• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት ራሱን “ሳያጸዳ” በሌላው ዘምቷል

March 4, 2016 09:14 am by Editor 3 Comments

“የኢህአዴግን መርህ እስከተከተለ ድረስ መሃይምም ቢሆን ሚኒስትር እናደርጋለን” ያሉት መለስ ዙሪያቸውን “የበታች” በሆኑ ሹሞች አስከብበው የቆዩት ያለምክንያት አልነበረም፡፡ “አዋቂ፣ ጠቢብ፣ ባለራዕይ፣ ምንተስኖት፣ …” የሚሉ “ማዕረጎችን” አስገኝተውላቸዋል፡፡ ከዚህ አንጻር የፈለጉትን ሥልጣን ላይ ያስቀምጣሉ፤ ከዚያ በሙስና ያበሰብሳሉ፤ ከዚያም ወደ “ቆሻሻ ቅርጫት” ይጥላሉ፡፡ በሕይወት ለቆዩት “ቅርጫቱ” ትልቅ መድህን ሲሆን ለዚያ ያልታደሉት ግን ትርጉሙ ሌላ ነው፡፡ ይህ የመለስ አሠራር የህወሃት መመሪያ ሆኖ ቆይቷል፤ አሁንም እየተሰራበት ነው፡፡

በኦሮሞ ከተሞች በተነሳው ሕዝባዊ ንቅናቄ የተደናገጠው ህወሃት ከረፈደ “ጽዳት” ጀምሯል፡፡ የችግሩ መንስዔ ራሱ ሆኖ “ልክ መግባት” ሲገባው ለህዝብ “ሥራ ላይ ነን” ለማለት “የኦህዴድን አመራሮች” ማንሳቱ አስታውቋል፡፡

የጎልጉል እማኝ ዘጋቢዎች በላኩልን መረጃዎች መሠረት ዳባ ደበሌና ሰለሞን ኩቹ ከሥልጣናቸው ከተነሱ በኋላ “በደኅንነት ቁጥጥር ሥር” መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ምናልባት በካህኑ ህወሃት ፊት ቀርበው “ንሰሃ” ከገቡ የ“መዝገብ ቤት” ሥራ ሊያገኙ ይችላሉ፡፡ ካልሆነ ግን “ለታምራት ላይኔም አንራራም” እያለ “ንጽህናውን” የሚሰብከው ህወሃት “ወደሚነጹበት ቦታ” ይልካቸው ይሆናል የሚል አስተያየት ይነገራል፡፡

እማኝ ዘጋቢዎቻችን በላኩልን መረጃ መሠረት ሁለቱም በመሬት ችብቸባ ላይ ዋንኛ ተዋናዮች የነበሩ ሲሆን ይህንንም ሽያጭ እንዲያስፈጽሙ በህወሃት ሰዎች ቀጥተኛ ትዕዛዝ ይሰጣቸው እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ “የቡራዩን መሬት በማስቸብቸብ ቀዳሚው ሌባ መሆኑ አገር ያወቀው … (ባዶ በርሜል) የነበረና የስርአቱ መጠቀሚያ ሆኖ ያገለገለ … አሁን አገልግሎቱን ጨርሶ እንደ አሮጌ ቁና ተጣለ፡፡ የሌሎቹም አቃጣሪዎች ጊዜያቸው ሲያበቃ መጣላቸው አይቀርም” በማለት እማኝ ዘጋቢው ንዴት የተቀላቀለበትን ቁጭታቸውን ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ የኦሮሞ ከተሞች የተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ እያሸበረው የመጣው ህወሃት ራሱን ከማንጻት ይልቅ ሰይፉን በሌሎች ራሱ በወንጀልና በሙስና ባበሰበሳቸው ላይ መሰንዘሩ ከወትሮ ያልተለየ እና መለስ ትተውለት የሄዱትን “ውርስ/ሌጋሲ” እያስጠበቀ መሆኑ ለብዙዎች ግልጽ ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Sanjaw Sew Bela says

    March 6, 2016 01:04 am at 1:04 am

    Don’t just put a picture in your articles with out saying who it is and giving credit to the source or photographer. Same as your foot note saying give us credit for this news item. Gebito?!

    Reply
    • Editor says

      March 7, 2016 06:57 am at 6:57 am

      Give us the source, if you know it and we’d acknowledge it.

      Thanks

      Reply
  2. Yikir says

    March 29, 2016 09:49 pm at 9:49 pm

    1. Ke 4tegna kifil minister lemehon biye timihirten tewiku. 2 .MELES ZERAWI Zelalem yeminor mesilogn neber. 3 .kebadu sihtete ;Abebe Bikila bebado igiru roto alemim gud masegnetun mezengate sihon ;4 .ABEBE GELAW MENORUN MERSATE NEW. Lenegeru yeteshomutim tebareru. ATO H/MARIAM GIN SIYAYUT TILIK SEW AYIMESILIM??? Werada new.KALABAY .WASHO LEMALET NEW. Ye Abay tsehaye kal malete ayidelem.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule