• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት ራሱን “ሳያጸዳ” በሌላው ዘምቷል

March 4, 2016 09:14 am by Editor 3 Comments

“የኢህአዴግን መርህ እስከተከተለ ድረስ መሃይምም ቢሆን ሚኒስትር እናደርጋለን” ያሉት መለስ ዙሪያቸውን “የበታች” በሆኑ ሹሞች አስከብበው የቆዩት ያለምክንያት አልነበረም፡፡ “አዋቂ፣ ጠቢብ፣ ባለራዕይ፣ ምንተስኖት፣ …” የሚሉ “ማዕረጎችን” አስገኝተውላቸዋል፡፡ ከዚህ አንጻር የፈለጉትን ሥልጣን ላይ ያስቀምጣሉ፤ ከዚያ በሙስና ያበሰብሳሉ፤ ከዚያም ወደ “ቆሻሻ ቅርጫት” ይጥላሉ፡፡ በሕይወት ለቆዩት “ቅርጫቱ” ትልቅ መድህን ሲሆን ለዚያ ያልታደሉት ግን ትርጉሙ ሌላ ነው፡፡ ይህ የመለስ አሠራር የህወሃት መመሪያ ሆኖ ቆይቷል፤ አሁንም እየተሰራበት ነው፡፡

በኦሮሞ ከተሞች በተነሳው ሕዝባዊ ንቅናቄ የተደናገጠው ህወሃት ከረፈደ “ጽዳት” ጀምሯል፡፡ የችግሩ መንስዔ ራሱ ሆኖ “ልክ መግባት” ሲገባው ለህዝብ “ሥራ ላይ ነን” ለማለት “የኦህዴድን አመራሮች” ማንሳቱ አስታውቋል፡፡

የጎልጉል እማኝ ዘጋቢዎች በላኩልን መረጃዎች መሠረት ዳባ ደበሌና ሰለሞን ኩቹ ከሥልጣናቸው ከተነሱ በኋላ “በደኅንነት ቁጥጥር ሥር” መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ምናልባት በካህኑ ህወሃት ፊት ቀርበው “ንሰሃ” ከገቡ የ“መዝገብ ቤት” ሥራ ሊያገኙ ይችላሉ፡፡ ካልሆነ ግን “ለታምራት ላይኔም አንራራም” እያለ “ንጽህናውን” የሚሰብከው ህወሃት “ወደሚነጹበት ቦታ” ይልካቸው ይሆናል የሚል አስተያየት ይነገራል፡፡

እማኝ ዘጋቢዎቻችን በላኩልን መረጃ መሠረት ሁለቱም በመሬት ችብቸባ ላይ ዋንኛ ተዋናዮች የነበሩ ሲሆን ይህንንም ሽያጭ እንዲያስፈጽሙ በህወሃት ሰዎች ቀጥተኛ ትዕዛዝ ይሰጣቸው እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ “የቡራዩን መሬት በማስቸብቸብ ቀዳሚው ሌባ መሆኑ አገር ያወቀው … (ባዶ በርሜል) የነበረና የስርአቱ መጠቀሚያ ሆኖ ያገለገለ … አሁን አገልግሎቱን ጨርሶ እንደ አሮጌ ቁና ተጣለ፡፡ የሌሎቹም አቃጣሪዎች ጊዜያቸው ሲያበቃ መጣላቸው አይቀርም” በማለት እማኝ ዘጋቢው ንዴት የተቀላቀለበትን ቁጭታቸውን ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ የኦሮሞ ከተሞች የተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ እያሸበረው የመጣው ህወሃት ራሱን ከማንጻት ይልቅ ሰይፉን በሌሎች ራሱ በወንጀልና በሙስና ባበሰበሳቸው ላይ መሰንዘሩ ከወትሮ ያልተለየ እና መለስ ትተውለት የሄዱትን “ውርስ/ሌጋሲ” እያስጠበቀ መሆኑ ለብዙዎች ግልጽ ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Sanjaw Sew Bela says

    March 6, 2016 01:04 am at 1:04 am

    Don’t just put a picture in your articles with out saying who it is and giving credit to the source or photographer. Same as your foot note saying give us credit for this news item. Gebito?!

    Reply
    • Editor says

      March 7, 2016 06:57 am at 6:57 am

      Give us the source, if you know it and we’d acknowledge it.

      Thanks

      Reply
  2. Yikir says

    March 29, 2016 09:49 pm at 9:49 pm

    1. Ke 4tegna kifil minister lemehon biye timihirten tewiku. 2 .MELES ZERAWI Zelalem yeminor mesilogn neber. 3 .kebadu sihtete ;Abebe Bikila bebado igiru roto alemim gud masegnetun mezengate sihon ;4 .ABEBE GELAW MENORUN MERSATE NEW. Lenegeru yeteshomutim tebareru. ATO H/MARIAM GIN SIYAYUT TILIK SEW AYIMESILIM??? Werada new.KALABAY .WASHO LEMALET NEW. Ye Abay tsehaye kal malete ayidelem.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule