• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሕዝብ አገዛዙን መገልበጥ ይፈልጋል” የአልሲሲ ተቃዋሚዎች

September 21, 2020 04:07 pm by Editor Leave a Comment

የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ከስልጣን እንዲወርዱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ በመዲናዋ ካይሮና በአጎራባች ከተሞች ዛሬ (ሰኞ) ተካሄደ። በካይሮ ዳርቻ በምትገኘው የጊዛ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ሰልፈኞች የተቃውሞ ትዕይንት ያካሄዱት የፀጥታ ኃይሎችን ማስጠንቀቂያ በመጣስ ነው።

ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ካሰሙት መፈክር መካከል “ሲሲ ውጣ” እና “ሕዝብ አገዛዙን መገልበጥ ይፈልጋል” (“Sisi out” and “The people want to overthrow the regime”)የሚሉት የማኅበራዊ ሚዲያውን አጨናንቀውት ውለዋል።

ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ከመንግሥት ተቃውሞ በላይ አንድ የፖሊስ መኪናን ያቃጠሉ ሲሆን በፖሊስ ላይ ድንጋይ የወረወሩበት ድርጊትን የሚያሳይ ቪዲዮም በማህበራዊ ሚዲያ ተለቋል። አልጀዚራ በዘገባው እንዳመለከተው የአሁኑ ተቃውሞ ከመቀስቀሱ በፊትም የፀጥታ ኃይሎች በርካታ ተቃዋሚ ግብፃዊያንን ይዘው ማሰራቸው ተነግሯል።

የግብፅ መንግሥት በታላላቅ ከተሞች የፀጥታ ሀይሎችን እያሰማራ መሆኑ ተሰምቷል። በአገሪቱ የፀጥታ ሀይሎቹ በታላላቅ ከተሞች መሰማራት የጀመሩት የፕሬዝዳንት አብዱልፋታህ አል ሲሲን አስተዳደር የሚያወግዝ ተቃውሞ ሊቀሰቀስ ይችላል በሚል ስጋት እንደሆነ ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል።

ሰልፉ የተጠራው መንግሥት ያደርሰዋል ያለው የአስተዳደር ብልሹነት በማጋለጥ የሚታወቅ የቀድሞ የመከላከያ ኮንትራክተር መሐመድ ዓሊ በተባለ ግለሰብ በስደት በውጭ አገር በሚኖር እንደሆነ በመረጃው ተጠቅሷል። ባለፈው ዓመትም የግብፅ መንግስት በሙስና ውስጥ ተዘፍቆ ሀገሪቱን ለከፋ እግር እንደዳረጋት የሚያሳይ መረጃን መሐመድ ይፋ አድርጎ ነበር።

በወቅቱ የሀገሪቱ መንግሥት ተቃውሞውን ለማብረድ ቢያንስ 4ሺ ሰዎችን ማሰሩን ሚድል ኢስት ሞኒተር ዘግቧል። መሐመድ ዓሊ በተለይም በከፍተኛ ሹሞች ይፈፀማል የሚባለውን ምዝበራ በማጋለጥ ታዋቂነትን ያፈራ እንደሆነ በመረጃው ተጠቅሷል።

ዛሬ ለተቃውሞ ወደ አደባባይ የወጡ ግብጻዊያን የፕሬዝዳንት አብድል ፈታህ አልሲሲ መኖሪያ ቤትን ማቃጠላቸውን ሚድል ኢስት ሞኒተር ጨምሮ ዘግቧል። በግብፅ ስዊዝ፣ ካፈር ኤል ዳዋር፣ በናይል ዴልታ፣ ካይሮ፣ አሌክሳንድሪያ እና አስዋን ከተማ ውስጥ አልሲሲ ስልጣን እንዲለቁ የሚጠይቅ ሰልፍ  ተነስቷል።

የግብፅ ፀጥታ ኃይሎች በሰልፈኞች ላይ ያደረሱትን ጥቃት ተከትሎም አስዋን ውስጥ የሚገኘው የፕሬዚዳንቱ መኖሪያ ቤት በሰልፈኞች ተቃጥሏል ነው የተባለው። ፀረ-አል ሲሲ ተቃዋሚዎቹም በፖሊስ ላይ ድንጋይ ሲወረውሩና  የፖሊስ ሀይሉም ሲያፈገፍግ የሚያሳዩ ምስሎችም በማህበራዊ ትሥሥር ገፆች ላይ እየተዘዋወረ አንደሚገኝም ዘገባው ጠቅሷል።

በዋና ከተማዋ ካይሮም ካፌዎችን ለአድማ በከፊል ዝግ መሆናቸውንም ዘገባው ጠቅሷል።  የተቃውሞ ሰልፉም መሀመድ አሊ የተባለ አክቲቪስት በሀገሪቱ ያለውን ፍትህ መጓደል ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ እንዲያቃወምና ሀገሩን እንዲታደግ በጠራው ሰልፍ መሰረት የተካሄደ መሆኑንም ዘገባው ጠቅሷል።  መንግሥትን በመቃወም ሰልፍ እየተካሄደባቸው በሚገኙ አካባቢዎች ከፍተኛ የፀጥታ ቁጥጥር እንዳለ አልጀዚራ ዘግቧል። በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን የሚዘዋወሩ ተንቀሳቃሽ ምስሎችም ፕሬዚዳንት አል ሲ ሲ ከስልጣን ይውረዱ የሚሉ መፈክሮችን የሚያሰሙ እና ባነሮችን የያዙ ተቃዋሚዎች አሳይተዋል።

የቀድሞ የመከላከያ ኮንትራክተር መሀመድ አሊ ባለፈው ዓመት የነበረውን ተቃውሞ ለማስታወስ በትናትናው ዕለት ተመሳሳይ ተቃውሞ እንዲካሄድ ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ ነው ከፍተኛ የፀጥታ ቁጥጥር እየተደረገ የሚገኘው።

በተመሳሳይ የጸጥታ ኃይሎቹ  ከተቃውሞ ጋር ተያይዞ ታዋቂ ፖለቲከኞች እና አክትቪስቶችን ማሰራቸው ተነግሯል። እንዲሁም ተቃውሞ በበረታባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ የካፌ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲዘጉ መደረጉም ታውቋል። ባለፈው ዓመት ባልተለመደ ሁኔታ በሺህዎች የሚቆጠሩ ግብፃዊያን ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ከስልጣን እንዲለቁ ለመጠየቀ ተቃውሞ ሰልፍ ባካሄዱበት ጊዜ መንግሥት ተቃውሞውን ለመቆጣጠር ከ2 ሺህ 300 በላይ ሰዎች ማሰሩ መረጃዎች  አመልክተዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Slider Tagged With: al sisi, Egypt, protest, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule