• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሁለቱ ጄኔራሎች

June 11, 2018 10:07 am by Editor Leave a Comment

ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ እና ሜ/ጀኔራል አለምሸት ደግፌ ከመከላከያ ሰራዊቱ በተለያየ ጊዜ “የመከላከያ ሪፎርም አደናቃፊ” በሚል ማዕረጋቸው ተገፍፎ የተሰናበቱ ወታደራዊ መኮንኖች ናቸው። ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ የቀድሞ የጦር ሠራዊት አባል የነበረና በ1978 ዓ.ም ኢህዴንን የተቀላቀለ ጀግና አዋጊ እንደሆነ የኢህዴን ጓዶቹ ሳይቀር ይመሰክሩለታል። ድህረ-ደርግ በሲቪል አስተዳዳሪነት የላስታ ወረዳ አስተዳደር ቀጥሎም የሰሜን ወሎ ዞን አመራር ሆኖ ሰርቷል።

የባድመ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ ወደ ወታደራዊ አመራርነት የተመለሰው አሳምነው ጽጌ፣ የቀደመ የትግል ልምዱን መነሻ በማድረግ ያለአንዳች ማዕረግ በጦርነቱ ውስጥ በባድመ የጦር ግንባር 22ኛ ክፍለ ጦርን እየመራ ተዋግቷል። ባድመ ላይ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ሲውለበለብ ከነበሩት ጥቂት አመራሮች አንዱ አሳምነው ጽጌ ይገኝበት ነበር።በጦርነቱ ጊዜ በህወሓት የጦር መኮንኖች ብስለት አልባ የጦር ስትራቴጅና በጦር ግንባሩ ላይ ያደረሱት የጦርነት ኪሳራዎች የከነከነው አሳምነው ጽጌ የህወሃት የበላይነት በሰራዊቱ ውስጥ መኖሩን በመረጃ በመሞገት 1993ዓ.ም ሀረር ሁርሶ ላይ በተካሄደ  መድረክ ላይ በመድረኩ ተሳታፊዎች ስምምነት እንዲደረስበት አድርጓል።

ከባድመ ጦርነት በኋላ ወደ ሲቪል አመራርነት በመመለስ መከላከያ ውስጥ ያለውን የህወሓት የበላይነት  በአመለካከት ደረጃ እየተዋጋሁ መከላከያ ውስጥ ልቆይ በሚል ሊቆይ እንደቻለ የሚገልጹት የጎልጉል የመረጃ ምንጮች፤ አሳምነው አሜሪካ ሀገር ለአንድ አመት ወታደራዊ ትምህርት ተምሮ መምጣቱን ይገልጻሉ። ከአሜሪካ ወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት መልስ የብርጋዴል ጀኔራልነት ማዕረግ የተሰጠው አሳምነው ጽጌ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲን እንዲያቋቁም የጠሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ እንደተወጣ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ነባር መምህራን ይመሰክሩለታል።

የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንደሚሉት “አሳምነው መከላከያ ዩኒቨርሲቲን በብቃት መርቷል። ሆኖም ተቋሙን በሚመራበት ወቅት የህወሓት ሰዎች ‹አሳምነው አሜሪካ ሄዶ ያመጣው ነገር አለ› በሚል ያዋክቡት ነበር” ይላሉ። “አሳምነው ወደ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች (ወታደሮች) በፈተና እንዲገቡ በማድረጉ ጥርስ ውስጥ ገብቷል” የሚሉት ምንጮቻችን በፈተናውም ብዙ የአማራ ልጆች በማለፋቸው የበለጠ አሳምነው ከህወሓት ሰዎች ጋር መቃቃሩን ያስታውሳሉ።

“እንዴት ብዙ አማራዎች ፈተናውን ሊያልፉ ቻሉ” በሚል ሲጠየቅ አሳምነው ለነሳሞራ “ውጤቱን ካላመናችሁ ፈተናውን ራሳችሁ አውጥታችሁ ፈትኗቸው” እንዳላቸው እና ሳሞራ የኑስ በበኩሉ “ይህማ አይሆንም፣ ትምህርት ቤቱ ይፈርሳል እንጂ ይሄን ያህል ቁጥር አማራ አይማርበትም” እስከማለት ደርሶ እንደነበር የወቅቱን ሁኔታ ያስታውሳሉ። ጉዳዩ እስከ መለስ ዜናዊ ደርሶ በመጨረሻ በወታደራዊ ትምህርት ቤቱ የተነሳው መካረር አድጎ ጀኔራል አሳምነው እንዲታገድ መደረጉና ከዚህም አልፎ በሳሞራ የኑስ ነገር ማወሳሰብ የተነሳ “የመከላከያ ሪፎርም አደናቃፊ” በሚል በ1998ዓ.ም ማዕረጉ ተገፍፎ ከሠራዊት አባልነቱ መሰናበቱ የሚታወስ ነው።

ጀኔራሉ በሚያዚያ 2001ዓ.ም “መፈንቅለ መንግስት ሙከራ” ላይ ተሳትፈሃል በሚል ክስ ተመስርቶበት እድሜ ልክ ተፈርዶበት በቅርቡ ከ9 አመታት እስር በኋላ ተፈቷል። ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ በሰራዊቱ ውስጥ በቆየባቸው ዓመታት ከሳሞራ የኑስ ጋር ስምምነት እንዳልነበራቸው የሚገልጹት የመረጃ ምንጮቻችን፤ ሳሞራ የኑስ ከኤታማዦር ሹምነቱ በተነሳበት ሰዓት ቤተመንግሥት በክብር እንግድነት ተገኝቶ ወታደራዊ ማዕረጉ በክብር መመለሱና ጡረታ እንዲወጣ መደረጉ ሳሞራን በእጅጉ ያስከፋው ድርጊት መሆኑን የመረጃ ምንጮቻቸን ዘገባ ይጠቁማል።

ዝዋይ አስርቤት ሆኖ ሞቱን ሲጠብቅ የነበረው የኢህዴኑ ታጋይ ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ በህዝባዊ ኃይል ጫና ከእስር ተፈትቶ ወታደራዊ ማዕረጉ በጠላቱ ፊት እንዲመለስለት የተደረገበት አጋጣሚ ለብአዴን ሰዎች የሰርግና ምላሽ ያህል ሲያስፈነድቃቸው የህወሓት ሰዎችን ደግሞ ጸጉር እንዳስነጫቸው የአደባባይ ምሥጢር ነው።

በተመሳሳይ መልኩ የኦህዴድ ሰዎችን ያስፈነጨ ድርጊትም ታይቷል። የኦህዴዱ ሜ/ጄኔራል አለምሸት ደግፌ የኢህዴን መስራቹን ሜ/ጀኔራል ኃይሌ ጥላሁንን ተክቶ የአየር ኃይል አዛዥ እንደነበር ይታወሳል። የቀድሞው ጦር ሠራዊት አባል የነበረውና ሩሲያ ድረስ ተልኮ ከፍተኛ የወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት እንደተማረ የሚነገርለት ይሄው ጀኔራል ብዙም ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ “የመከላከያ ሪፎርም አደናቃፊ” በሚል ማዕረጉን ተገፎ ከሠራዊቱ እንደተሰናበተ ይታወቃል።

ጄኔራሉ የአየር ኃይል አዛዥ በነበረበት ወቅት ከጦር አውሮፕላኖች እና የመለዋወጫ  ግዥዎች ጋር ተያይዞ በሙስና ንክኪ እንዳለበት እና “የድርሻህን ይዘህ ጥፋ” የተባለው ጄኔራል፤ ሲ.ኤም.ሲ ላይ “አይማ ኢንተርናሽናል” የተባለ ታዋቂ ሆቴል በስሙ ከፍቶ ንግዱን በማጧጧፍ ላይ ይገኛል። “ኢህዴን/ብአዴን ብቻውን ከሚደሰት አጫፋሪ ያግኝ” በሚል የሜ/ጀኔራል አለምሸት ደግፌ ማዕረግ ሊመለስለት እንደቻለ የመረጃ ምንጮቻችን ይገልጻሉ። ጀኔራሉም “የኦሮሞ ዘመን አሁን ነው” በሚል መኩራራት በቤተመንግሥቱ ውስጥ ሲናገር እንዳመሸ የሚገልጹት የመረጃ ምንጮቻችን ጄኔራሉ የሆቴል ንግዱ የተስማማው በመሆኑ ወታደራዊ ማዕረጉ መመለሱ ለህይወት ታሪኩ ማሟያ እንጂ ለኑሮ መደገፊያ እንደማይጠቀምበት ለህወሓትም ሆነ ለኦህዴድ አመራሮች ግልጽ መሆኑን ያስረዳሉ ነው።

ከአራተኛ ክፍል ዕውቀት ያላለፈ የትምህርት ደረጃ ላይ ከሚገኙት የህወሓት ጄኔራሎች አንጻር በተለይ (ሜ/ጄ አለምሸት ወደ ንግዱ በመመለሱ ካልፈለገው) የብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ወደ ሠራዊቱ በከፍተኛ አማካሪነት ወይም በሌላ ጠቃሚ መስክ መመለስ ለአገርም ለሠራዊቱም ጠቃሚ እንደሆነ በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ አስተያየት የሚሰጡ ይናገራሉ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: alemshet, asaminew, degefe, Full Width Top, Middle Column, tsigie

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule