• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሳሚ ዶላር አንዱ ነው፤ ሌሎቹስ ዶላር አጣቢዎች? ምነው ዝም ተባሉ?

October 28, 2022 04:04 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማና ባደረገው ብርቱ ክትትል በህገ-ወጥ መንገድ ከ5.1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ ከ25 ግብረ-አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራባቸው መሆኑን ገለፀ፡፡ ዜናውን የሰሙ “በነካ እጃችሁ ወኪሎቹ ጋር ጎራ በሉ” ሲሉ ተደምጠዋል።

በወንጀሉ የተጠረጠረው ሳሙኤል እጓለ አለሙ በቅፅል ስሙ ሳሚ ዶላር የሚባል ሲሆን ነዋሪነቱን በአዲስ አበባ ከተማ በማድረግ ወደ አሜሪካን ሀገር በተደጋጋሚ የሚመላለስ የኤሌክትሪክ መሳሪያዎች፣ የቤት እና የቢሮ እቃዎች
እንዲሁም ተዛማጅ መገልገያዎች የችርቻሮ ንግድ ፍቃድን ሽፋን በማድረግ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ተጠርጥሮ በራሱና ዮዲት እጓለ አለሙ ከተባለች እህቱ ጋር በመሆን በስማቸው በተለያዩ ባንኮች በከፈቷቸው ሃያ አምስት የባንክ አካውንቶች በአንድ ዓመት ውስጥ ከ247 ሚሊየን ብር (ሁለት መቶ አርባ ሰባት ሚሊየን ብር) በላይ ማንቀሳቀሳቸውን ፖሊስ ደርሶባቸው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ግለሰቡ ከሃያ አምስቱ የወንጀል ግብረ-አበሮቹ ጋር በመሆን በህገ-ወጥ መንገድ ከ5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅሱ እንደነበር በቅድመ ምርመራ ተደርሶባቸዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በሕገ-ወጥ የውጭ ሀገር የገንዘብ ዝውውር፣ በግብር ስወራ ወንጀል እና ከህወሃት የሽብር ቡድን ጋር የግንኙነት መረብ በመፍጠር ከፍተኛ ገንዘብ ሲያዘዋውሩ እንደነበር ተጠርጥረው ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በአጠቃላይ በአንድ ዓመት ውስጥ 5,248,000,000 (ከ5 ነጥብ 1 ቢሊዮን) ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲያንቀሳቅሱ እንደነበር ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ደርሶባቸዋል ሲል የዘገበው የፌዴራል ፖሊስ ነው።

በተያያዘ ይህን ዜና የሰሙ ራሳቸውን “ባለሃብት” የሚባሉትን፣ ሰው ግን በተለምዶ “ወኪል” እያለ የሚጠቋቆምባቸው በተመሳሳይ ስራ የተሰማሩ ስለመሆናቸው አስታውቀዋል። አቀባባዮቹም እነማ እንደሆኑ ስውር ባለመሆኑ መንግስት በነካ እጁ ጎራ ይበል ሲል ጥቆማ ሰጥተዋል። ዱባይ ላይ ሃብት የከመሩትና እግራቸው አዲስ አበባ የሆነውን፣ ለራሳቸው የውጭ ድርጅት በራሳቸው የአገር ቤት ድርጅት ኤል ሲል (LC) እየከፈቱ የሚመዘብሩት በደንብ ስለሚታወቁ መንግስት ዙሩን እንዲያከረው አሳስበዋል።

አሁን ላይ የውጭ ብር መንዛሪዎች አዲስ አበባ ዙሪያና ቅርብ በሆኑ ከተሞች የሚኖሩ እንድ ፍሬ ልጆችን በመቅጠር ነው የሚያሰሩት። በስማቸው ተያዥ አድርገው ገንዘብ በማስገባት በጥቁር ለሚመነዘርላቸው አካላት በአድራሽነትና አስተላላፊነት በወር እስከ 30 ሺህ ብር እንደሚከፈላቸው ብር ተልኮለት የተቀበል ዳያስፖራ ብሩን ከሰጥችው ልጅ መረጃ ማግኘቱን አመልካቶ ነው አሰራሩን ያስታወቀው።

አብዛኞቹ በስም የሚታወቁ የድርጅት ባለ ቤቶችና ሪል ስቴት ስር የሚንቀሳቀሱ በውጭ ምንዛሬ አጠባው ዋና ፊት አውራሪ መሆናቸውን ጥቆማ የሰጡት አመልክተዋል።

ሪልስቴ ዙሪያ ያሉ አብዛኞቹ ከመሬት ጋር በተያያዘ የሚያከማቹትን ሃብት ወደ ውጭ ስለሚያሸሹና በውክልና ድርጅቱን ላቆሙላቸው ዛሬ ላይ ሃብት የሚያስተላለፉትም በውጭ ምንዛሬ ብቻ በመሆኑ ዶላሩን እየለቀሙ ኑሮ እንዲግል፣ ህዝብ እንዲማረርና መንግስት ላይ እንዲነሳ ኢኮኖሚው ላይ ሚስማር የሚመቱት መሆናቸውን ጠቋሚዎቹ ስም ዘርዝረው ልከዋል። ሆኖም አዘግይተነዋል። ዶላር የሚዛወርባቸውን ቤቶችና እናውቃቸዋለን ያሉትን ተሽከርካሪዎች ሳይቀር ጠቁመዋል።

አብዛኞች እንደሚሉት በዚህ ሌብነት የተሰማሩት ቀደም ብለው ከትህነግ ጋር አብረው ሲነገዱና በውክልና “ምስለኔ ሃብታም” የሚባሉት ናቸው። ንብረት በተጋነነ ብር በመግዛት በቋሚ የወኪሎቻቸውን ብር የቻሉትን በውጭ ምንዛሬ፣ ያልቻሉትን በአገር ውስጥ በቋሚ ንብረት ላይ በማስቀመጥ ደሃው ቤት እንዳይገዛ፣ መሬት ወስዶ ጎጆ እንዳይቀይስ ዋጋውን እንዳናሩበት መረጃውን የላኩት አመልክተዋል። መንግስት ቆርጦና ወስኖ እነዚህ አካላት ላይ ከዘመተ የመሬትና የቤት ዋጋ በቅጽበት እንደሚሽቆለቆል በዕምነት ተናግረዋል።

መንግስት በአዲሱ ዓመት ሌብነት ላይ እንደሚዘምት፣ ዘመቻውንም ለመጀመር ዝግጅት ላይ እንዳለ ዳግም ወረራ መቀስቀሱ ይታወሳል። የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ታዬ ደንደአ “ሌባ ሊመነጠር ሲል ጦርነት መክፈት ምንን ለማሰናከል ታስቦ እንደሆነ ይታወቃል። ሁሉም ጎን ለጎን ይሄዳል” ማለታቸው ይታወሳል። (Ethio12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, illegal money, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule