• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል

March 16, 2020 11:41 pm by Editor 7 Comments

የሚዲያው ዝምታ ለምን ይሆን?

የኮሮና ቫይረስ በቻይና ከመከሰቱ በፊት በአሜሪካ በቫይረሱ ተጠቅተው የሞቱ መኖራቸው ተረጋገጠ። ይህንን ያረጋገጡት የአሜሪካ የበሽታ ቁጥጥር ማዕከል (CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሮበርት ሬድፊልድ ናቸው። ዳይሬክተሩ እንዳሉት ይህ የታወቀው በኢንፍሉዌንዛ በሞቱ ሰዎች ላይ በድጋሚ በተደረገ ምርመራ ነው።

በተለያዩ የሚዲያ ዘገባዎች በተደጋጋሚ ሲነገር እንደቆየው የኮሮና ቫይረስ የተጀመረው በቻይና ዉሃን ከተማ እንደሆነ ነበር። ለበሽታው መነሻም የተለያዩ መላምቶች ሲሰጡ ቆይተዋል። አንዱ መላምት ከእንስሳት ወደ ሰው ነው የተላለፈው የሚል ነው።

ለዚህም እንደ ማስረጃነት የሚቀርበው ቻይናውያኑ የሚበሉት፣ “እርጥብ ገበያ” (wet market) ተብሎ በሚጠራው ቦታ ከባህር የሚገኙ ማንኛውም የአሣ ዝርያ እስከ የሌሊት ወፍ፣ እባብ፣ ውሻ፣ ሸለምጥማጥ፣ የዱር ድመት፣ ዓይጠመጎጥ፣ ወዘተ እየታረዱና እየተከተፉ የሚሸጡበት በደም፣ በፈርስና በመሳሰሉ የአራዊቱ ፍሳሾች የተበከለ በመሆኑና በሽታው የተነሳው እነዚህን እንስሳት ከመብላት ነው የሚል ነው።

ሌላኛው መላምት ደግሞ በቻይና ዉሃን ከተማ ድብቅ የባዮሎጂካል መሣሪያ ማምረቻ ጋር የተያያዝ ነው። መላምቱ፣ በፋብሪካው የኮሮና ቫይረስ ለማምረት ሙከራ ሲደረግ ስለነበር ቫይረሱ ከዚያ አፈትልኮ የወጣ ነው የሚል ነው። ይህም በሽታው የተዛመተው ከእንስሳት ወደ ሰው ሳይሆን፣ በቅድሚያ ሰዎች ተይዘው ነው ወደ እንስሳቱ የተዛመተው ለሚለው መከራከሪያ እንደ ማስረጃ ይቀርባል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ የተለያዩ መላምቶች የሚቀርቡ ሲሆን በሚዲያ ብዙም ትኩረት ሳያገኝ የታለፈው ጉዳይ ግን በሽታው በቻይና ከመከሰቱ በፊት በአሜሪካ የኢንፍሉዌንዛ ወቅት በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተው የሞቱ ሰዎች እንዳሉ መገለጹ ነው።

ይህ የሚዲያ አውታሮች በሚገባው መጠን ጆሮ የከለከሉት ወይም እንደ ጉዳዩ ግዝፈት ሰፊ ሽፋንና ትኩረት ያልሰጡት ጉዳይ ይፋ የሆነው የአሜሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ማርች ፲፩ በተወካዮች ምክርቤት ለውይይት ተጠርተው በሰጡት ማብራሪያ ላይ ነበር።

የምክርቤቱ ኦቨርሳይት ኮሚቴ (Oversight Committee) የማዕከሉን (CDC) ዳይሬክተር ዶ/ር ሮበርት ሬድፊልድን ጠርቶ ባወያየበት ወቅት ጥያቄዎችን አቅርቦላቸው ነበር። በውይይቱ ወቅት ሃርሊ ሮውዳ የተባሉ የካሊፎርኒያ እንደራሴ ባለፉት ወራት አንዳንድ ኢንፍሉዌንዛ ወይም ፍሉ በሽተኞች በርግጥ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች እንደነበሩና ምናልባትም በትክክል ሳይመረመሩ እንደቀሩ ለዳይሬክተሩ ጥያቄ ያቀርባሉ።

ዳይሬክተሩ ሲመልሱም “ባለው መደበኛ አሠራር የመጀመሪያው ምርመራ የኢንፍሉዌንዛ ምርመራ ማድረግ ነው፤ በኢንፍሉዌንዛ ከተያዙ ፖዘቲቭ ይሆናሉ (ወይም ኢንፍሉዌንዛ ይዟቸዋል ይባላል)” ብለዋል።

እንደራሴው በመቀጠልም ባለፉት ወራት ኮሮና ይፋ ከመሆኑ በፊት በኢንፍሉዌንዛ የሞቱትን አሁን ከሞቱ በኋላ ኮሮና እንደነበረባቸው ምርመራ ስለመደረጉ ይጠይቃሉ።

ዳይሬክተሩ ሲመልሱም “በሁሉም ከተማ፤ በሁሉም ጠቅላይ ግዛት እና በሁሉም ሆስፒታል ባይተገበርም ማዕከላችን በሳምባ ምች የሞቱ ሰዎችን የሚከታተልበት ስልት አለው” ይላሉ።

ይህንን ምላሽ ተከትለው እንደራሴው እንዲህ በማለት ሌላ ጥያቄ ያቀርባሉ፤ “ስለዚህ አንዳንድ ሰዎች በአሜሪካ በኢንፍሉዌንዛ የሞቱ ናቸው ያልናቸው እንደተባለው ሳይሆን በርግጥም የሞቱት በኮሮና ቫይረስ ነው ሊባል ይችላል” በማለት ጥያቄያቸውን አጠናክረው ያቀርባሉ።

ዳይሬክተሩ ሲመልሱም፤ “አንዳንድ ኬዞች በርግጥ በዚያ መልኩ በአሜሪካ ለመከሰታቸው በምርመራ ታውቋል” ብለዋል።

በአሜሪካ የኢንፍሉዌንዛ (የፍሉ) ወቅት የሚባለው የሚጀምረው በኦክቶበር (ጥቅምት) አካባቢ እንደሆነና ዲሴምበር (ታህሣሥ) ላይ ከፍ እያለ መጥቶ እስከ ማርች (መጋቢት) ድረስ አንዳንዴም እስከ ሜይ (ግንቦት) እንደሚዘልቅ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከሉ ያወጣው መረጃ ያመለክታል።

ከሴፕቴምበር ፳፱ ጀምሮ እስከ ፌብሩዋሪ ፲፱ ባለው ጊዜ ውስጥ 250,000 አሜሪካውያን ከፍሉ ጋር በተያያዘ ሆስፒታል ገብተው እንደነበርና ከእነዚህም 14,000 በዚህ የኢንፍሉዌንዛ ወቅት መሞታቸውን የኢንፌክሽንና የአለርጂ በሽታዎች ብሔራዊ ማዕከል አስታውቆ ነበር። ከሞቱት ቁጥር ውስጥ ስንቱ በኮሮና ቫይረስ እንደሞቱ በውል አልታወቀም።

እንደራሴው አጥብቀው ላቀረቡት ጥያቄ የማዕከሉ ዳይሬክተር የሰጡት ምላሽም ከዚህ ጋር የተያያዘ ነው። ዳይሬክተሩ ያሉት በመደበኛ ኢንፍሉዌንዛ ሞቱ ከተባሉት ውስጥ ከሞት በኋላ (posthumous) በተደረገ ምርመራ በኮሮና ቫይረስ መሞታቸው ታውቋል የሚለውን ነው ያረጋገጡት።

ጉዳዩ ይህ ከሆነ በቻይና ዉሃን ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ከመሞታቸው በፊት አሜሪካ ውስጥ ሞተዋል የሚለውን የሚያረጋግጥ ይሆናል፤ ይህ ደግሞ በሽታው አስቀድሞ አሜሪካ ተከስቶ ነበር ወደሚለው ድምዳሜ ይወስዳል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ በቻይና እና ጃፓን የሚገኙ የሚዲያ ውጤቶች እያነሱ ያለው ጥያቄ በአሜሪካ የመጀመሪያው የኮሮና ተጠቂ የሞተው መቼ ነው? እስካሁን ስንት ሞተዋል? በሽታው በአሜሪካ የጀመረው መቼ ነው? ወዘተ የሚሉ ሆነዋል። እነሱ ይህንን ቢሉም ራሳቸው የአሜሪካን ሚዲያ አውታሮች ግን ይህንን ታላቅ ጉዳይ ዝም ማለታቸው ለምን ይሆን የሚለው ግን ከቫይረሱ የመከላከያ ክትባት ባልተናነሰ ምክንያቱ የመታወቁ ጉዳይ ልዩ ምርምር ያሻዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Slider Tagged With: coronavirus, covid-19, Full Width Top, Middle Column, wuhan china

Reader Interactions

Comments

  1. AA says

    March 18, 2020 11:32 am at 11:32 am

    Hallo dear Goolgule colleagues,

    I am writing this to you because I appreciate what you are doing and I hope that you remain as you are now. I strongly suggest that you stay away from posting the kind of information that you did on this Covid-19. Remember the issue is so scientific, too technical and very new even to the world of scientists. Your piece of writing is not something that is substantiated. It is not verified and it has some kind of twisting interpretations. Stay on things that you are sure of.

    Thank you.

    Reply
    • Editor says

      March 19, 2020 07:03 am at 7:03 am

      Dear AA,

      Many thanks for your comments and suggestions.

      As we have linked the article with the source that we found, it is very substantiated and supported by evidence. Dr. Redfield of the CDC said that at the House Oversight Committee discussion. He admitted that in the United States people have actually been diagnosed with and died of Covid-19 while it was thought that it is influenza. This was a posthumous diagnosis and it was confirmed by the good doctor himself.

      In case you have overlooked the link here it is – https://edition.cnn.com/world/live-news/coronavirus-outbreak-03-11-20-intl-hnk/h_1319f66f92245a2fe4ec63fe91ab66c9

      It was reported by the CNN and here is what was reported:

      3:46 p.m. ET, March 11, 2020
      CDC director says some coronavirus-related deaths have been found posthumously

      During the House Oversight Committee discussion on the novel coronavirus response, the director of the US Centers for Disease Control and Prevention said some deaths from coronavirus have been discovered posthumously.

      Rep. Harley Rouda asked CDC director Dr. Robert Redfield if it’s possible that some flu patients may have been misdiagnosed and actually had coronavirus.

      “The standard practice is the first thing you do is test for influenza, so if they had influenza they would be positive,” Redfield said.

      Rouda then asked Redfield if they are doing posthumous testing.

      Redfield said there has been “a surveillance system of deaths from pneumonia, that the CDC has; it’s not in every city, every state, every hospital.”

      Rouda followed up and asked, “So we could have some people in the United States dying for what appears to be influenza when in fact it could be the coronavirus?”

      The doctor replied that “some cases have actually been diagnosed that way in the United States today.”

      Thanks for your engagement.

      Editor

      Reply
  2. Tesfa says

    March 19, 2020 04:03 pm at 4:03 pm

    ሃሳቡ የቀረበው በአማርኛ በመሆኑ ያለኝን ሃሳብ በዚሁ ቋንቋ ባካፍል የሚሻል ይመስለኛል። ዓለማችን ከእንስሳት ወደ ሰው ከሰው ወደ እንስሳ በሚተላለፉ በሽታዎች መታመስ የጀመረችው አሁን አይደለም። እውቁ ቫይሮሎጂስት Stephen S. Morse የበሽታን ትልልፍ አስመልክቶ እንዲህ ይለናል። Viruses have no locomotion. ማለት የፈለገው በሌላው ላይ ተንጠላጥለው ነው በየዓለማቱ ሁሉ የሚዳረሱት ነው። ቻይና ነገሮችን በማፈንና በመደበቅ የምትታወቅ ሃገር ናት። ለዚህም መረጃው በኮሮና ቫይረስ ሟች ዶክተሯ የበሽታውን ምልክት እንዳገኘ ሲነግራቸው የወሰድት ፓሊስ ጣቢያ ነው። ውሸት ነው ብለህ ፈርም ተብሎ በመፈረም ከተለቀቀ በህዋላ ያው እንደ ሰደድ እሳት የቫይረሱ ስርጭት በቻይና ሲቀጣጠል እርሱም የዚሁ ሰለባ ሆኗል በማለት የቻይና መንግሥት አሳውቆናል። ታዲያ መንግሥታት የውሸት ቋቶች ለመሆናቸው ምስራቅ ምእራብ ማየት አያስፈልግም። የማይዋሽ መንግስት የለም። ወደ በሽታው ቀድሞ መከሰት ጉዳይ ስንገባ የሚታመን ወሬ የለም። CNN እና Fox News ጎራ ለይተው የሚፋለሙ የውሸት ቱልቱላዎች ናቸው። ራሱ ዜናው ሁሉ በውሸት የተሞላ ነው። በዚያ ላይ ሶሻል ሚዲያን እና ሌሎችንም የፈሪ ድላዎች ስታክልበት እውነት መቀበሯን በቀላሉ ተረዳለህ። ዋናው ነገር በሽታው የዓለም ችግር መሆኑ ነው። ይህ ጉዳይ በቅርብ እልባት ካላገኘ አዕላፍ ሰዎች ህይወታቸውን ያጣሉ። በመሆኑም ምንጩ የት ሃገር እንደሆነ መከራከሩ ጠቃሚነት የለውም። ዝም ብሎ በመከራ ዝናብ መካከል ድንጋይ መወራወሩም ለማንም አይበጅም። በመሰረቱ ብዙ ነገሮች ስም የሚሰጣቸው በመነጩበት (በተገኙበት) ሥፍራ ነው። ግን የአሁኑ ጂኦ ፓለቲካ አትንኩኝ የሚል በመሆኑ ቻይናም ከእኔ አልመጣም ማለቷ አታድርስ ነው። አሜሪካም ቢሆን በሌሎች ላይ ነገርን ማላከኳ ዛሬ የተጀመረ አይደለም።
    የዚህ ድህረ ገጽ ዝግጅት ክፍልም የሁለቱን መንግስታት አተካራም ሆነ የአሜሪካው የወሬ አውታር ዳይሬክተር ዶ/ር ሮበርት ቃለ ምልልስ ዋቢ አርጎ ያቀረበውም መጣጥፍ እንደ መረጃ ማቅረቡ ጠቃሚነት የለውም። ይልቁንስ ለህዝባችን ምክር ነገር ሃሳብ በሙያው ከተሰማሩ ሰዎች አጠናቅሮ ቢያቀርብ መልካም ነበር እላለሁ።

    Reply
    • Editor says

      March 19, 2020 11:17 pm at 11:17 pm

      ተስፋ

      ለአስተያየቱ እናመሰግናለን፤ ሆኖም ዜናው ሲኤንኤን እንደ ዜና ከዋናው ስብሰባ ቀንጭቦ አቀረበው እንጂ በርግጥም በምክርቤቱ ውይይት የተደረገበት ነው። እንጂ የሃሰት ዜና አይደለም። ሙሉውን እዚህ ላይ ማዳመጥ ይቻላል። https://oversight.house.gov/legislation/hearings/coronavirus-preparedness-and-response

      እርስዎ በጠቀሱዋቸው የዜና አውታሮች መካከል ያለውን ጉዳይ እኛም ሳናውቀው ቀርተን አይደለም። ሆኖም ዋናው ነገር ዜናው በምክርቤት ደረጃ የቀረበ መሆኑን ለማሳወቅ ነው።

      በየጊዜው ስለሚሰጡት አስተያየቶች ምስጋና እናቀርባለን።

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
  3. Alex says

    March 21, 2020 07:36 pm at 7:36 pm

    I prefer better to think about our problems doesn’t matter where it’s already done we have to think how to stop the virus inside our country if all of the continent think the same way coronavirus I don’t think it’ll get space on the planet but talking about a thing even not sure exactly what it is, how stop that I don’t think will be solution when a news posted about must be you are responsible for it don’t bring a news from other social media how sure even that news taken from other same do. Every news must be take responsible for that should be taken by you attended.

    Reply
  4. Ayele says

    April 21, 2020 08:30 pm at 8:30 pm

    ከሞት በኋላ (posthumous) በተደረገ ምርመራ ??? mean postmortem?

    Reply
    • Editor says

      April 22, 2020 11:19 am at 11:19 am

      The title of the news reads:
      CDC director says some coronavirus-related deaths have been found posthumously

      Both would work. Thanks for the comment, though.

      Editor

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule