• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሳሚ ዶላር አንዱ ነው፤ ሌሎቹስ ዶላር አጣቢዎች? ምነው ዝም ተባሉ?

October 28, 2022 04:04 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማና ባደረገው ብርቱ ክትትል በህገ-ወጥ መንገድ ከ5.1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ ከ25 ግብረ-አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራባቸው መሆኑን ገለፀ፡፡ ዜናውን የሰሙ “በነካ እጃችሁ ወኪሎቹ ጋር ጎራ በሉ” ሲሉ ተደምጠዋል።

በወንጀሉ የተጠረጠረው ሳሙኤል እጓለ አለሙ በቅፅል ስሙ ሳሚ ዶላር የሚባል ሲሆን ነዋሪነቱን በአዲስ አበባ ከተማ በማድረግ ወደ አሜሪካን ሀገር በተደጋጋሚ የሚመላለስ የኤሌክትሪክ መሳሪያዎች፣ የቤት እና የቢሮ እቃዎች
እንዲሁም ተዛማጅ መገልገያዎች የችርቻሮ ንግድ ፍቃድን ሽፋን በማድረግ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ተጠርጥሮ በራሱና ዮዲት እጓለ አለሙ ከተባለች እህቱ ጋር በመሆን በስማቸው በተለያዩ ባንኮች በከፈቷቸው ሃያ አምስት የባንክ አካውንቶች በአንድ ዓመት ውስጥ ከ247 ሚሊየን ብር (ሁለት መቶ አርባ ሰባት ሚሊየን ብር) በላይ ማንቀሳቀሳቸውን ፖሊስ ደርሶባቸው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ግለሰቡ ከሃያ አምስቱ የወንጀል ግብረ-አበሮቹ ጋር በመሆን በህገ-ወጥ መንገድ ከ5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅሱ እንደነበር በቅድመ ምርመራ ተደርሶባቸዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በሕገ-ወጥ የውጭ ሀገር የገንዘብ ዝውውር፣ በግብር ስወራ ወንጀል እና ከህወሃት የሽብር ቡድን ጋር የግንኙነት መረብ በመፍጠር ከፍተኛ ገንዘብ ሲያዘዋውሩ እንደነበር ተጠርጥረው ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በአጠቃላይ በአንድ ዓመት ውስጥ 5,248,000,000 (ከ5 ነጥብ 1 ቢሊዮን) ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲያንቀሳቅሱ እንደነበር ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ደርሶባቸዋል ሲል የዘገበው የፌዴራል ፖሊስ ነው።

በተያያዘ ይህን ዜና የሰሙ ራሳቸውን “ባለሃብት” የሚባሉትን፣ ሰው ግን በተለምዶ “ወኪል” እያለ የሚጠቋቆምባቸው በተመሳሳይ ስራ የተሰማሩ ስለመሆናቸው አስታውቀዋል። አቀባባዮቹም እነማ እንደሆኑ ስውር ባለመሆኑ መንግስት በነካ እጁ ጎራ ይበል ሲል ጥቆማ ሰጥተዋል። ዱባይ ላይ ሃብት የከመሩትና እግራቸው አዲስ አበባ የሆነውን፣ ለራሳቸው የውጭ ድርጅት በራሳቸው የአገር ቤት ድርጅት ኤል ሲል (LC) እየከፈቱ የሚመዘብሩት በደንብ ስለሚታወቁ መንግስት ዙሩን እንዲያከረው አሳስበዋል።

አሁን ላይ የውጭ ብር መንዛሪዎች አዲስ አበባ ዙሪያና ቅርብ በሆኑ ከተሞች የሚኖሩ እንድ ፍሬ ልጆችን በመቅጠር ነው የሚያሰሩት። በስማቸው ተያዥ አድርገው ገንዘብ በማስገባት በጥቁር ለሚመነዘርላቸው አካላት በአድራሽነትና አስተላላፊነት በወር እስከ 30 ሺህ ብር እንደሚከፈላቸው ብር ተልኮለት የተቀበል ዳያስፖራ ብሩን ከሰጥችው ልጅ መረጃ ማግኘቱን አመልካቶ ነው አሰራሩን ያስታወቀው።

አብዛኞቹ በስም የሚታወቁ የድርጅት ባለ ቤቶችና ሪል ስቴት ስር የሚንቀሳቀሱ በውጭ ምንዛሬ አጠባው ዋና ፊት አውራሪ መሆናቸውን ጥቆማ የሰጡት አመልክተዋል።

ሪልስቴ ዙሪያ ያሉ አብዛኞቹ ከመሬት ጋር በተያያዘ የሚያከማቹትን ሃብት ወደ ውጭ ስለሚያሸሹና በውክልና ድርጅቱን ላቆሙላቸው ዛሬ ላይ ሃብት የሚያስተላለፉትም በውጭ ምንዛሬ ብቻ በመሆኑ ዶላሩን እየለቀሙ ኑሮ እንዲግል፣ ህዝብ እንዲማረርና መንግስት ላይ እንዲነሳ ኢኮኖሚው ላይ ሚስማር የሚመቱት መሆናቸውን ጠቋሚዎቹ ስም ዘርዝረው ልከዋል። ሆኖም አዘግይተነዋል። ዶላር የሚዛወርባቸውን ቤቶችና እናውቃቸዋለን ያሉትን ተሽከርካሪዎች ሳይቀር ጠቁመዋል።

አብዛኞች እንደሚሉት በዚህ ሌብነት የተሰማሩት ቀደም ብለው ከትህነግ ጋር አብረው ሲነገዱና በውክልና “ምስለኔ ሃብታም” የሚባሉት ናቸው። ንብረት በተጋነነ ብር በመግዛት በቋሚ የወኪሎቻቸውን ብር የቻሉትን በውጭ ምንዛሬ፣ ያልቻሉትን በአገር ውስጥ በቋሚ ንብረት ላይ በማስቀመጥ ደሃው ቤት እንዳይገዛ፣ መሬት ወስዶ ጎጆ እንዳይቀይስ ዋጋውን እንዳናሩበት መረጃውን የላኩት አመልክተዋል። መንግስት ቆርጦና ወስኖ እነዚህ አካላት ላይ ከዘመተ የመሬትና የቤት ዋጋ በቅጽበት እንደሚሽቆለቆል በዕምነት ተናግረዋል።

መንግስት በአዲሱ ዓመት ሌብነት ላይ እንደሚዘምት፣ ዘመቻውንም ለመጀመር ዝግጅት ላይ እንዳለ ዳግም ወረራ መቀስቀሱ ይታወሳል። የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ታዬ ደንደአ “ሌባ ሊመነጠር ሲል ጦርነት መክፈት ምንን ለማሰናከል ታስቦ እንደሆነ ይታወቃል። ሁሉም ጎን ለጎን ይሄዳል” ማለታቸው ይታወሳል። (Ethio12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, illegal money, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule