• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሁለቱ ጄኔራሎች

June 11, 2018 10:07 am by Editor Leave a Comment

ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ እና ሜ/ጀኔራል አለምሸት ደግፌ ከመከላከያ ሰራዊቱ በተለያየ ጊዜ “የመከላከያ ሪፎርም አደናቃፊ” በሚል ማዕረጋቸው ተገፍፎ የተሰናበቱ ወታደራዊ መኮንኖች ናቸው። ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ የቀድሞ የጦር ሠራዊት አባል የነበረና በ1978 ዓ.ም ኢህዴንን የተቀላቀለ ጀግና አዋጊ እንደሆነ የኢህዴን ጓዶቹ ሳይቀር ይመሰክሩለታል። ድህረ-ደርግ በሲቪል አስተዳዳሪነት የላስታ ወረዳ አስተዳደር ቀጥሎም የሰሜን ወሎ ዞን አመራር ሆኖ ሰርቷል።

የባድመ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ ወደ ወታደራዊ አመራርነት የተመለሰው አሳምነው ጽጌ፣ የቀደመ የትግል ልምዱን መነሻ በማድረግ ያለአንዳች ማዕረግ በጦርነቱ ውስጥ በባድመ የጦር ግንባር 22ኛ ክፍለ ጦርን እየመራ ተዋግቷል። ባድመ ላይ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ሲውለበለብ ከነበሩት ጥቂት አመራሮች አንዱ አሳምነው ጽጌ ይገኝበት ነበር።በጦርነቱ ጊዜ በህወሓት የጦር መኮንኖች ብስለት አልባ የጦር ስትራቴጅና በጦር ግንባሩ ላይ ያደረሱት የጦርነት ኪሳራዎች የከነከነው አሳምነው ጽጌ የህወሃት የበላይነት በሰራዊቱ ውስጥ መኖሩን በመረጃ በመሞገት 1993ዓ.ም ሀረር ሁርሶ ላይ በተካሄደ  መድረክ ላይ በመድረኩ ተሳታፊዎች ስምምነት እንዲደረስበት አድርጓል።

ከባድመ ጦርነት በኋላ ወደ ሲቪል አመራርነት በመመለስ መከላከያ ውስጥ ያለውን የህወሓት የበላይነት  በአመለካከት ደረጃ እየተዋጋሁ መከላከያ ውስጥ ልቆይ በሚል ሊቆይ እንደቻለ የሚገልጹት የጎልጉል የመረጃ ምንጮች፤ አሳምነው አሜሪካ ሀገር ለአንድ አመት ወታደራዊ ትምህርት ተምሮ መምጣቱን ይገልጻሉ። ከአሜሪካ ወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት መልስ የብርጋዴል ጀኔራልነት ማዕረግ የተሰጠው አሳምነው ጽጌ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲን እንዲያቋቁም የጠሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ እንደተወጣ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ነባር መምህራን ይመሰክሩለታል።

የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንደሚሉት “አሳምነው መከላከያ ዩኒቨርሲቲን በብቃት መርቷል። ሆኖም ተቋሙን በሚመራበት ወቅት የህወሓት ሰዎች ‹አሳምነው አሜሪካ ሄዶ ያመጣው ነገር አለ› በሚል ያዋክቡት ነበር” ይላሉ። “አሳምነው ወደ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች (ወታደሮች) በፈተና እንዲገቡ በማድረጉ ጥርስ ውስጥ ገብቷል” የሚሉት ምንጮቻችን በፈተናውም ብዙ የአማራ ልጆች በማለፋቸው የበለጠ አሳምነው ከህወሓት ሰዎች ጋር መቃቃሩን ያስታውሳሉ።

“እንዴት ብዙ አማራዎች ፈተናውን ሊያልፉ ቻሉ” በሚል ሲጠየቅ አሳምነው ለነሳሞራ “ውጤቱን ካላመናችሁ ፈተናውን ራሳችሁ አውጥታችሁ ፈትኗቸው” እንዳላቸው እና ሳሞራ የኑስ በበኩሉ “ይህማ አይሆንም፣ ትምህርት ቤቱ ይፈርሳል እንጂ ይሄን ያህል ቁጥር አማራ አይማርበትም” እስከማለት ደርሶ እንደነበር የወቅቱን ሁኔታ ያስታውሳሉ። ጉዳዩ እስከ መለስ ዜናዊ ደርሶ በመጨረሻ በወታደራዊ ትምህርት ቤቱ የተነሳው መካረር አድጎ ጀኔራል አሳምነው እንዲታገድ መደረጉና ከዚህም አልፎ በሳሞራ የኑስ ነገር ማወሳሰብ የተነሳ “የመከላከያ ሪፎርም አደናቃፊ” በሚል በ1998ዓ.ም ማዕረጉ ተገፍፎ ከሠራዊት አባልነቱ መሰናበቱ የሚታወስ ነው።

ጀኔራሉ በሚያዚያ 2001ዓ.ም “መፈንቅለ መንግስት ሙከራ” ላይ ተሳትፈሃል በሚል ክስ ተመስርቶበት እድሜ ልክ ተፈርዶበት በቅርቡ ከ9 አመታት እስር በኋላ ተፈቷል። ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ በሰራዊቱ ውስጥ በቆየባቸው ዓመታት ከሳሞራ የኑስ ጋር ስምምነት እንዳልነበራቸው የሚገልጹት የመረጃ ምንጮቻችን፤ ሳሞራ የኑስ ከኤታማዦር ሹምነቱ በተነሳበት ሰዓት ቤተመንግሥት በክብር እንግድነት ተገኝቶ ወታደራዊ ማዕረጉ በክብር መመለሱና ጡረታ እንዲወጣ መደረጉ ሳሞራን በእጅጉ ያስከፋው ድርጊት መሆኑን የመረጃ ምንጮቻቸን ዘገባ ይጠቁማል።

ዝዋይ አስርቤት ሆኖ ሞቱን ሲጠብቅ የነበረው የኢህዴኑ ታጋይ ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ በህዝባዊ ኃይል ጫና ከእስር ተፈትቶ ወታደራዊ ማዕረጉ በጠላቱ ፊት እንዲመለስለት የተደረገበት አጋጣሚ ለብአዴን ሰዎች የሰርግና ምላሽ ያህል ሲያስፈነድቃቸው የህወሓት ሰዎችን ደግሞ ጸጉር እንዳስነጫቸው የአደባባይ ምሥጢር ነው።

በተመሳሳይ መልኩ የኦህዴድ ሰዎችን ያስፈነጨ ድርጊትም ታይቷል። የኦህዴዱ ሜ/ጄኔራል አለምሸት ደግፌ የኢህዴን መስራቹን ሜ/ጀኔራል ኃይሌ ጥላሁንን ተክቶ የአየር ኃይል አዛዥ እንደነበር ይታወሳል። የቀድሞው ጦር ሠራዊት አባል የነበረውና ሩሲያ ድረስ ተልኮ ከፍተኛ የወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት እንደተማረ የሚነገርለት ይሄው ጀኔራል ብዙም ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ “የመከላከያ ሪፎርም አደናቃፊ” በሚል ማዕረጉን ተገፎ ከሠራዊቱ እንደተሰናበተ ይታወቃል።

ጄኔራሉ የአየር ኃይል አዛዥ በነበረበት ወቅት ከጦር አውሮፕላኖች እና የመለዋወጫ  ግዥዎች ጋር ተያይዞ በሙስና ንክኪ እንዳለበት እና “የድርሻህን ይዘህ ጥፋ” የተባለው ጄኔራል፤ ሲ.ኤም.ሲ ላይ “አይማ ኢንተርናሽናል” የተባለ ታዋቂ ሆቴል በስሙ ከፍቶ ንግዱን በማጧጧፍ ላይ ይገኛል። “ኢህዴን/ብአዴን ብቻውን ከሚደሰት አጫፋሪ ያግኝ” በሚል የሜ/ጀኔራል አለምሸት ደግፌ ማዕረግ ሊመለስለት እንደቻለ የመረጃ ምንጮቻችን ይገልጻሉ። ጀኔራሉም “የኦሮሞ ዘመን አሁን ነው” በሚል መኩራራት በቤተመንግሥቱ ውስጥ ሲናገር እንዳመሸ የሚገልጹት የመረጃ ምንጮቻችን ጄኔራሉ የሆቴል ንግዱ የተስማማው በመሆኑ ወታደራዊ ማዕረጉ መመለሱ ለህይወት ታሪኩ ማሟያ እንጂ ለኑሮ መደገፊያ እንደማይጠቀምበት ለህወሓትም ሆነ ለኦህዴድ አመራሮች ግልጽ መሆኑን ያስረዳሉ ነው።

ከአራተኛ ክፍል ዕውቀት ያላለፈ የትምህርት ደረጃ ላይ ከሚገኙት የህወሓት ጄኔራሎች አንጻር በተለይ (ሜ/ጄ አለምሸት ወደ ንግዱ በመመለሱ ካልፈለገው) የብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ወደ ሠራዊቱ በከፍተኛ አማካሪነት ወይም በሌላ ጠቃሚ መስክ መመለስ ለአገርም ለሠራዊቱም ጠቃሚ እንደሆነ በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ አስተያየት የሚሰጡ ይናገራሉ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Filed Under: Uncategorized Tagged With: alemshet, asaminew, degefe, Full Width Top, Middle Column, tsigie

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule