የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ከስልጣን እንዲወርዱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ በመዲናዋ ካይሮና በአጎራባች ከተሞች ዛሬ (ሰኞ) ተካሄደ። በካይሮ ዳርቻ በምትገኘው የጊዛ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ሰልፈኞች የተቃውሞ ትዕይንት ያካሄዱት የፀጥታ ኃይሎችን ማስጠንቀቂያ በመጣስ ነው። ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ካሰሙት መፈክር መካከል “ሲሲ ውጣ” እና “ሕዝብ አገዛዙን መገልበጥ ይፈልጋል” ("Sisi out" and "The people want to overthrow the regime")የሚሉት የማኅበራዊ ሚዲያውን አጨናንቀውት ውለዋል። ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ከመንግሥት ተቃውሞ በላይ አንድ የፖሊስ መኪናን ያቃጠሉ ሲሆን በፖሊስ ላይ ድንጋይ የወረወሩበት ድርጊትን የሚያሳይ ቪዲዮም በማህበራዊ ሚዲያ ተለቋል። አልጀዚራ በዘገባው እንዳመለከተው የአሁኑ ተቃውሞ ከመቀስቀሱ በፊትም የፀጥታ ኃይሎች … [Read more...] about “ሕዝብ አገዛዙን መገልበጥ ይፈልጋል” የአልሲሲ ተቃዋሚዎች
Slider
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ ህገ-ወጥ ገንዘብ በቁጥጥር ሥር ዋለ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አብዱልአዚም መሀመድ እንደገለጹት፣ በክልሉ በሚገኙ 4 የተለያዩ ኬላዎች በተደረገ ፍተሻ 2,370,000 ብር በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡ በክልሉ ኩርሙክ ወረዳ ሱዳን ድንበር አካባቢ በግለሰብ ሲዘዋወር የነበረ 600 ሺህ ብር የሚሆን ገንዘብ በቁጥጥር ስር እንደዋለ ተናግረዋል፡፡ ግለሰቡ 600 ሺህ ብር በሞተር ብስክሌት ጭኖ ሲጓዝ የጸጥታ ኃይሎች ባደረጉት ፍተሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቀዋል። በቁጥጥር ስር የዋለው ተጠርጣሪው ለፖሊስ በሰጠው ቃል ገንዘቡን ለወርቅ ግዥ እያንቀሳቀስኩ ነው ማለቱን ተናግረዋል። በመተከል ዞን ጉባ ወረዳ ማንኩሽ ኬላ 300 ሺህ ብር በቁጥጥር ስር መዋሉን … [Read more...] about በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ ህገ-ወጥ ገንዘብ በቁጥጥር ሥር ዋለ
ለጌታቸው አሰፋና መሰሎቹ ክስ ምስክር ማሰማት ተጀመረ
በእነ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ በተከሰሱ በ26 የቀድሞ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች ላይ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የዐቃቤ ህግ ምስክር ማሰማት ጀመረ። በእነ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ በ26 የቀድሞ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች በተከሰሱበት በአዋጅ ከተሰጣቸው ስልጣን ውጪ ሰዎችን በመያዝና በማሰር ስልጣንን ያለ አግባብ መገልግል ወንጀል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ከመጋረጃ ጀርባ ማንነታቸው የማይገለፅ ምስክሮችን ዛሬ ማሰማት ጀምሯል። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት አጠቃላይ 22 ተከሳሾች ሲሆኑ፥ ጌታቸው አሰፋ፣ አፅበሃ ግደይ፣ አሰፋ በላይ እና ሺሻይ ልኡል በሌሉበት ነው ጉዳያቸው የታየው። ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በምስክር ጥበቃ አዋጅ 699/ 2003 መሰረት ጥበቃ የሚያስፈልጋቸው እና ማንነታቸው የማይገለፅ 29 ምስክሮችን … [Read more...] about ለጌታቸው አሰፋና መሰሎቹ ክስ ምስክር ማሰማት ተጀመረ
ሶማሌ ክልል የጦር መሣሪያ መሰብሰብ ሊጀምር ነው
የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ዋና አዛዥ ጦር መሳሪያዎችን የመሰብሰብ ዘመቻ እንደሚጀመር አስታወቁ! ትላንት (እሁድ) ከሶማሌ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ጋር ቆይታ ያደረጉት፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ዋና አዛዥ ረ/ኮሚሽነር መሀመድ አህመድ በሁሉም የሶማሌ ክልል አከባቢዎች ጦር መሳሪያዎችን የመሰብሰብ ዘመቻ እንደሚጀመር እና ከአሁን በኋላ ለአንድም የሲቪል ማህበረሰብ ትጥቅ እንደማይፈቀድላቸው አስታወቀዋል። በተጨማሪ ከመንግሥት ጦር መሳሪያ ውጭ፣ ለሲቪል ግለሰቦች ታጥቆ መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑንም ዋና አዛዥ መሀመድ አህመድ ገልፀዋል ። አክለውም ይህ የጦር መሳሪያ የመሰብሰብ ውሳኔው ለዜጎች ሰላም እና ደህንነት ተብሎ የታወጀ ውሳኔ እንደሆነ ኃላፊው አብራርተዋል። የክልሉ ፀጥታ አካላት በክልሉ ውስጥ ያለው የጦር መሳሪያ የመሰብሰብ ዘመቻ በቂ አቅምና ዝግጅትም አላቸው ያሉት … [Read more...] about ሶማሌ ክልል የጦር መሣሪያ መሰብሰብ ሊጀምር ነው
አፋር የመንግሥትንና የሕዝብን አስቸኳይ ድጋፍና እርዳታ ይሻል!
ይህን ከባድ የተፈጥሮ አደጋ በቸልታ የሚታለፍ አይደለም። አፋር የሃገራችን ዳር ድንበር ለዘመናት እየጠብቁ የቆዩ፣ የሰው ልጆችን ሁሉ በእኩልነት እና በክብር ተቀብለው የሚያስተናግዱ እንግዳ ተቀባይ እና ከሌሎች ጋር ተካፍለው መብላት ህይወታቸው የሆነ የኢትዮጵያ ውድ ህዝቦች ናቸው። እነዚህ ወገኖቻችን ባጋጠማቸው ከፍተኛ የሆነ የጎርፍ አደጋ ከ200 ሺህ ህዝብ በላይ ተፈናቅሎ የመንግስትን እና የህዝብን ድጋፍ እየጠበቁ ነው። ሰብዓዊነት ሁሉም ሊሰማው ይገባል። አንድ አካላችን ሲታመም ሁሉም አካላችን እንደሚታመም ሁሉ የአፋር ወገኖቻችን ጉዳት እና ህመም እኛንም ሊያመን ይገባል። በሌላ በኩል ፦ ጣና ሐይቅ በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩ የተነሳ ውሃው ተመልሶ በሐይቁ ዙሪያ ያሉ ቀበሌዎችን እያጥለቀለቀ ይገኛል። በዚሁ ምክንያት እስካሁን ድረስ በደንቢያ ወረዳ … [Read more...] about አፋር የመንግሥትንና የሕዝብን አስቸኳይ ድጋፍና እርዳታ ይሻል!
የሕገወጥነት ጽንፍ ሰለባዎች
ዕለተ ዓርብ ሐምሌ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. በቃሊቲ አውቶቡስ መናኸሪያ የተገኘነው ማልደን ነበር። መናኸሪያው እንደ ወትሮው ግርግር አይታይበትም። አለፍ አለፍ እያሉ ወደ መናኸሪያው የሚገቡ ሰዎችም በቀጭን ገመድ ራሳቸውን ከልለው የኮሮና ሙቀት በሚለኩ ሰዎች እየተፈተሹ ይገባሉ። ምንም ዓይነት የቅድመ ጥንቃቄ የምክር አገልግሎት ሲሰጥ ግን አላየንም። አውቶቡሱ ከመነሳቱ በፊት ረዳቱ በር ላይ የተለካውን የሰውነት የሙቀት ልኬት የተነገረንን ውጤት እየመዘገበ ወደ ውስጥ ማስገባት ጀመረ። ባስ ውስጥ ሦስት ሰዎች ሳይመረመሩ ገብተው ነበረና በግምት ሲሞላ በማየታችን ሁኔታው ትክክል እንዳልሆነ አስረድተን ተሳፋሪዎቹ ሙቀታቸውን እንዲለኩ በማድረግ ጉዞዋችንን ጀመርን። የባስ ውስጥ አቀማመጣችን ያው እንደ ከተማው ትራንስፖርት በወንበር አንድ ሰው ነው። ከእኔ በስተቀኝ ከተቀመጡት … [Read more...] about የሕገወጥነት ጽንፍ ሰለባዎች
“የፌዴራል መንግሥት በትግራይ የሆነ ዕርምጃ እወስዳለሁ ካለ ራሱ ያደርገዋል”
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2012 ዓ.ም. ምሽት በፋና ቴሌቪዥን በትግርኛ ቋንቋ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር። ከተነሱት ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል ለውጡና የትግራይ ክልል ሁኔታ፣ የድምፂ ወያነና የትግራይ ቴሌቪዥን መዘጋት፣ ምርጫን በተመለከተ፣ የኤርትራ ጉዳይና የፌዴራል መንግሥት ትግራይን ሊያጠቃ ነው ስለመባሉ ይገኙበታል። በማብራሪያቸው የተነሱ ዋና ዋና ጉዳዮች እንደሚከተለው ተጠናቅረዋል። ለውጡና የትግራይ ክልል ሁኔታ “የትግራይ ሕዝብ የማይሳተፍበት ፖለቲካ በኢትዮጵያ ይኖራል የሚል እምነት የለኝም። ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ በአሁኑ ወቅት ሦስት ችግሮች አሉ። እነዚህ ሦስት ችግሮችን በግልጽ መገንዘብ ያስፈልጋል። የመጀመርያው ችግር ከለውጥ ጋር የተያያዘ ነው። አገራችን ከለውጥ ጋር በተያያዘ ፈተና ውስጥ ነው … [Read more...] about “የፌዴራል መንግሥት በትግራይ የሆነ ዕርምጃ እወስዳለሁ ካለ ራሱ ያደርገዋል”
ህወሓት ይፍረስ፤ ዕልቂት ሰባኪዎች ለፍርድ ይቅረቡ!
“ሃጫሉን የገደሉት ነፍጠኞች ናቸው፤ መላው የኦሮሞ ህዝብ የምኒሊክን ሃውልት አፍርሰህ ወደ ቤተመንግሥት ገስግስ!” ይህንን የዘር ዕልቂት የተናገረው የዶ/ር ዐቢይ የለውጥ ቡድን እነ ጃዋር መሃመድን በቁጥጥር ሥር ከማዋሉ በፊት በሕወሃት የደም ገንዘብ የሚቀለበው ሕዝቅኤል ጋቢሣ አሜሪካ ቁጭ ብሎ ሕወሃት ባደራጀው ዲጂታል ሚድያ በመጠቀም ሲያውጅ ነበር። “በደረሰን መረጃ መሠረት፤ የሃጫሉ ሁንዴሳ ገዳዮች ነፍጠኞ ሳይሆኑ ሥልጠናና ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የመጡ ትግርኛ ተናጋሪ ኤርትራውያን ናቸው፤ እኔ በደንብ አውቃለሁ እነማን እንደገደሉት፤ ምን ዓይነት ሚሊተሪ ፐርሶኔል እንደተሳተፈም አውቃለሁ፤ ኢትዮጵያውያን እንኳን አይደሉም፤ ኤርትራውያን ናቸው" ይህን የተናገረው ደግሞ በጎጥ አስተሳሰብ እጅግ የጠበበው መርዘኛው ፀጋዬ አራርሳ ነው። ፀጋዬ አራርሣ፤ ሃገር መምራት የማይችል ደካማ ነው፤ … [Read more...] about ህወሓት ይፍረስ፤ ዕልቂት ሰባኪዎች ለፍርድ ይቅረቡ!
ኢትዮ 360 በገንዘብ ችግር ታንቄያለሁ፤ ራሴን ግምግሚያለሁና ዕርዱኝ አለ
ከየአቅጣጫው ከተለያዩ ምንጮች ገንዘብ እንደሚለገሰውና የውክልና ፕሮፓጋንዳ እንደሚሠራ ይፋ የተደረገበት ኢትዮ 360 ሚዲያ ይህንኑ ለማስተባበል የገንዘብ ችግር አንቆናል፤ ዋናው ችግሬ ብር ነው እርዱኝ ሲል ባወጣው መግለጫ የልመና ድምጹን አሰማ። በተለይ ከቅርብ ጊዜ በኋላ በውስጥ በተከሰተ መከፋፈል ምክንያት የተለያዩ ምሥጢሮች እየወጡበት የተቸገረው ኢትዮ 360 አሁን ካለው የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር ራሱን መገምገሙን በመግለጫው ጠቁሟል። ቅዳሜ ዕለት መግለጫው እንደወጣ በዲሲ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ (በተለምዶ ዲኤምቪ በሚባለው) የተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ያነጋገረችው የጎልጉል መረጃ አቀባይ እንዳለችው መግለጫው ሌላ ገንዘብ የመሰብሰቢያ ስልት ነው በማት አስተያየት ሰጪዎች መናገራቸውን ገልጻለች። “ሁሉንም እኮ እናውቃቸዋለን፤ ኮትና ከረባት አሳምረው ሲታዩ … [Read more...] about ኢትዮ 360 በገንዘብ ችግር ታንቄያለሁ፤ ራሴን ግምግሚያለሁና ዕርዱኝ አለ










