• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሕዝብ አገዛዙን መገልበጥ ይፈልጋል” የአልሲሲ ተቃዋሚዎች

September 21, 2020 04:07 pm by Editor Leave a Comment

የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ከስልጣን እንዲወርዱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ በመዲናዋ ካይሮና በአጎራባች ከተሞች ዛሬ (ሰኞ) ተካሄደ። በካይሮ ዳርቻ በምትገኘው የጊዛ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ሰልፈኞች የተቃውሞ ትዕይንት ያካሄዱት የፀጥታ ኃይሎችን ማስጠንቀቂያ በመጣስ ነው።

ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ካሰሙት መፈክር መካከል “ሲሲ ውጣ” እና “ሕዝብ አገዛዙን መገልበጥ ይፈልጋል” (“Sisi out” and “The people want to overthrow the regime”)የሚሉት የማኅበራዊ ሚዲያውን አጨናንቀውት ውለዋል።

ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ከመንግሥት ተቃውሞ በላይ አንድ የፖሊስ መኪናን ያቃጠሉ ሲሆን በፖሊስ ላይ ድንጋይ የወረወሩበት ድርጊትን የሚያሳይ ቪዲዮም በማህበራዊ ሚዲያ ተለቋል። አልጀዚራ በዘገባው እንዳመለከተው የአሁኑ ተቃውሞ ከመቀስቀሱ በፊትም የፀጥታ ኃይሎች በርካታ ተቃዋሚ ግብፃዊያንን ይዘው ማሰራቸው ተነግሯል።

የግብፅ መንግሥት በታላላቅ ከተሞች የፀጥታ ሀይሎችን እያሰማራ መሆኑ ተሰምቷል። በአገሪቱ የፀጥታ ሀይሎቹ በታላላቅ ከተሞች መሰማራት የጀመሩት የፕሬዝዳንት አብዱልፋታህ አል ሲሲን አስተዳደር የሚያወግዝ ተቃውሞ ሊቀሰቀስ ይችላል በሚል ስጋት እንደሆነ ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል።

ሰልፉ የተጠራው መንግሥት ያደርሰዋል ያለው የአስተዳደር ብልሹነት በማጋለጥ የሚታወቅ የቀድሞ የመከላከያ ኮንትራክተር መሐመድ ዓሊ በተባለ ግለሰብ በስደት በውጭ አገር በሚኖር እንደሆነ በመረጃው ተጠቅሷል። ባለፈው ዓመትም የግብፅ መንግስት በሙስና ውስጥ ተዘፍቆ ሀገሪቱን ለከፋ እግር እንደዳረጋት የሚያሳይ መረጃን መሐመድ ይፋ አድርጎ ነበር።

በወቅቱ የሀገሪቱ መንግሥት ተቃውሞውን ለማብረድ ቢያንስ 4ሺ ሰዎችን ማሰሩን ሚድል ኢስት ሞኒተር ዘግቧል። መሐመድ ዓሊ በተለይም በከፍተኛ ሹሞች ይፈፀማል የሚባለውን ምዝበራ በማጋለጥ ታዋቂነትን ያፈራ እንደሆነ በመረጃው ተጠቅሷል።

ዛሬ ለተቃውሞ ወደ አደባባይ የወጡ ግብጻዊያን የፕሬዝዳንት አብድል ፈታህ አልሲሲ መኖሪያ ቤትን ማቃጠላቸውን ሚድል ኢስት ሞኒተር ጨምሮ ዘግቧል። በግብፅ ስዊዝ፣ ካፈር ኤል ዳዋር፣ በናይል ዴልታ፣ ካይሮ፣ አሌክሳንድሪያ እና አስዋን ከተማ ውስጥ አልሲሲ ስልጣን እንዲለቁ የሚጠይቅ ሰልፍ  ተነስቷል።

የግብፅ ፀጥታ ኃይሎች በሰልፈኞች ላይ ያደረሱትን ጥቃት ተከትሎም አስዋን ውስጥ የሚገኘው የፕሬዚዳንቱ መኖሪያ ቤት በሰልፈኞች ተቃጥሏል ነው የተባለው። ፀረ-አል ሲሲ ተቃዋሚዎቹም በፖሊስ ላይ ድንጋይ ሲወረውሩና  የፖሊስ ሀይሉም ሲያፈገፍግ የሚያሳዩ ምስሎችም በማህበራዊ ትሥሥር ገፆች ላይ እየተዘዋወረ አንደሚገኝም ዘገባው ጠቅሷል።

በዋና ከተማዋ ካይሮም ካፌዎችን ለአድማ በከፊል ዝግ መሆናቸውንም ዘገባው ጠቅሷል።  የተቃውሞ ሰልፉም መሀመድ አሊ የተባለ አክቲቪስት በሀገሪቱ ያለውን ፍትህ መጓደል ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ እንዲያቃወምና ሀገሩን እንዲታደግ በጠራው ሰልፍ መሰረት የተካሄደ መሆኑንም ዘገባው ጠቅሷል።  መንግሥትን በመቃወም ሰልፍ እየተካሄደባቸው በሚገኙ አካባቢዎች ከፍተኛ የፀጥታ ቁጥጥር እንዳለ አልጀዚራ ዘግቧል። በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን የሚዘዋወሩ ተንቀሳቃሽ ምስሎችም ፕሬዚዳንት አል ሲ ሲ ከስልጣን ይውረዱ የሚሉ መፈክሮችን የሚያሰሙ እና ባነሮችን የያዙ ተቃዋሚዎች አሳይተዋል።

የቀድሞ የመከላከያ ኮንትራክተር መሀመድ አሊ ባለፈው ዓመት የነበረውን ተቃውሞ ለማስታወስ በትናትናው ዕለት ተመሳሳይ ተቃውሞ እንዲካሄድ ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ ነው ከፍተኛ የፀጥታ ቁጥጥር እየተደረገ የሚገኘው።

በተመሳሳይ የጸጥታ ኃይሎቹ  ከተቃውሞ ጋር ተያይዞ ታዋቂ ፖለቲከኞች እና አክትቪስቶችን ማሰራቸው ተነግሯል። እንዲሁም ተቃውሞ በበረታባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ የካፌ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲዘጉ መደረጉም ታውቋል። ባለፈው ዓመት ባልተለመደ ሁኔታ በሺህዎች የሚቆጠሩ ግብፃዊያን ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ከስልጣን እንዲለቁ ለመጠየቀ ተቃውሞ ሰልፍ ባካሄዱበት ጊዜ መንግሥት ተቃውሞውን ለመቆጣጠር ከ2 ሺህ 300 በላይ ሰዎች ማሰሩ መረጃዎች  አመልክተዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, News, Slider Tagged With: al sisi, Egypt, protest, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule