በ10 ዓመቱ ወደ ውጪ ሸሽቷል የተባለው ሀብት ከባለፈው 44 ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ10 ዓመቱ እንደሚበልጥ የጥናት ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ ለሸገር ነግረዋል፡፡ በጉዳዩ የማክሮ ኢኮኖሚ ተንታኝና ተመራማሪው ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ ከሸገር ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት፦በኢትዮጵያ በ10 ዓመት ውስጥ ብቻ 45 ቢሊየን ዶላር ከሀገር መውጣቱን ገልጸው ይህም የ10 ዓመቱን ወደ ውጪ የሸሸ ኃብት ከባለፈው 44 ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ10 ዓመቱ እንደሚበልጥ ተነግረዋል። የማክሮ ኢኮኖሚ ተመራማሪው በ44 ዓመት ውስጥ ከኢትዮጵያ የሸሸው ሀብት 31 ቢሊየን ዶላር ነው የተባለ ሲሆን፣ ይህም በጥናት ተረጋግጦ መታተሙን አንስተዋል፡፡ በተጨማሪም በከተማው ውስጥ ከመደበኛው ሥርዓት ውጪም ከፍተኛ ዶላር እንደሚገላበጥ አስረድተዋል። ለመሆኑ ዋናው ምክንያት … [Read more...] about በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል
illegal money
ሳሚ ዶላር አንዱ ነው፤ ሌሎቹስ ዶላር አጣቢዎች? ምነው ዝም ተባሉ?
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማና ባደረገው ብርቱ ክትትል በህገ-ወጥ መንገድ ከ5.1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ ከ25 ግብረ-አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራባቸው መሆኑን ገለፀ፡፡ ዜናውን የሰሙ “በነካ እጃችሁ ወኪሎቹ ጋር ጎራ በሉ” ሲሉ ተደምጠዋል። በወንጀሉ የተጠረጠረው ሳሙኤል እጓለ አለሙ በቅፅል ስሙ ሳሚ ዶላር የሚባል ሲሆን ነዋሪነቱን በአዲስ አበባ ከተማ በማድረግ ወደ አሜሪካን ሀገር በተደጋጋሚ የሚመላለስ የኤሌክትሪክ መሳሪያዎች፣ የቤት እና የቢሮ እቃዎችእንዲሁም ተዛማጅ መገልገያዎች የችርቻሮ ንግድ ፍቃድን ሽፋን በማድረግ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ተጠርጥሮ በራሱና ዮዲት እጓለ አለሙ ከተባለች እህቱ ጋር በመሆን በስማቸው በተለያዩ ባንኮች … [Read more...] about ሳሚ ዶላር አንዱ ነው፤ ሌሎቹስ ዶላር አጣቢዎች? ምነው ዝም ተባሉ?
በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ በተሰማሩ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስና ከኦሮሚያ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ በተሰማሩ ግለሰቦችና ድርጅቶቻቸው ላይ ጥናትን መሰረት ያደረገ እርምጃ መወሰዱን አስታውቋል፡፡ አገልግሎቱ ለሚዲያ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ባለፉት ሁለት ወራት በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች ምንዛሪ ዙሪያ ሰፊና ጥልቀት ያለው ጥናት ሲካሄድ እንደነበር አመልክቷል፡፡ ችግሩ በጥናት ከተለየ በኋላም መረጃዎችንና ማስረጃዎችን መነሻ በማድረግ በተከናወነው ክትትል በሕገወጥ የውጭ ምንዛሪ ላይ ተሳታፊ የነበሩ 48 ግለሰቦችና ከፍተኛ መጠን ያላቸው የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች እንዲሁም ከድርጊቱ ጋር የተያያዙ የባንክ ደብተሮችና ልዩ ልዩ ሰነዶች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል ነው የተባለው፡፡ በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች … [Read more...] about በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ በተሰማሩ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው
ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ
በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ ለአሸባሪው ሕወሀት ቡድን ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር መያዙን የአስተዳደሩ ሰላምና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። "ከአሸባሪው ሕወሀት ቡድን የጥፋት ተልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 20 ሰርጎ ገቦች” በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ተናግረዋል። የጽሕፈት ቤቱ ኀላፊ አቶ ሸጌ መንግስቴ ከግንቦት 12 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በተደረገ የተቀናጀ ጥረትም ለሕወሀት የሽብር ቡድን ሊደርስ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር መያዙን ገልጸዋል። ገንዘቡን ለሽብር ቡድኑ ሊያደርሱ የነበሩ 20 ተጠርጣሪዎች በጸጥታ ኀይሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን አመልክተዋል። በሌላ በኩል “ከአሸባሪው ሕወሓት ቡድን የጥፋት ተልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 20 ሰርጎ ገቦች” በከተማ አስተዳደሩ በቁጥጥር ስር … [Read more...] about ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ
በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ
አንድ የውጪ ሀገር ዜግነት ባለው ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ብርበራ ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላር እና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። ግለሰቡ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው 24 ኮንዶሚኒየም ጀርባ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለ 3 ወለል ፎቅ ተከራይቶ የሚኖር መሆኑን ገልጿል። ተጠርጣሪው ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ አገር ዜጎችን እየተቀበለ በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ የተለያዩ ህገ ወጥ ተግባራትን ሲፈጽም እንደነበር ከህብረተሰቡ ጥቆማ ማግኘቱንም ነው የገለጸው። ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ፤ጥቆማውን መነሻ በማድረግ የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ተቀናጅተው ባደረጉት ክትትል ግንቦት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በግለሰቡ መኖሪያ ቤት በተደረገ ፍተሻ በመኝታ ክፍል ውስጥ የተገኘ 5 ሺህ … [Read more...] about በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ
በሰባት ወር ውስጥ ከ2.3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ በሕጋዊ መንገድ በዳያስፖራው ወደ አገር ቤት ተልኳል
ዳያስፖራው በ2014 ዓ.ም በጀት ዓመት ሰባት ወራት ወራት ከ2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ (ሬሚታንስ) በሕጋዊ መንገድ ወደ አገር ቤት መላኩን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ አስታወቀ። በ2014 ዓ.ም በጀት ዓመት ሰባት ወራት ዳያስፖራው 2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ወደ አገር ቤት በሕጋዊ መንገድ እንዲልክ ታቅዶ 2 ነጥብ 35 ቢሊዮን ዶላር መላኩን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ለኢዜአ በላከው መግለጫ አስታውቋል። በበጀት ዓመቱም አራት ቢሊዮን ዶላር ከሬሚታንስ ለመሰብሰብ መታቀዱን አመልክቷል። በተያያዘም በ2014 ዓ.ም በጀት ዓመት ሰባት ወራት 4 ሺህ 83 የዳያስፖራ አባላት በአገር ውስጥ በሚገኙ ባንኮች 4 ሚሊዮን 953 ሺህ 333 ዶላር ተቀማጭ እንዲያደርጉ ታቅዶ፤4 ሺህ 7 ዳያስፖራዎች ከ3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ተቀማጭ ማድረጋቸውን ገልጿል። ዳያስፖራው … [Read more...] about በሰባት ወር ውስጥ ከ2.3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ በሕጋዊ መንገድ በዳያስፖራው ወደ አገር ቤት ተልኳል
የተለያዩ ሀገራትን የገንዘብ ኖቶች ለማባዛት በዝግጅት ላይ የነበሩ የዉጭ ሀገር ዜጎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
አንድ ካሜሩናዊ እና አንድ ኮቲዲቫራዊ ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች በጋራ በመሆን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 አማዶ ፔንሲኦን ውስጥ እና በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አዲስ ብራይት ፔንሲኦን ውስጥ ነዉ የኢትዮጵያና የተለያዪ ሀገራት የገንዘብ ኖቶችን በማዘጋጀት ላይ እያሉ በቁጥጥር ስር ዉለዋል፡፡ የግለሰቦቹን ህገወጥ እንቅስቃሴ ሲከታተል የነበረዉ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ተጠርጣሪዎቹን ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጥቆማ በመስጠት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ አድርጓል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ሲዉሉ 107,330 ትክክለኛ የኢትዮጵያ ብሮች ፣ የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች፣ባለ 200 በርካታ ፎርጅድ የኢትዮጵያ ብሮች፣ ዱቄት መሳይ ኬሚካል፣ ፈሳሽ ኬሚካሎች፣ ከተር ወይም የወረቀት መቁረጫ፣ … [Read more...] about የተለያዩ ሀገራትን የገንዘብ ኖቶች ለማባዛት በዝግጅት ላይ የነበሩ የዉጭ ሀገር ዜጎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
34 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ
34 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር አዉሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። ተጠርጣሪው ግለሰብ በጥቁር ፌስታል የተጠቀለለ ነገር ይዞ ሲንቀሳቀስ መደበኛ የወንጀል መከላከል ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተነስቷል፡፡ ፖሊሶቹ ባደረባቸው ጥርጣሬ ግለሰቡን ሲፈትሹት 34 ሺህ የአሜርካ ዶላር ይዞ በህገ ወጥ መንገድ ሲያዘዋውር በመገኘቱ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት ነው ተብሏል፡፡ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በአዲስ አበባ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሲሆን የኑሮ ውድነት እንዲባባስ እና መንግስት ማግኘት ያለበትን ገቢ እንዲያጣ እያደረገ ይገኛል፡፡ ወንጀል ፈፃሚዎች እና ህገ-ወጥ ተግባራት ላይ የሚሳተፉ አካላት የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ህግን በጣሰ መልኩ እየተንቀሳቀሱ … [Read more...] about 34 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ
በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 110 ሺህ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ዋለ
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በተደረገ ክትትል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 1 መቶ 10 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረው ዶላር የተያዘው ሚያዚያ 28 ለ29 አጥቢያ 2013 ዓ/ም በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ላምበረት መናኸሪያ ግቢ ውስጥ ከለሊቱ 10 ሰዓት ገደማ ነው፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ ሃረር ሊጓዙ የተዘጋጁ ሁለት ተጠርጣሪዎች በያዙት ሻንጣ ላይ በተደረገ ፍተሻ በጥቁር ላስቲክ የተጠቀለለ 110 ሺህ የአሜሪካ ዶላር መገኘቱን ፖሊስ ያስታወቀው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ (ኢብኮ) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 110 ሺህ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ዋለ
ግምታቸው 14 ሚሊዮን ብር የሚጠጉ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ
በተለያዩ የጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያዎችና ኬላዎች ከ13 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ልዩ ልዩ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ሥር መዋሉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ። የተያዙት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት ሳይፈፀምበት ከመስከረም 4 እስከ 9/2013 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል። ሚኒስቴሩ እንደገለጸው ወደ ሀገር ሊገባ የነበረ ማሽላና ስንዴ፣ ወደ አዲስ አበባ ሲጓጓዝ የነበረ ሲጋራ፣ በሕዝብ ማመላሻ ሚኒባስ ሲጓጓዝ የነበረ የሽጉጥ ጥይት፣ በጭነት ተሸከርካሪ ሲጓጓዝ የነበረ የክላሽ ጥይትና የሞባይል ስልኮች ይገኙበታል። በተጨማሪም ከሀገር ሊወጣ ሲሉ የተያዙ የቁም ከብቶች፣ የብር ጌጣጌጥ፣ የአሜሪካ ዶላርን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች፣ ልባሽና አዳዲስ አልባሳት ይገኙበታል። የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ … [Read more...] about ግምታቸው 14 ሚሊዮን ብር የሚጠጉ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ