• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት ራሱን “ሳያጸዳ” በሌላው ዘምቷል

March 4, 2016 09:14 am by Editor 3 Comments

“የኢህአዴግን መርህ እስከተከተለ ድረስ መሃይምም ቢሆን ሚኒስትር እናደርጋለን” ያሉት መለስ ዙሪያቸውን “የበታች” በሆኑ ሹሞች አስከብበው የቆዩት ያለምክንያት አልነበረም፡፡ “አዋቂ፣ ጠቢብ፣ ባለራዕይ፣ ምንተስኖት፣ …” የሚሉ “ማዕረጎችን” አስገኝተውላቸዋል፡፡ ከዚህ አንጻር የፈለጉትን ሥልጣን ላይ ያስቀምጣሉ፤ ከዚያ በሙስና ያበሰብሳሉ፤ ከዚያም ወደ “ቆሻሻ ቅርጫት” ይጥላሉ፡፡ በሕይወት ለቆዩት “ቅርጫቱ” ትልቅ መድህን ሲሆን ለዚያ ያልታደሉት ግን ትርጉሙ ሌላ ነው፡፡ ይህ የመለስ አሠራር የህወሃት መመሪያ ሆኖ ቆይቷል፤ አሁንም እየተሰራበት ነው፡፡

በኦሮሞ ከተሞች በተነሳው ሕዝባዊ ንቅናቄ የተደናገጠው ህወሃት ከረፈደ “ጽዳት” ጀምሯል፡፡ የችግሩ መንስዔ ራሱ ሆኖ “ልክ መግባት” ሲገባው ለህዝብ “ሥራ ላይ ነን” ለማለት “የኦህዴድን አመራሮች” ማንሳቱ አስታውቋል፡፡

የጎልጉል እማኝ ዘጋቢዎች በላኩልን መረጃዎች መሠረት ዳባ ደበሌና ሰለሞን ኩቹ ከሥልጣናቸው ከተነሱ በኋላ “በደኅንነት ቁጥጥር ሥር” መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ምናልባት በካህኑ ህወሃት ፊት ቀርበው “ንሰሃ” ከገቡ የ“መዝገብ ቤት” ሥራ ሊያገኙ ይችላሉ፡፡ ካልሆነ ግን “ለታምራት ላይኔም አንራራም” እያለ “ንጽህናውን” የሚሰብከው ህወሃት “ወደሚነጹበት ቦታ” ይልካቸው ይሆናል የሚል አስተያየት ይነገራል፡፡

እማኝ ዘጋቢዎቻችን በላኩልን መረጃ መሠረት ሁለቱም በመሬት ችብቸባ ላይ ዋንኛ ተዋናዮች የነበሩ ሲሆን ይህንንም ሽያጭ እንዲያስፈጽሙ በህወሃት ሰዎች ቀጥተኛ ትዕዛዝ ይሰጣቸው እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ “የቡራዩን መሬት በማስቸብቸብ ቀዳሚው ሌባ መሆኑ አገር ያወቀው … (ባዶ በርሜል) የነበረና የስርአቱ መጠቀሚያ ሆኖ ያገለገለ … አሁን አገልግሎቱን ጨርሶ እንደ አሮጌ ቁና ተጣለ፡፡ የሌሎቹም አቃጣሪዎች ጊዜያቸው ሲያበቃ መጣላቸው አይቀርም” በማለት እማኝ ዘጋቢው ንዴት የተቀላቀለበትን ቁጭታቸውን ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ የኦሮሞ ከተሞች የተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ እያሸበረው የመጣው ህወሃት ራሱን ከማንጻት ይልቅ ሰይፉን በሌሎች ራሱ በወንጀልና በሙስና ባበሰበሳቸው ላይ መሰንዘሩ ከወትሮ ያልተለየ እና መለስ ትተውለት የሄዱትን “ውርስ/ሌጋሲ” እያስጠበቀ መሆኑ ለብዙዎች ግልጽ ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Sanjaw Sew Bela says

    March 6, 2016 01:04 am at 1:04 am

    Don’t just put a picture in your articles with out saying who it is and giving credit to the source or photographer. Same as your foot note saying give us credit for this news item. Gebito?!

    Reply
    • Editor says

      March 7, 2016 06:57 am at 6:57 am

      Give us the source, if you know it and we’d acknowledge it.

      Thanks

      Reply
  2. Yikir says

    March 29, 2016 09:49 pm at 9:49 pm

    1. Ke 4tegna kifil minister lemehon biye timihirten tewiku. 2 .MELES ZERAWI Zelalem yeminor mesilogn neber. 3 .kebadu sihtete ;Abebe Bikila bebado igiru roto alemim gud masegnetun mezengate sihon ;4 .ABEBE GELAW MENORUN MERSATE NEW. Lenegeru yeteshomutim tebareru. ATO H/MARIAM GIN SIYAYUT TILIK SEW AYIMESILIM??? Werada new.KALABAY .WASHO LEMALET NEW. Ye Abay tsehaye kal malete ayidelem.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule