• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓትና ተላላኪዎቹ በአሸባሪነት እንዲሰየሙ ተጠየቀ

November 4, 2020 02:10 am by Editor Leave a Comment

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው።

ለአብነት ያህል፤ በአዲስ አበባ በሚኒባስ የፈነዳ ቦምብ በኦነግና በኤርትራ ላይ የተሳበበ መሆኑን የሚያስታውሱ ወገኖች ህወሓት ያኔ የፈጸመውን የአሸባሪነት ተግባር ላሁኑ እንደ ግብዓት ያነሳሉ። ሆኖም ቆየት ብሎ የታተመው የዊኪሊክስ (ሹልክ ዓምድ) ዘገባ ፍንዳታውን አቀነባብሮ ያከናወነው ህወሓት ስለመሆኑ እዚህ ላይ በዝርዝር አስረድቷል። ከበረሃ ጀምሮ ማሸበር ሙያው የሆነው ህወሓት ሥልጣን ይዞም ይህንኑ በደም የተነከረ ታሪኩን ቀጥሎበታል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትላንት (ማክሰኞ) በመደበኛነት ከያዛቸው አጀንዳዎች አስቀድሞ በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለው ግፍና ጭፍጨፋ ላይ ውይይት አድርጓል።

ምክር ቤቱ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ወለጋ ዞን ማንነትን መሰረት ያደረገው ጭፍጨፋ ላይ የተሰማውን ሀዘን በመግለፅ እና የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ መደበኛ ውይይቱን ሊያደርግ ቢያስብም አባላቱ ቅድሚያ ሊሰጥ የሚገባው የዜጎች ህይወት በመሆኑ ውይይቱ ከዚህ እንዲጀምር በሚል በጉዳዩ ላይ በስፋት ተወያይቷል።

የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤው አቶ ታገሰ ጫፎ ምክር ቤቱ አጀንዳውን ቀድሞ ቀርፆ የተዘጋጀ መሆኑን በመጥቀስ በዜጎች ላይ የተፈፀመውን ጥቃት በሚመለከት ትናንት ማምሻውን የምክር ቤቱ አመራር ምክክር አድርጎበት አስፈፃሚው አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበት ውሳኔ ላይ መደረሱን አንስተዋል።

ይህንን ተከትሎሞ በጉዳዩ ላይ የምክር ቤቱ አባላት ሀሳብ እንዲሰጡበት ተደርጓል።

በዚሁ መሰረት ህወሓትን ጨምሮ ጥቃት የሚፈፅሙ ህገ ወጥ ቡድኖችን በሽብርተኝነት በመበየን  የማያዳግም እርምጃ እንዲወሰድባቸው የሚል ሀሳብ ቀርቧል።

ምክር ቤቱ በጉዳዩ ዙሪያ በስፋት ከተወያየ በኋላ አስፈፃሚው አካል ምክር ቤት ቀርቦ ማብራሪያ እንዲሰጥ፣ ምህረት የሌለው እርምጃ እንዲወሰድ እና ችግሩ እንዳይደገም ምን መወሰን አለበት በሚለው ጉዳይ ላይ የውሳኔ ሀሳብ እንዲቀርብ አቅጣጫ አሳልፏል ሲል የዘገበው ኤፍቢሲ ነው።

ሰሞኑን ማንነትን በማተኮር የተካሄደውን ጭፍጨፋ በተመለከተ የምክር ቤት አባላት በስሜት የተናገሩበት ቪዲዮ ከዚህ በታች ቀርቧል፤

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News, Slider

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule