• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዲስ አበባን በፓርላማ የሚወክሏት ተመራጮች

July 11, 2021 08:05 pm by Editor 1 Comment

አዲስ አበባ ከተማ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 23 መቀመጫዎች አሏት፡፡ ሰኔ 14፤ 2013 በተካሔደው ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ፤ ከ23 የፓርላማ መቀመጫዎች ገዢው ብልጽግና ፓርቲ  በ22 የምርጫ ክልሎች ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትላንት ቅዳሜ ምሽት አስታውቋል፡፡

ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ  ያላቀረበበት ብቸኛ የአዲስ አበባ ምርጫ ክልል በሆነው ምርጫ ክልል 28 ደግሞ፤ የግል ተወዳዳሪው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ማሸነፋቸው ተገልጿል፡፡ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት  የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ናቸው፡፡

የምርጫ ውጤት

ብልጽግና ፓርቲ በከፍተኛ ውጤት፣ አብላጫውን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበርን በማግኘት አሸንፏል።

በዚህ መሰረት ብልጽግና ፓርቲ ከ436 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ 410 መቀመጫ ማግኘቱን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

  • የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አብን 5 የህዝብ ተወካች ምክር ቤት መቀመጫዎች ማግኘቱንም ቦርዱ አስታውቋል።
  • የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ደግሞ 4 የህዝብ ተወካች ምክር ቤት መቀመጫዎች ማግኘቱን ነው ቦርዱ ገልጿል።
  • የጌዲዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅትም 2 የህዝብ ተወካች ምክር ቤት መቀመጫዎችን ማግኘቱንም ነው ቦርዱ ያስታወቀው።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለክልል ም/ቤት በተደረገው ምርጫ አዲስ አበባ 138 መቀመጫ ሲኖረው ብልጽግና 138 መቀመጫዎችን አግኝቷል፡፡

ለክልል ም/ቤት 96 መቀመጫ ያለው አፋር ደግሞ ብልጽግና 51 እንዲሁም የአርጎባ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት 3 መቀመጫዎችን አግኝተዋል፡፡

294 የክልል ም/ቤት መቀመጫ ባለው አማራ 128 መቀመጫዎችን ብልጽግና ሲያገኝ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ደግሞ 13 መቀመጫዎችን አግኝቷል፡፡

ለክልል ም/ቤት 99 መቀመጫ ባለው ቤንሻንጉል ብልጽግና 22 መቀመጫዎችን ማግኝቱን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡

ድሬዳዋ 189 የም/ቤት መቀመጫ ያለው ሲሆን 189 መቀመጫ ብልጽግና አግኝቷል ተብሏል፡፡

ጋምቤላ 156 የክልል ም/ቤት መቀመጫ ያለው ሲሆን ብልጽግና 149 እንዲሁም የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ 7 መቀመጫዎችን አግኝተዋል፡፡

537 የክልል ም/ቤት መቀመጫ ባለው ኦሮሚያ ብልጽግና 513 መቀመጫዎችን  አግኝቷል፡፡

ለክልል ም/ቤት 190 መቀመጫዎች ባሉት ሲዳማ ብልጽግና 190 መቀመጫዎችን ማግኘት ችሏል፡፡

የደቡብ ክልል 291 የክልል ም/ቤት መቀመጫ ሲኖረው ብልጽግና 245፣ ኢዜማ 10 እንዲሁም የጌዴኦ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ 6 መቀመጫዎች ማግኘታውን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column, Uncategorized Tagged With: election 2013, election 2021

Reader Interactions

Comments

  1. ዑመር ሰይድ says

    July 18, 2021 07:46 am at 7:46 am

    በጣም ጥሩ መረጃዎችን እያደረሳችሁን ነው።በርቱልን ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule