• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ 

August 8, 2023 05:47 pm by Editor 1 Comment

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) ወይም ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ተብሎ በሚጠራው የወንበዴ ቡድን ስም አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ለመመስረት የቀረበውን ውሳኔ ፍርድ ቤት ውድቅ አደረገ።

በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የምርጫ ጉዳይ ክርክር ችሎት በምርጫ ቦርድና እነ’ገ/ሚካኤል ተስፋዬ መካከል የተደረገው ክርክር ውሣኔ አግኝቷል።

በህወሓት ስም የሚጠራ ለረጅም ዓመታት የሚታወቅ ፓርቲ የነበረ በመሆኑ በዚሁ ስም አዲስ ፓርቲ ማቋቋም መራጩን ያደናግራል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ስም ክልላዊ ፓርቲ ለመመሥረት የቀረበለትን የቅድመ ዕውቅና ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል።

ይህንን ተከትሎ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ያቀና ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና በእነ’ገ/ሚካኤል ተስፋዬ መካከል ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የምርጫ ጉዳይ ክርክር ችሎት የተደረገው ክርክር ውሣኔ ማግኘቱን ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

በዚህም ፍርድ ቤቱ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ተብሎ የሚጠራ ክልላዊ ፓርቲ ለመመሥረት የቅድመ ዕውቅና ፍቃድ መጠየቃቸው፤ በተጠቀሰው ስያሜ የሚጠራ ለረጅም ዓመታት የሚታወቅ ፓርቲ የነበረ በመሆኑ በዚሁ ስም አዲስ ፓርቲ ማቋቋም መራጩን የሚያደናግር በመሆኑ፤ ቦርዱ ህወሓት ተብሎ የሚጠራ ክልላዊ ፓርቲ ለመመሥረት የቀረበውን የቅድመ ዕውቅና ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ስሕተት አይደለም በሚል የቦርዱን ውሣኔ በማጽናት ውሣኔ ሰጥቷል።

እነ’ገ/ሚካኤል ተስፋዬ ሌሎች ሶስት ግለሰቦች 120 መስራች አባላት ዝርዝርን በማያያዝ ግንቦት 21 2015 ዓ.ም ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ስም አዲስ ፓርቲ ለማቋቋም ከምርጫ ቦርድ የጊዜያዊ ፈቃድ ጥያቄ አቅርበው ነበር።

የምርጫ ቦርድም ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም በሰጠው ምላሽ ህወሓት ተብሎ የሚጠራ ክልላዊ ፓርቲ ለመመሥረት የቀረበውን የቅድመ ዕውቅና ጥያቄ አልቀበለውም በማለት ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል።

በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የምርጫ ጉዳይ ክርክር ችሎት ይህንኑ የምርጫ ቦርድ ውሳኔን ስህተት የለበትም በሚል አጽንቶታል። 

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ህወሃትን ወደ ጅጋዊ ፓርቲነት ለመመለስ ጥያቄው ሲቀርብለት ህወሓትን ወደ ህጋዊ ሰውነት ለመመለስ የሚያስችል የህግ አሰራር የለም በማለት ነበር የመለሰው። ቦርዱ ህወሓትን ከህጋዊ የፖለቲካ ፖርቲነት የሰረዘው “ኃይልን መሰረት ባደረገ የአመጽ ተግባር ላይ ተሳትፏል” በሚል ምክንያት ነበር።

ቦርዱ ፖርቲው ከህጋዊ ፖርቲነት እንዲሰረዝ እና የፖርቲው ኃላፊዎችም በፖርቲው ስም እንዳይንቀሳቀሱ የሚል ውሳኔ አሳልፎ ነበር።

ትግራይ ክልልን ሲመራ የነበረው ህወሓት ከፌደራል መንግስት ጋር ያለው አለመግባባት ወደ ጦርነት ማምራቱን ተከትሎ ነበር ምርጫ ቦርድ ይህን ውሴኔ ያሳለፈው።

በህወሓት እና በፌደራል መንግስት መካከል ለሁለት አመታት የተካሄደው ጦርነት በፕሪቶሪያ የዘላቂ ተኩስ አቁም ስምምነት ሊቆም ችሏል።

ቦርዱ እንዳስታወቀው አሁን ላይ ግጭቱ በስምምነት በመፈታቱ ውሳኔው እንዲሽር ህወሓት መጠየቁን ገልጿል።

“ለቦርዱ ውሳኔ ምክንያት የሆነው ኃይልን መሰረት ያደረገ የአመጽ ተግባር አሁን ባይኖርም እንደገና ህጋዊ ሰውነቱን ለፖርቲው ለመመለስ የሚያችሉ ድንጋጌዎች በአዋጅ 1662/2011 ተደንግጎ አይገኝም” ብሏል ቦርዱ።

ምርጫ ቦርድ በዚህ ምክንያት ህወሓት ያቀረበውን የህጋዊ ሰውነት ይመለስልኝ ጥያቄ እንደማይቀበለው ገልጿል።

ህወሓት ህጋዊ ሰውነት የሚያገኘው በድጋሚ ለመመዝገብ ጥያቄ ሲያቀርብ እና ቦርዱ ሲፈቅድ ነው ብሏል። (አል አይን)

ከዚህ የቦርዱ ውሳኔ በኋላ ነበር ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት የተመራው። ሆኖም ፍርድ ቤቱ የቦርዱን ውሳኔ በማጽናት ትህነግን ሕጋዊ ሰውነት ከልክሎታል። ይህም በበርካታዎች ዘንድ የትህነግ አራተኛ ሞት ተብሏል።

የመጀመሪያው ከአራት ኪሎ ተባርሮ ሥልጣኑን ሲያጣ የሞተው የሥልጣን ሞት፤ ቀጣዩ ደግሞ ኢህአዴግ ፈርሶ ብልጽግና ሲመሠረት አልፈልግም ብሎ በወጣ ጊዜ የገጠመው የፖለቲካ ሞት፤ ከዚያም መከላከያን በሌሊት አርዶ ሞቱን ያሸተተበትና ወደ ጦርነት ገብቶ እንዳያንሰራራ ተደርጎ የከሰመበት፣ በሃሰት የገነባው ወኔው የተሰለበበት የውጊያ ዐውድ ሞት፤ ትላንት ፍርድ ቤት የወሰነበት ሕጋዊ ሞት ሆኗል። ቀጣዩና ምናልባትም የመጨረሻው ከትግራይ ሕዝብ ልብ ወጥቶ ዘላለማዊውን ሞት የሚሞትበት ይሆናል።

ይህንን የትህነግን ሥልታዊ አሟሟት የተከታተሉ እንደ ወያኔ ያለ ዘንዶ እንዲህ እየገዘገዙ ቆራርጠው ካላስወገዱት እንደ እባብ ቆዳውን ቀይሮ ስለሚመጣ አካሄዱ በዚሁ መልክ መቀጠል ያስፈልገዋል ብለዋል። በቀጣይ ወያኔን የሚያስታውሱን ሃውልቶችና መታሰቢያዎችን በሙሉ ከነርኩሰታቸው ከኢትዮጵያ ምድር ማስወገድ ወሳኝ መሆኑን አክለው ተናግረዋል። 

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Uncategorized Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. አብይ አህመድ says

    August 8, 2023 07:53 pm at 7:53 pm

    ኢህአዴግ ተዋህዶ ሥያሜውን ወደ ብልጽግና ከመቀየሩ ጋር በተያያዘ በተፈጠረ አለመተማመን ምክንያት ለሁለት ተከፍሎ ለእርስ በርስ ጦርኘታችን ምክንያት ቢሆን በስተ መጨረሻ ህወሃት በዉህደቱ ተስማምቶ የታረቀ በመሆኑ የዘበዘባችሁት በዘበዝ በጭራሽ የማይጨበጥ በሬ ወለድ ከንቱ ምኞታችሁ ነው።ኢህአዴግ አልተሸነፈም አልፈረሰም ነገር ግን ከህብረ ብሔርነት ወደ ወጥ ፓርቲነት ተለወጠ እንጂ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule