• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዲስ አበባን በፓርላማ የሚወክሏት ተመራጮች

July 11, 2021 08:05 pm by Editor 1 Comment

አዲስ አበባ ከተማ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 23 መቀመጫዎች አሏት፡፡ ሰኔ 14፤ 2013 በተካሔደው ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ፤ ከ23 የፓርላማ መቀመጫዎች ገዢው ብልጽግና ፓርቲ  በ22 የምርጫ ክልሎች ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትላንት ቅዳሜ ምሽት አስታውቋል፡፡

ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ  ያላቀረበበት ብቸኛ የአዲስ አበባ ምርጫ ክልል በሆነው ምርጫ ክልል 28 ደግሞ፤ የግል ተወዳዳሪው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ማሸነፋቸው ተገልጿል፡፡ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት  የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ናቸው፡፡

የምርጫ ውጤት

ብልጽግና ፓርቲ በከፍተኛ ውጤት፣ አብላጫውን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበርን በማግኘት አሸንፏል።

በዚህ መሰረት ብልጽግና ፓርቲ ከ436 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ 410 መቀመጫ ማግኘቱን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

  • የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አብን 5 የህዝብ ተወካች ምክር ቤት መቀመጫዎች ማግኘቱንም ቦርዱ አስታውቋል።
  • የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ደግሞ 4 የህዝብ ተወካች ምክር ቤት መቀመጫዎች ማግኘቱን ነው ቦርዱ ገልጿል።
  • የጌዲዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅትም 2 የህዝብ ተወካች ምክር ቤት መቀመጫዎችን ማግኘቱንም ነው ቦርዱ ያስታወቀው።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለክልል ም/ቤት በተደረገው ምርጫ አዲስ አበባ 138 መቀመጫ ሲኖረው ብልጽግና 138 መቀመጫዎችን አግኝቷል፡፡

ለክልል ም/ቤት 96 መቀመጫ ያለው አፋር ደግሞ ብልጽግና 51 እንዲሁም የአርጎባ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት 3 መቀመጫዎችን አግኝተዋል፡፡

294 የክልል ም/ቤት መቀመጫ ባለው አማራ 128 መቀመጫዎችን ብልጽግና ሲያገኝ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ደግሞ 13 መቀመጫዎችን አግኝቷል፡፡

ለክልል ም/ቤት 99 መቀመጫ ባለው ቤንሻንጉል ብልጽግና 22 መቀመጫዎችን ማግኝቱን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡

ድሬዳዋ 189 የም/ቤት መቀመጫ ያለው ሲሆን 189 መቀመጫ ብልጽግና አግኝቷል ተብሏል፡፡

ጋምቤላ 156 የክልል ም/ቤት መቀመጫ ያለው ሲሆን ብልጽግና 149 እንዲሁም የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ 7 መቀመጫዎችን አግኝተዋል፡፡

537 የክልል ም/ቤት መቀመጫ ባለው ኦሮሚያ ብልጽግና 513 መቀመጫዎችን  አግኝቷል፡፡

ለክልል ም/ቤት 190 መቀመጫዎች ባሉት ሲዳማ ብልጽግና 190 መቀመጫዎችን ማግኘት ችሏል፡፡

የደቡብ ክልል 291 የክልል ም/ቤት መቀመጫ ሲኖረው ብልጽግና 245፣ ኢዜማ 10 እንዲሁም የጌዴኦ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ 6 መቀመጫዎች ማግኘታውን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News, Right Column, Uncategorized Tagged With: election 2013, election 2021

Reader Interactions

Comments

  1. ዑመር ሰይድ says

    July 18, 2021 07:46 am at 7:46 am

    በጣም ጥሩ መረጃዎችን እያደረሳችሁን ነው።በርቱልን ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule