• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢሳያስ ከ“ጎረቤት” ትግራይ በፊት የአማራን ክልል ሊጎበኙ ነው

August 17, 2018 07:54 pm by Editor 3 Comments

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኤርትራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የሰላም ስምምነት ከፈፀሙና ሁለቱ መሪዎች በየአገራቱ ጉብኝት ካደረጉ በኋላ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ያለው ግንኙነት ከመንግሥት አልፎ በሕዝብ ደረጃ በርካታ ለውጦችን አምጥቶዋል። ይህንን ተከትሎ ኢሳያስ ለመጀመሪያ ጊዜ በክልል ደረጃ የአማራን ብሔራዊ ክልልን እንደሚጎበኙ ተገልጾዋል። ኤርትራን ከትግራ ጋር እንድታብር  ለሚመኛትና በኢሳያስ አጠራር የህወሓት “ጥምብ አንሣዎች” ይህ ትልቅ የፖለቲካ ኪሳራና ውርደት ነው ተብሏል።

ፋና ባሰራጨው ዜና ላይ እንደተገለጸው “የአማራ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ንጉሡ ጥላሁን የሚመሩት ልኡክ በአስመራ ይገኛል። በቆይታቸውም አቶ ንጉሱ ጥላሁን ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ልዩ አማካሪ ከአቶ የማነ ገብረአብ ጋር የኤርትራውያንንና የኢትዮጵያውያንን የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ላይ መወያየታቸውን አስታውቀዋል” ብሏል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ “እንዲሁም የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የሚመሩት የልዑካን ቡድን ወደ አማራ ክልል እንዲሚመጣ ከስምምነት መድረሳቸውም” አቶ ንጉሡ አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ኤርትራ ሄደው በነበሩበት ወቅት ከኤርትራ ጋር የመጀመሪያውን የወዳጅነት እግርኳስ ጨዋታ ለማድረግ የጠየቀው የአማራ ክልል ፌዴሬሽን ጥያቄው ወዲያውኑ ተመልሶለታል።የሤራና ተራ የሽቅድምድም ፖለቲካ የሚጫወተው የወንበዴው ቡድን ህወሓት በቀጣይ የትግራይ ክልል ጨዋታ እንዲያደርግ የጠየቀ መሆኑ በወቅቱ የተዘገበ ጉዳይ ነበር።

“የኤርትራ ልጆች! አማራ ባህራችሁን ይፈልጋል፤ እኛ ትግራዮች ግን የምንፈልገው ፍቅራችሁን ነው”

ኢሳያስ ከኢትዮጵያ ጋር የቀጥታ ግንኙነት በማድረጋቸው ታላቅ የፖለቲካ ኪሳራ ውስጥ የገባው ህወሓት ለኤርትራ የምንቀርበው እኛ ነን፤ በደምም የተሳሰርነው እኛ ነን ከማለት አልፎ “የኤርትራ ልጆች! አማራ ባህራችሁን ይፈልጋል፤ እኛ ትግራዮች ግን የምንፈልገው ፍቅራችሁን ነው” እስከማለት የደረሰ መሆኑ አይዘነጋም።

በመቀጠልም ኢሳያስን ለማባበል እና ኤርትራውያንን ወገናዊ ለማድረግ የኤርትራ ቲቪ ወደ ትግራይ መጥቶ እንዲዘግብ ህወሓት ያቀረበው ጥያቄ ኢሳያስና መንግሥታቸው ከህወሓት ጋር የጎንዮሽ ግንኙነት እንደያማያደርጉ በመግለጽ ጥሪውን ውድቅ ማድረጋቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው።

ህወሓትን የፈጠሩትና ማንነቱን የሚውቁት ኢሳያስ አሁን ባለንበት ወቅት ህወሓትን አጥብቀው ይጸየፉታል፤ የወንበዴ ቡድኑንም መሪዎች እጅግ ይንቋቸዋል። ከዚህ አንጻር ህወሓት የኢትዮጵያና የኤርትራ የጋራ ጠላት መሆኑን ኢሳያስ በውል ያውቃሉ። (በዚህ ጉዳይ ላይ ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ ያቀናበረው ዘገባ እዚህ ላይ ይገኛል)።

ኢሳያስ አፈወርቂ እኤአ ሰኔ 20 (ሰኔ 13) ባደረጉት ንግግር በኢትዮጵያ እየተከሰተ ስላለው ለውጥ ካደነቁ በኋላ በዋንኛነት የንግግራቸው ትኩረት የነበረው “መርዘኛ፣ በጣም አደገኛ፣ (ተንኮለኛና ምቀኛ) ስለሆነው የህወሓት ሌጋሲ” ነበር። ሲቀጥሉም የህወሓት “ጥምብ አንሣዎች” ሥልጣናቸውን እንዳጡ ሲያውቁ በመደናገጥ “አዎንታዊውን ለውጥ ለማጨናገፍ” ይህም በሁለቱ አገራትና በኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚሠሩ ንግግራቸውን ሊያደምጥ ለተሰበሰበው ሕዝባቸው በግልጽ ተናግረው ነበር። ይህንን ካሉ በኋላ ነበር ከዶ/ር ዐቢይ ጋር የሰላም ግንኙነቱን መስመር ማስያዝ የጀመሩት።

በዚህ ዓይነት የለውጥ ሂደት ላይ የሚገኙት የሻዕቢያ መሪዎች እየወሰዱ ያሉት እርምጃ ህወሓትን ትልቅ ኪሳራና ውርደት ውስጥ ቢከተውም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን ለዓመታት ሲመኘው የኖረው ሐቅ ነው በማለት ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ግለሰብ ይናገራሉ። ይህ የማይገባው ህወሓት ግን አሁንም የጥላቻ ፖለቲካውን ለመተግበር ከላይ ታች ደፋ ቀና ይላል፤ ባይሳካለትም ሙከራውን ይቀጥላል፤ ሁሉንም የሚያደርገው ደግሞ በትግራይ ሕዝብ ስም ስለሆነ እንዳንዱ የትግራይ ሕዝብ ይህንን የህወሓት መሠሪነት አጥብቆ በመቃወም ዶ/ር ዐቢይ እንዳሉት “አንቅሮ ሊተፋቸው” ይገባል። ሕዝብ የተፋው ህወሓት ከነወንበዴ መሪዎቹ ወደ መቃብር መግባቱ የማይቀር ይሆናል በማለት አስተያየት ሰጪው ተናግረዋል።

ማስተካከያ – የማነ ገብረአብ ተናገሩት ብለን የጠቀስነው ህወሃት በEritrea Press ስም በከፈተው ማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ ሆኖ ስላገኘነው ከይቅርታ ጋር መረጃውን አንስተነዋል። ከአንባቢዎቻችን በውስጥ መስመር በደረሰን መረጃ መሰረት ከታላቅ ይቅርታ ጋር ማስተካከያ አድርገናል። በEritrean Press ስም የተከፈቱት ሁለቱም የማኅበራዊ ድረገጾች (አንዱ እውነተኛ የኤርትራ ፕሬስ ሲሆን ሌላኛውና አነስተኛ ተከታይ ያለው የህወሓት የሳይበር አርበኞች የከፈቱት መሆኑ ይታወቃል) አወዛጋቢ ሆነው መቆየታቸውን ብናስታውስም ይህንን መረጃ ግን በወቅቱ በፋይል ክምችታችን ውስጥ አስቀምጠነው ስለነበር በመዘንጋት እንደትክክለኛ መረጃ አውጥተን ልንጠቀምበት ችለናል። ለስህተቱ ሙሉ ኃላፊነት እንወስዳለን።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: bahir dar, Eritrea, Full Width Top, isayas, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Biniam says

    August 18, 2018 08:46 am at 8:46 am

    እርማት ይደረግ፡
    “የማነ ገብረአብ” ተናገሩት ተብሎ ” Eritrean Press ” የተባለው በቅርብ በወያነ የተገነባ ወብ-ሳይት በመጥቀስ አማካሪው አቶ የማነ ገብረአብ ያልተናገሩት ነውር የሐሰት ወሬ ተቅሳቹ እንደ source መጠቀማቹ ትክክል አይደለም። ወያነ “Eritrean Press ” የሚባል እውነተኛው የኤርትራ ወብ-ሳይት ስም በመጠቀም አካውንት መፍጠሩ እና ይህን የሚያጋልጥ በ ሶሻል ሚድያ ተሰረጭተዋል። ለተጨማሪ
    Be Aware Of Fake ‘Eritrean Press’ Accounts on facebook https://twitter.com/EriLoveer/status/1020405837418967040

    Reply
    • Editor says

      August 18, 2018 09:20 am at 9:20 am

      Biniam

      ለአስተያየቱ እናመሰግናለን። ከእርስዎና ከሌሎች በውስጥ መስመር በደረሰን መረጃ መሰረት ከታላቅ ይቅርታ ጋር ማስተካከያ አድርገናል። በEritrean Press ስም የተከፈቱት ሁለቱም የማኅበራዊ ድረገጾች (አንዱ እውነተኛ የኤርትራ ፕሬስ ሲሆን ሌላኛውና አነስተኛ ተከታይ ያለው የህወሓት የሳይበር አርበኞች የከፈቱት መሆኑ ይታወቃል) አወዛጋቢ ሆነው መቆየታቸውን ብናስታውስም ይህንን መረጃ ግን በወቅቱ በፋይል ክምችታችን ውስጥ አስቀምጠነው ስለነበር በመዘንጋት እንደትክክለኛ መረጃ አውጥተን ልንጠቀምበት ችለናል።

      ለስህተቱ ሙሉ ኃላፊነት እንወስዳለን።

      ከታላቅ ምስጋና ጋር
      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
  2. Tesfa says

    August 20, 2018 01:49 pm at 1:49 pm

    አወናባጅ ሃይሎች ዛሬም በመልካም ነገር ላይ ጥላሸት መቀባትና ህዝባችንን መከፋፈል ቋሚ ተግባራቸው ነው። የኤርትራው መሪ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር መጎብኘት ዳንኪራ አያስመታም። ሃገሩ ነው። ችግሩ ሰልፋችን ሁሉ የአስረሽ ምቺው ሆነና አቋቋማችን ተንጋደደ። የምናስበውና የምንተነፍስበት ጭንቅላትና ሳንባ በፓለቲካና በዘር ዙሪያ የተገጠመልን በመሆኑ የተከታይ ተከታይ ሆነን እንሆ አንድ የሚያረጉንን ነገር እያፈረስን በሚያራርቁን ላይ እሳቱ ቦግ ብሎ እንዲነድ ነዳጅ ስናቀርብ ቆይተናል። ይህ ጊዜ ማንም ያላተረፈበት የኪሳራ ዘመን እንደነበር አቶ ኢሳይያስ በግልጽ አስቀምጠውታል።
    አሁን በኢትዮጵያና በኤርትራ የተደረሰው ስምምነት የውጭ ሃይል ያልገባበት፤ በሁለት መሪዎች መካከል የተፈጸመ ተግባር ነው። ይህ ራሱ ህዝባችንን ሊያኮራ ይገባል። የራስን ችግር በራስ መፍታት። ይህ ግን በዘራቸውና በጥቅማቸው ለሰከሩ አይታያቸውም። ልምዳቸው እየቀሙ እየገደሉ እያሰሩ መኖር ነውና! ይህንም አጥፊ ስራቸውን ለማበራከት በእየ ድህረ – ገጽ የፈጠራ ወሬ መንዛታቸው አንሶ መሳይ ድህረ – ገጾችንም በማቅረብ ህዝባችንን ለማወናበድ የሚያደርጉት ሴራ ዛሬም አልተገታም። የጎጥ ፓለቲከኞች ዛሬም አካኪ ዘራፍ ከማለት አላለፉም። ሃገርና አፍሪቃ አቀፍ እይታ ኑሮአቸው አያውቅም። በነጻነት ስም ባርነትን፤ በህዝብ ስም ንግድን የለመድ እኔ አውቅላችሁሃለሁ የሚሉ ጎጠኞች ዛሬ ወድቀው በመፈራገጥ ላይ ናቸው። ለበደልና ለግፍ ማብቂያ አለው። የእናንተ ቀን ለማክተሙ ምስክር አያሻም። ህዝባችን ወደ ነበረበት የግፍ ዓመታት ላይመለስ ቆርጦ ተነስቷል። ለፕሬዝደንት ኢሳያስም መልካም ጉዞና የጉብኝት ጊዜ እንዲሆንላቸው ከወዲሁ እመኛለሁ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule