• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቅኝ ተገዥነቱን ያወቀ ሕዝብ በከፊል ነፃ ነው!

August 12, 2016 03:26 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሬ ወያኔ ቅኝ ተገዥ ከሆነ ድፍን 25 ዓመት ሆነው። በእነዚህ ረጅም ዓመታት፣ የተማሩትም ሆነ ያልተማሩት ዜጎች፣ በቅኝ ተገዥነት መያዛቸውን ያወቁትም ሆነ ለማወቅ የጣሩት በጣም ጥቂቶች ናቸው። እነዚህ በቅኝ ተገዥነት ተይዘናል ያሉት የጥቂቶቹ ድምፅ፣ በብዙኃኑ፣ ከሁሉም በላይ በጎሣ ፖለቲከኞቹ ድምፅ ተውጦ፣ ወያኔ፣ ያላንዳች ሀግ ባይ፣ ሩብ ምዕተ ዓመታት  የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት በእጅጉ የጎዱ ሥራዎችን እንዲሠራ ሠፊ ዕድል ሰጠው። በመሆኑም የኢትዮጵያዊነት አያያዥ ማገርና ወራጅ፣ መሠረትና ጭምጭም የነበሩትን፣ የኢትዮጵያዊነት ዕሴቶቻችን ከሥራቸው ነቀላቸው። ሕዝቡን በነገድ ከፋፍሎ እሣትና ጭድ አደረጋቸው። የኢትዮጵያ ነገዶች ሙጫ በመሆን ከሌሎች ነገዶችና ጎሣዎች ጋር ሰምና ፈትል ሆኖ፣ ኢትዮጵያዊነትን ሲገነባ የኖረውን የዐማራ ነገድ፣ በዘር ጠላትነት ፈርጆ፣ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ፈጸመበት። አምስት ሚሊዮን ዐማራ ከምድረ ኢትዮጵያ እንዲጠፋ ተደረገ። በወለጋ፣ በኢሉባቡር፣ በከፋ፣ በሐረርጌ፣ በጎጃምና በጎንደር ይኖሩ የነበሩትን ዐማሮች በግፍ ሀብት ንብረታቸውን ነጥቀው ለርሃብ፣ ለድህነትና ለአገር አልባነት አሳልፎ ሰጣቸው። ይህ ዓለም በዝምታ እየተመለከተው ያለው የዘር ጥቃት፣ ዛሬ የጥቃቱ ሰለባ የሆኑት ዐማሮች የቅኝ አገዛዙን ሰንሰለት በጣጥሰው፣ ፍፁም ነፃ የሆነ ዐማራዊ ማንነታቸውን አረጋግጠው፣ የኢትዮጵያን ትንሣዔ ለማብሰር ከአፋኙ የወያኔ የስለላና የአፈና መዋቅር ኃይል ጋር የሞት ሽረት ትግል እያደረጉ ይገኛሉ።

የዐማራው ነገድ ዛሬ በትግሬ ወያኔ ቅኝ ተገዥ መሆኑን ከማወቅ አልፎ፣ ለነፃነቱ ቆርጦ የሕይዎት መስዋዕትነት እየከፈለ ነው። በዚህ የሞት ሽረት ትግል ውስጥ፣ እስካሁን በጎንደር ከተማ፣ አዘዞ፣ ቆላድባ፣ አርማጭሆ፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ወልቃይት፣ ጋይንት፣ ደብረታቦር፣ ባሕር ዳር ወዘተርፈ ቁጥራቸው ገና በውል ያላወቅናቸው አያሌ ወንድምና እህቶቻችን ባልሞ ተኳሾች የጥይት አረር ወድቀዋል። በርካቶቹ በወያኔ እስር ቤቶች የመከራን ጽዋ እየተቀበሉ ነው። ዐማራውን ለዚህ ግፍ ያበቁት በወያኔ የመከላከያ፣ የፖሊስና የፀጥታ ሠራቶች የተቀጠሩ ብቻ ሳይሆኑ፣ ከሕዝቡ ጋር የሚኖሩት በየኮንዶሚኒየሙ በሰፈራነት የተሰገሰጉት ትግሬዎች መሆናቸውን ስንገነዘብ፣ «ለካ እስከ ዛሬ በጉርብትናም ሆነ በጋብቻ ከእነዚህ ሰዎች ጋር የፈጠርነው ግንኙነት፣ እኛን ለማጥቂያ ውስጣችንን ገልጠው እንዲያዩን ሁኔታዎችን ያመቻቸ ነው፤» ብለን እንድናስብ አስገድደውናል።

ባሕር ዳር እና ጎንደር በጥይት ለተቀጠፉት ሰዎች ገዳዮቹና አስገዳዮቹ በከተሞቹ ነዋሪ የሆኑት የወያኔ የውስጥ አርበኛ ትግሬዎች መሆናቸውን በተጨባጭ አረጋግጠናል። ይህም «ወያኔን እና ትግሬን ለዩ» ለሚሉ የዋሕ ፖለቲከኞችና የሰብአዊ መብት ጠበቆች ነን ለሚሉ ሁሉ የሚያራምዱት ሀሳብ መሠረት የሌለው መሆኑን አሳይቷል። ሕዝብን በሙሉ የክፋት ሥራ ተጠያቂ ማድረግ ተገቢ አይደለም የሚባለው፣ ሕዝቡ የጥፋት ተባባሪ አይደለም ከሚል መነሻ ሳይሆን፣ ሕዝብን በሕዝብነቱ መወንጀልም ሆነ ለጥፋቱ ተጠያቂ ማድረግ ለችግሮቹ ዘላቂ መፍትሔ አያስገኝም ከሚል መነሻ እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል። ዛሬ የትግራይ ሕዝብ በወያኔ አገዛዝ ተጠቃሚ መሆኑ ጥያቄ ውስጥ የሚገባ አይደለም። ሌላውን ቁሣዊና ለወዲፊቷ ትግራይ ልማትና ዕድገት የተሠሩትን መጠነ ሠፊ ሥራዎች ትተን፣ በአገዛዙ ባለሥልጣኖች እንደ ዐማራውና ኦሮሞው አይጠረጠሩም፣ አይፈተሹም፣ በሥራቸው የመረጃ ታኮ አይለጠፍባቸውም፣ የመሥራትና የመንቀሳቀስ መብታቸው የተገደበ አይደለም፤ የፈለጉትን  ሠርተውና ተናግረው በሰላም ተኝተው ያድራሉ። ይህ ጥቅም አይደለም የሚል ካለ፣ ይህን መብት ያጡት የዐማራ ልጆች ጥቅሙ ከቁሣዊ አልፎ የኅልውና እና የነፃነት ዋጋ ያለው መሆኑን እየከፈሉት ባለው የደምና የሕይዎት ዋጋ ሊማር ይገባዋል።

ከሁሉም በላይ፣ የትግራይ ሕዝብ፣ ልጆቹ የሁሉም ነገር አድራጊና ፈጣሪዎች መሆናቸውን ስለሚያውቅ፣ በልጆቹ ድርጊት ይመካል። ከመመካትም አልፎ እየኮራ ሌሎችን ሲያዋርድ እያየን ነው። ይህም ለአጉል ትዕቢት ዳርጎት ሌሎችን «ሽንታም፣ ፈሪ» በማለት  በየምርመራ ጣቢያውና በየፓልቶክ ክፍሉ የምንሰማው የዕለት ተዕለት ስድባቸው ነው። ይህ ድርጊት የሌሎችን ነገድ ልጆች አዕምሮ አያነቁርም፣ ደም አያፈላም፣ አያስቆጭም የሚል ካለ «ግሞ ሲሉህ፣ ጥንቦ በለው» ተብሎ ያላደገ የማንነት መገለጫ ዕሴት የሌለው፣ የተዋራጅ ሕዝብ ባህል ብቻ ነው። በመሆኑ፣ ከ25 ዓመታት ትዕግሥትና የአብሮነት ፍላጎት በመነጨ፣ ዐማራው ወያኔ የጣለበትን ዕዳ፣ ያሸከመውን የመከራ ቀንበር ተሸክሞ መቆየቱ ግልጽ ነው።

የዐማራው ሕዝብ ዛሬ ግን ከመከራ አልፎ፣ ማንነቱን በመነጠቁ «አሻፈረኝ፣ መከራው በዛብኝ፣ ሸክሙ ከምችለው በላይ ሆነብኝ፣ ግፉ ከአናት በላይ ወጣ፣» ብሎ ማንነቱን ለማስከበርና ነፃነቱን ሙሉ በሙሉ ለማስመለስ ከአፋኙ የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ሠራዊት ፊት ለፊት በባዶ እጁ እየተጋፈጠ ይገኛል። ይህም ዐማራው በቅኝ ቅዛት መያዙን ከማወቅ አልፎ፣ ለነፃነቱ ቁርጠኛ ውሣኔ ላይ የደረሰ መሆኑን ያሳያል። ካልቆረጡ ከግብ አይደረስምና! በዚህ ረገድ የቁርጠኝነቱን ጉዞ፤ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በከፈተው የጀግንነት ድርጊት፣ ለዐማራው ወጣት አርአያነቱን አሳይቷል። ዐማራው ማንነቱን አስጠብቆ የኢትዮጵያ ትንሣዔ አብሳሪ የሚሆነውም በዚህ መንገድ ብቻ መሆኑን የትግሬ-ወያኔ ባሕሪ አስተምሮናል። ስለዚህ ትግሉ፣ መስዋዕትነትን ቀንሶ፣ ባጭር ጊዜ ውስጥ የድሉ ባለቤት የሚሆንበትን መንገድ መከተል ብልኅነት ብቻ ሳይሆን፣ አዋቂነትም ነው።

ለዚህም የሚረዳው፣ በየቀበሌውና ወረዳው የጎበዝ አለቆችን በመምረጥ የተደራጁ ቡድኖችን መፍጠር ሲቻለው ነው። በየደረጃው የተመረጡ የጎበዝ አለቆች በተመሳሳይ መልክ ከሚደራጁ አቻዎቻቸው ጋር ተያያዥና ተጋጋዥ የሆኑ ሥራዎችን ለመሥራት ሁኔታዎች በፈቀዱት መጠን የግንኙነት ሰንሰለት መፍጠር እጅግ አስፈላጊና ጠቃሚም ነው። ይህ ግንኙነት በአስተማማኝ ሁኔታ ከተመሠረተ በኋላ፣ የወያኔን የስለላና የአፈና መዋቅር ኃይል ለማሳሳት፣ የገንዘብ አቅሙን ለማዳከም፣ በተለያዩ ቦታዎች የሕዝባዊ እንቢተኝነቱ እንቅስቃሴን፥ ሰልፍና የመሳሰሉን፣ ማካሄድ። ለትግሬ-ወያኔ አፋኝ ኃይል፣ የኃይል ምንጭ፣ የሥንቅና የትጥቅ አቅርቦት ክምችት ያለባቸውን ቦታዎች በማጥናት ድንገተኛ ወረራ በማድረግ የሕዝብ ማድረግ የግድ ይላል። ይህ ሁሉ ሲሆን፣ አመራሩ ከውስጥ ከሕዝቡ መሀል ያሉ፣ የንቅናቄው ተሳታፊዎች አምነው የመረጧቸውን እንጂ፣ ከርቀት «መንፈስ ነን» የሚሉ የአየር በአየር የፖለቲካ ሰዎች ነን ከሚሉት ጋር እንቅስቃሴው እንዳይያያዝ ጥንቃቄ መደረግ አለበት። «የአህያ ባል ከጅብ አያድንም» እና በዚህ ረገድ ብርቱ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ ነው። ወያኔ እንኳን ሰበብ አገኝቶ፣ ራሱ ወንጀል ፈብርኮ፣ ሰዎችን ማሰር መግደሉ ይታወቃልና፣ ከውጭ ሆነው የሚፎክሩ ድርጅቶች፣ ለሕዝቡ መመቻ፣ መረጃ እየሰጡ ናቸውና በወልቃይት ጠገዴ የማንነት ጥያቄ ባለቤቱ ዐማራው ራሱ እንጂ፣ ሌሎች አለመሆናቸውን በግልጽ ሊያውቁት ይገባል።

በመሆኑም የወልቃይት ጠገዴ የማንነት ጥያቄ የመላው ዐማራ ጥያቄ በመሆኑ፣ የጎንደር፣ የጎጃም፣ የወሎ፣ የሸዋ፣ የሐረርጌ፣ የአዲስ አበባ፣ የወለጋ፣ የአርሲ፣ የከፋ፣ የጋሞጎፋ፣ የሲዳሞ፣ የባሌ እንዲሁም በዓለም ላይ በስደት የሚኖረው ዐማራ የትግሉ አካል እንዲሆን፣ የንቅናቄው አስኳል የሆነው የወልቃይት ጠገዴ የማንነት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ የመሪነቱን ቦታ በመያዝ፣ ሕዝቡን መድረስ ይጠበቅበታል። ከሁሉም በላይ የእንቅስቃሴው ባለቤቶች «እኛ ነን፣ እኔ ነኝ» ለሚሉ ወገኖች አቅማቸውንና ቁርጣቸውን እንዲያውቁ፣ የንቅናቄውን ዕለታዊና ሳምንታዊ ዘገባዎች ለዓለም ማኅበረሰብ የሚሰማ፣ ሕዝቡ የሚፈልገውን ርዳታ ተቀብሎ በትግሉ ውስጥ ላሉት አመራሮች ማስረክብ የሚችል ታማኝ ግለሰብ ወይም ቡድን ካለ እርሱን፣ ከሌለ በፍጥነት ተሰይሞ፣ ሕዝቡ እንዲያውቀው ቢደረግ ውንዥንብሩን ያጠራዋል፤ የሰከነ ሥራም ለመሥራት ያስችላል ብለን እናምናለን።

ሌላው፣ ንቅናቄው ሊመራባቸው የሚገቡ ቋሚ መፈክሮች ያሹታል። መፍክሮቹን ማንም እንደፈለገ እንዳይለጥጣቸው ከወልቃይት ጠገዴና ከዐማራ ማንነት ጋር የተያያዙ፣ ይህንም ባጭሩ መልዕክት የሚያስተላልፉ ሊዘጋጁ ይገባል እንላለን። ይህ ሲሆን ጎንደር ላይ የተቀጣጠለው የዐማራ የማንነት ጥያቄ፣ ቅኝ ገዥውን ቡድን ድባቅ መትቶ፣ ዐማራው ማንነቱናና ኅልውናውን አስጠብቆ፣ የኢትዮጵያን ነፃነት ዕውን ለማድረግ የበኩሉን አስተዋፅዖ ያደርጋል ብለን እናምናለን። በዛሬዪቱ ኢትዮጵያ የዕውቀትም ሆነ የሀብት ባለቤቶች እነርሱ መሆናቸው ስለሚታወቅ፣ በዚህ ነፃነት ከማንም ይልቅ ተጠቃሚዎቹ ትግሬዎች ይሆናሉ። ስለዚህ በነገይቱ ኢትዮጵያ ትግሬዎች ያላቸውን ዕውቀትና ሀብት በሥራ ላይ አውለው በነፃነት ለመጠቀም፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከወያኔ ነፃ መውጣቱ ፍቱን አብነት ነው። ለዚህም ከጠፊው የወያኔ ቡድን ጋር ሳይሆን፣ ከዘላለማዊው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና ከታሪክ ጋር መቆም ይጠበቅባችኋል።

ወያኔ ለትግሬም ሆነ ለኢትዮጵያ አጥፊ እንጂ፣ አልሚ አይደለም። የትግራይ ተወላጆች፣ በጊዜአዊ ሥልጣንና ጥቅም ተገብዛችሁ ሊሆን ይችላል፤ ይህ ግን ዘላቂ አይደለም። ከዘላቂ ጥቅም፣ ክብር፣ ማንነትና ከሠፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር እንድትቆሙ ጥሪያችን እናቀርባለን።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

የዐማራነት ማንነት በትግላችን ያብባል!

ዐማራነት ነፃነትና ዕኩልነት ነው!                                        

ዐማራነት ፍትሕና ኢትዮጵያያዊነት፣ ጀግንነትና መስዋዕትነት ነው!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule