• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ በተሰማሩ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው

October 27, 2022 09:39 am by Editor Leave a Comment

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስና ከኦሮሚያ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ በተሰማሩ ግለሰቦችና ድርጅቶቻቸው ላይ ጥናትን መሰረት ያደረገ እርምጃ መወሰዱን አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱ ለሚዲያ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ባለፉት ሁለት ወራት በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች ምንዛሪ ዙሪያ ሰፊና ጥልቀት ያለው ጥናት ሲካሄድ እንደነበር አመልክቷል፡፡

ችግሩ በጥናት ከተለየ በኋላም መረጃዎችንና ማስረጃዎችን መነሻ በማድረግ በተከናወነው ክትትል በሕገወጥ የውጭ ምንዛሪ ላይ ተሳታፊ የነበሩ 48 ግለሰቦችና ከፍተኛ መጠን ያላቸው የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች እንዲሁም ከድርጊቱ ጋር የተያያዙ የባንክ ደብተሮችና ልዩ ልዩ ሰነዶች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል ነው የተባለው፡፡

በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች የውጭ ሀገር የምንዛሪ ዋጋን የሚተምኑ፣ የሚሰበስቡና ሰብሳቢዎችንም የሚያሰማሩ መሆናቸውን መግለጫው ጠቁሟል፡፡ ሕገወጥ ድርጊታቸውንም ሕጋዊ ፈቃድ ባላቸው የተለያዩ የንግድ ድርጅቶች፣ የችርቻሮ ሱቆች፣ ቡቲኮች፣ ግሮሰሪዎችና ሱፐርማርኬቶች ሽፋን እንደሚያከናውኑ፤ በተሽከርካሪዎች ላይም ጭምር ይፈጽሙ እንደነበር አመላክቷል፡፡

በሕገ ወጥ መንገድ የሚሰበሰበው የውጭ ምንዛሪ በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ከሀገር ለማሸሽ እንዲሁም የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ አቅም በማሳጠት ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ግሽበት በማስከተል ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ለመፍጠር ታቅዶ ሲከናወን እንደነበር በጥናት መለየቱን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መግለጫ ጠቁሟል፡፡

በወንጀል ድርጊቱ ተጠርጥረው ከተያዙት ውስጥም ለህወሓት ድጋፍ ከሚያደርጉ የሽብር ቡድኑ ደጋፊዎች ጋር በትስስር የሚሠሩና ቀደም ብሎም የውጭ ምንዛሪን በሕገወጥ መንገድ ወደ ትግራይ ሲያስገቡ የነበሩ ይገኙበታል፡፡ ይህም በተቀናጀ መልኩ በውጭም በሀገር ውስጥም ሀብት ለማሸሽና የውጭ ምንዛሪ አቅምን ለማዳከም ይሠራ እንደነበር ያሳያል ብሏል መግለጫው፡፡

እንደ አገልግሎቱ መግለጫ ሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ዝውውሩ ወንጀል ከኢትዮጵያ እስከ ሶማሌ ላንድ ሀርጌሳ፤ ከዱባይና አሜሪካ እንዲሁም በሌሎች ሀገራትም ጭምር በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ቤተሰባዊ በሆነ ኔትዎርክ ጭምር የተደራጀና የሚታዘዝ ነበር፡፡ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ሕገወጥ የውጭ ምንዛሪ አስተላላፊዎቹ መካከል አንዳንዶቹ ከዚህ ቀደም በቁጥጥር ስር ውለው ፍርዳቸውን ጨርሰው የተለቀቁ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ከ100 ሺሕ ብር በላይ በማስከፈል ወደ ውጭ እንልካለን በማለት የዜጎችን ሀብትና ንብረት ሲዘርፉ የነበሩም በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀልና በውጭ ምንዛሪ ዝውውሩ በነበራቸው ተሳትፎ እንዲያዙ ተደርጓል፡፡

መንግሥት ሕገወጥ ድርጊቱን ለመከላከል የውጭ ሀገራት ገንዘቦች ከኢትዮጵያ የሚወጡባቸውን መንገዶችና ስልቶች በመረጃ በመለየትና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ጥብቅ ቁጥጥር ማድረጉንና በወንጀለኞች ላይ እርምጃ መውሰዱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለጫው አስታውቋል፡፡ የሀገርን ሀብትና ንብረት ዘርፈው ገንዘቡን በውጭ ምንዛሪ በማሸሽ ከሚፈጠሩ ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ሀገሪቷን ለመታደግ የሚደረጉ ጥረቶችንም በከፍተኛ ትኩረት እየተከታተለና አስፈላጊውን የማስተካከያ እርምጃዎች እየወሰደ መሆኑንም አመልክቷል፡፡

ኅብረተሰቡ ሕገወጦች በቁጥጥር ሰር እንዲውሉ ጥቆማ በመስጠት ያበረከተው አስተዋጽዖ ከፍተኛ በመሆኑ ምስጋናውን ያቀረበው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በቀጣይም ከደኅንነትና ከጸጥታ ተቋማት ጎን በመሆን ድጋፉን እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርቧል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, illegal money, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule