• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

«የእሣት ልጅ አመድ» የሆነው የዘመኑ ኢትዮጵያዊ ታሪካዊ ማንነቱን ያስከብር!

May 6, 2016 05:41 am by Editor Leave a Comment

ከዛሬ ሰማኒያ ዓመታት በፊት የነበሩት ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን እና እናቶቻችን፣ ከትግራይ እና ከኤርትራ ምድር በበቀሉ ባንዶች አጋዥነት በፋሽስት ጣሊያኖች ጦር ማይጨው ላይ ድል ሲመቱ «እሺ፣ አሜን፣ እንገዛለን» ብለው እጃቸውን አጣጥፈው አልተቀመጡም። ራሣቸው ፋሽስቶችም እንዳመኑት፥ በተለይ በሰሜን ሸዋ፣ በጎጃም፣ በጎንደር፣ በወሎ፣ በጉራጌ፣ በጅባት እና ሜጫ እንዲሁም በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች የነበሩት አርበኞች በመረጧቸው የጎበዝ አለቆቻቸው እየተመሩ፣ ለአምሥት ዓመታት የፋሽስት ጣሊያንን ጦር ከእነ ባንዳ ግሣንግሱ መውጫ መግቢያ አሣጥተውታል። ከዚያም ከየካቲት 1933 ዓም ጀምረው ጀግኖች አርበኞቻችን ባደረጉት የተቀነባበረ የጥቃት ዘመቻ ልክ የዛሬ 75 ዓመት ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓም በቀዳማዊ ኃይለሥላሤ መሪነት በድል አድራጊነት ዋና ከተማችንን አዲስ አበባን ለመቆጣጠር በቅተዋል። ሆኖም ዛሬ ላይ ሆነን ስናየው ያ ሁሉ መስዋዕትነት ያስገኘልንን ብሔራዊ ክብር እና ልዕልና እንዲህ አሽቀንጥረን እንድንጥል ያደረገንን ምክንያት ለመገንዘብ ትልቅ እንቆቅልሽ ይሆንብናል።

የአምሥቱ ዓመት የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ በአገራችን በኢትዮጵያ ላይ ታላቅ የትውልድ ስብራትን ፈጥሮ አልፏል። ብዙ ጀግኖች አርበኞቻችን መሥዋዕት ሆነውብናል። በተቃራኒው ደግሞ ለፋሽስት ጣሊያኖች በባንዳነት ያገለገሉ አያሌ ከሃዲዎች ተፈልፍለዋል። በመሆኑም ፋሽስት ጣሊያኖች በጀግኖች አርበኞቻችን ከፍተኛ ተጋድሎ ከኢትዮጵያ ምድር ተጠራርገው ቢወጡም፣ እነርሱን በባንዳነት ሲያገለግሉ የነበሩት የእናት ጡት ነካሾች ግን ተንሠራፍተው ለመኖር በቅተዋል። ለዚህም የረዳቸው በተለይ ቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ሥልጣናቸውን ለማደላደል ሲሉ በአገሪቱ የመንግሥት መዋቅር ውስጥ አብዛኞቹን የጣሊያን ሎሌ ባንዶች በመሾማቸው ነው። በሚያሣፍር ሁኔታ ንጉሠ-ነገሥቱ ይባስ ብለው አርበኞችን እያደኑ በእሥር፣ አልፎም በግድያ ቀጧቸው። የአርበኞችን ቤተሰቦች አጎሣቆሉ። በተቃራኒው የባንዶች ልጆች በምርጥ ምርጥ የውጭ አገር ትምህርት ቤቶች እና ዩኒቨርሲቲዎች እንዲማሩ አደረጉ። የተዘረጋውም ሥርዓተ-ትምህርት ተተኪውን ትውልድ ስለአገሩ እንዲያውቅ ሣይሆን የምዕራቡን ሥልጣኔ የበላይነት እንዲቀበል የሚሰብክ እንዲሆን ተደርጎ ተቀረጸ። የእነዚህ ድምር ውጤት አገሩን የማያውቅ፣ በኢትዮጵያዊ ማንነቱ የሚያፍር፣ ዐይቶት የማያውቀውን የውጭውን ዓለም የሚቀላውጥ መጢቃ ትውልድ ፈጠረ። ስለዚህ ዛሬ ላይ ሆነን ስናየው ጣሊያኖች በ1888 ዓም ዐድዋ ላይ ድል ሆነው ቢመለሱም፣ ከማይጨው ውጊያ በኋላ ግን የረዥም ጊዜ ዕቅዳቸውን እንዳሣኩ መገንዘብ ይቻላል።

ከፋሽስት ጣሊያን ወረራ በኋላ ዘመናዊ ትምህርት የቀመሰው ትውልድ፣ በወቅቱ እንደ ወረርሽኝ በመላው ዓለም በመሠራጨት ላይ የነበረው የኮሚኒስት ርዕዮተ-ዓለም ተከታይ ለመሆን ጣረ። «ያ ትውልድ» ለአገሩ ቀና ያሰበ መስሎት ጎትቶ ያመጣው ርዕዮተ-ዓለም ግን ከራሱ አልፎ የታላላቆቹን እና የታናናሾቹን ትውልዶች ቀርጥፈው የሚበሉ አምባገነን ሥርዓቶችን ፈጠረ። በዚህ ረገድ ወታደራዊው ደርግም ሆነ የትግሬ-ወያኔ ሥርዓቶች ምንጫቸው «የተማሪዎች እንቅስቃሴ» እየተባለ የሚጠራው ክስተት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። በእርግጥ በአገራችን ላይ የደረሰውን እና አሁንም በመድረስ ላይ ያለውን መዓት ሁሉንም በዚያ ትውልድ የተሣሣተ የፖለቲካ አቅጣጫ ብቻ ማሳበብ ባይቻልም፣ ግዙፉን ድርሻ እንደሚወስድ ግን መጠራጠር አይገባም። ስለዚህ ዛሬ በኢትዮጵያዊነቱ የሚያፍር ትውልድ ቢፈጠር ሊደንቀን አይገባም፥ አባቱን አያውቅ፣ አያቱን ናፈቀ ተብሏልና።

ትውልድ በትውልድ ሲተካ በጎም ሆነ መጥፎ ነገሮች ይከሰታሉ። የአሁኑ ወጣት ትውልድ ያለፉት ትውልዶች ያከማቹት ጥሪት ውጤት ነው። ባንዳነት እንደ መሠልጠን እየተቆጠረ፣ በጥራዝ-ነጠቅነት ከውጪ «አዲስ መጣ» የተባለውን ርዕዮተ-ዓለም ስላነበነቡ ብቻ «አዋቂ» የሚያስብል ባህል እንዲስፋፋ እየተደረገ፣ ስለ አገር ታሪክ እና ስለ ሕዝብ ባህል ከማወቅ ይልቅ በምዕራቡ ዓለም የሚፈበረኩ ርካሽ የባህል ሸቀጦች ማራገፊያ መሆን የዘመናዊነት ምልክት ተደርጎ እየታየ፣ ዓለም በቴክኖሎጂ እየተመነደገ ሲሄድ የእኛ አገር ገዢዎች ሕዝብን በማስራብ እና በጅምላ በመፍጀት ከፍተኛ መዋዕለ-ንዋይ ሲያከማቹ እንድ ብልጠት እየተቆጠረ፣ ወዘተርፈ፤ ይህ አዲሱ ወጣት ትውልድ ከማን ያየውን እና የተማረውን የመልካም የዜግነት ምግባር እንዲያሣይ ይጠበቃል? ስለዚህ ከታሪክ ተወቃሽነት፣ ከትውልዱም ፈፅሞ መጥፋት እንድንድን በአንድነት ለትክክለኛው ኢትዮጵያዊ ማንነታችን ልዕልና እንነሣ!

ኢትዮጵያ በጀግኖች እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘለዓለም ፀንታ ትኖራለች!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule