለታል። ፕሮጀከቱ ለቀጣዩ ምርጫ ሩጫም ጭምር እንደሆነም ይተቻል።

የ2.4 ቢሊዮን ፕሮጀክት ይፋ መሆኑን ተከትሎ “ህወሃት ለኦህዴድ የሰጠው ጉቦ ነው። የህወሃት ታጣቂዎች ላፈሰሱት ደም የተሰጠ ጉቦ ነው። በቀጣይ በወገኖቻቸው ደምና አጥንት ላይ ቆመው ብር የሚቆጥሩ ዜጎችን እናይ ይሆን?…” የሚሉ የመረሩ ተቃውሞዎች ይሰማሉ።

“ከሃጂዎችና ሆዳሞች፣ ከሃጂና ሆዳም ትውልድን ነው የሚፈጠሩት። ህወሃትን ክህደት እንደወለደው ሁሉ ከሃጂዎችን ስብስቦ እዚህ ደረሰ። አሁን ያለው ትውልድ ግንዛቤው በማደጉ ከበላው ማካፈል ግድ ሆነበት። 2.4 ቢሊዮን ብር ፈቅዶ የማካፈል ፖለቲካን ሊጀምር ወሰነ። ይህ ኢምንት ገንዘብ በኦሮሚያ ከፈሰሰው ደምና ከተፈጸመው ግፍ በላይ ገዝፎ የዜና ሚዛን ማግኘቱ ያሳዝናል። አንድ አገር የምትቆመውና ሰላሟ የሚጠበቀው ፍትህ ሲሰፍንባት ብቻ ነው። የሰው ልጆች የማይደበቁት ህሊና አላቸው” ሲሉ ከኦህዴድ አስቀድመው የተሰናበቱ አስተያየት ሰጠተዋል። ኦህዴድ የክህደት መንገዱን እስካላቆመና ኦሮሚያን አስቀድሞ እስካልሰራ ድረስ ችግሩ ሁሌም አለ። አቶ ሃይለማርያም ህዝብ ነቀቷል፤ ካሁን በኋላ በዚህ ህዝብ ጫንቃ ላይ ሆኖ እንዳሻው መጋለብ አይቻልም ሲሉ የተናገሩት ጉዳዩ በውል ገብቷቸው ከሆነ ትክክል የሚሆኑት ራሳቸውንና ሌሎችን ነጻ ባለስልጣን ሲያደርጉ ብቻ ነው – እንደ ኦህዴዱ ሰው!!


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    April 18, 2016 03:24 pm at 3:24 pm

    Denez. Hula

    R u angry that youth r being employeed
    Your desire for chaos was shattered !

    Reply
  2. Negash says

    April 25, 2016 01:54 pm at 1:54 pm

    Excellent headline and article.

    Reply
  3. tajura lamibebo says

    May 2, 2016 03:19 pm at 3:19 pm

    try to do more god bless you. we are still under the yoke of #agame. so we have free and independent

    Reply
  4. Rasdejen says

    June 10, 2016 09:57 pm at 9:57 pm

    ህወሃት ደም? No, watch this: https://www.youtube.com/watch?v=ZWhW34r0rNg

    Reply
  5. yesanjaw says

    August 18, 2016 11:10 pm at 11:10 pm

    Hi

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule