• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሕዝብ አገዛዙን መገልበጥ ይፈልጋል” የአልሲሲ ተቃዋሚዎች

September 21, 2020 04:07 pm by Editor Leave a Comment

የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ከስልጣን እንዲወርዱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ በመዲናዋ ካይሮና በአጎራባች ከተሞች ዛሬ (ሰኞ) ተካሄደ። በካይሮ ዳርቻ በምትገኘው የጊዛ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ሰልፈኞች የተቃውሞ ትዕይንት ያካሄዱት የፀጥታ ኃይሎችን ማስጠንቀቂያ በመጣስ ነው።

ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ካሰሙት መፈክር መካከል “ሲሲ ውጣ” እና “ሕዝብ አገዛዙን መገልበጥ ይፈልጋል” (“Sisi out” and “The people want to overthrow the regime”)የሚሉት የማኅበራዊ ሚዲያውን አጨናንቀውት ውለዋል።

ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ከመንግሥት ተቃውሞ በላይ አንድ የፖሊስ መኪናን ያቃጠሉ ሲሆን በፖሊስ ላይ ድንጋይ የወረወሩበት ድርጊትን የሚያሳይ ቪዲዮም በማህበራዊ ሚዲያ ተለቋል። አልጀዚራ በዘገባው እንዳመለከተው የአሁኑ ተቃውሞ ከመቀስቀሱ በፊትም የፀጥታ ኃይሎች በርካታ ተቃዋሚ ግብፃዊያንን ይዘው ማሰራቸው ተነግሯል።

የግብፅ መንግሥት በታላላቅ ከተሞች የፀጥታ ሀይሎችን እያሰማራ መሆኑ ተሰምቷል። በአገሪቱ የፀጥታ ሀይሎቹ በታላላቅ ከተሞች መሰማራት የጀመሩት የፕሬዝዳንት አብዱልፋታህ አል ሲሲን አስተዳደር የሚያወግዝ ተቃውሞ ሊቀሰቀስ ይችላል በሚል ስጋት እንደሆነ ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል።

ሰልፉ የተጠራው መንግሥት ያደርሰዋል ያለው የአስተዳደር ብልሹነት በማጋለጥ የሚታወቅ የቀድሞ የመከላከያ ኮንትራክተር መሐመድ ዓሊ በተባለ ግለሰብ በስደት በውጭ አገር በሚኖር እንደሆነ በመረጃው ተጠቅሷል። ባለፈው ዓመትም የግብፅ መንግስት በሙስና ውስጥ ተዘፍቆ ሀገሪቱን ለከፋ እግር እንደዳረጋት የሚያሳይ መረጃን መሐመድ ይፋ አድርጎ ነበር።

በወቅቱ የሀገሪቱ መንግሥት ተቃውሞውን ለማብረድ ቢያንስ 4ሺ ሰዎችን ማሰሩን ሚድል ኢስት ሞኒተር ዘግቧል። መሐመድ ዓሊ በተለይም በከፍተኛ ሹሞች ይፈፀማል የሚባለውን ምዝበራ በማጋለጥ ታዋቂነትን ያፈራ እንደሆነ በመረጃው ተጠቅሷል።

ዛሬ ለተቃውሞ ወደ አደባባይ የወጡ ግብጻዊያን የፕሬዝዳንት አብድል ፈታህ አልሲሲ መኖሪያ ቤትን ማቃጠላቸውን ሚድል ኢስት ሞኒተር ጨምሮ ዘግቧል። በግብፅ ስዊዝ፣ ካፈር ኤል ዳዋር፣ በናይል ዴልታ፣ ካይሮ፣ አሌክሳንድሪያ እና አስዋን ከተማ ውስጥ አልሲሲ ስልጣን እንዲለቁ የሚጠይቅ ሰልፍ  ተነስቷል።

የግብፅ ፀጥታ ኃይሎች በሰልፈኞች ላይ ያደረሱትን ጥቃት ተከትሎም አስዋን ውስጥ የሚገኘው የፕሬዚዳንቱ መኖሪያ ቤት በሰልፈኞች ተቃጥሏል ነው የተባለው። ፀረ-አል ሲሲ ተቃዋሚዎቹም በፖሊስ ላይ ድንጋይ ሲወረውሩና  የፖሊስ ሀይሉም ሲያፈገፍግ የሚያሳዩ ምስሎችም በማህበራዊ ትሥሥር ገፆች ላይ እየተዘዋወረ አንደሚገኝም ዘገባው ጠቅሷል።

በዋና ከተማዋ ካይሮም ካፌዎችን ለአድማ በከፊል ዝግ መሆናቸውንም ዘገባው ጠቅሷል።  የተቃውሞ ሰልፉም መሀመድ አሊ የተባለ አክቲቪስት በሀገሪቱ ያለውን ፍትህ መጓደል ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ እንዲያቃወምና ሀገሩን እንዲታደግ በጠራው ሰልፍ መሰረት የተካሄደ መሆኑንም ዘገባው ጠቅሷል።  መንግሥትን በመቃወም ሰልፍ እየተካሄደባቸው በሚገኙ አካባቢዎች ከፍተኛ የፀጥታ ቁጥጥር እንዳለ አልጀዚራ ዘግቧል። በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን የሚዘዋወሩ ተንቀሳቃሽ ምስሎችም ፕሬዚዳንት አል ሲ ሲ ከስልጣን ይውረዱ የሚሉ መፈክሮችን የሚያሰሙ እና ባነሮችን የያዙ ተቃዋሚዎች አሳይተዋል።

የቀድሞ የመከላከያ ኮንትራክተር መሀመድ አሊ ባለፈው ዓመት የነበረውን ተቃውሞ ለማስታወስ በትናትናው ዕለት ተመሳሳይ ተቃውሞ እንዲካሄድ ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ ነው ከፍተኛ የፀጥታ ቁጥጥር እየተደረገ የሚገኘው።

በተመሳሳይ የጸጥታ ኃይሎቹ  ከተቃውሞ ጋር ተያይዞ ታዋቂ ፖለቲከኞች እና አክትቪስቶችን ማሰራቸው ተነግሯል። እንዲሁም ተቃውሞ በበረታባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ የካፌ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲዘጉ መደረጉም ታውቋል። ባለፈው ዓመት ባልተለመደ ሁኔታ በሺህዎች የሚቆጠሩ ግብፃዊያን ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ከስልጣን እንዲለቁ ለመጠየቀ ተቃውሞ ሰልፍ ባካሄዱበት ጊዜ መንግሥት ተቃውሞውን ለመቆጣጠር ከ2 ሺህ 300 በላይ ሰዎች ማሰሩ መረጃዎች  አመልክተዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Slider Tagged With: al sisi, Egypt, protest, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule