• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው

March 18, 2020 08:37 pm by Editor 1 Comment

በትግራይ የሚገኘውና 18 ሺሕ ገደማ ኤርትራውያን የሚኖሩበት ሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ሊዘጋ መሆኑን ስደተኞች ለዶይቼ ቬለ ተናገሩ።

በመጠለያው የሚኖሩ በአስር ቀናት ሕንፃጽ መጠለያን እንዲለቁ በኢትዮጵያ ስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር ባለፈው ሐሙስ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው ለዶይቼ ቬለ አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ ከሚገኙ ስድስት ኤርትራውያን ስደተኞች ከሚያስተናግዱ መጠለያ ጣብያዎች መካከል አንዱ የሆነው በትግራይ ክልል ሽረ ከተማ አቅራቢያ የሚገኘው ሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ ከሰባት ዓመት በፊት ተቋቁሞ 18 ሺህ ገደማ ኤርትራውያን ስደተኞች እያስተናገደ የሚገኝ ማእከል ነው።

በስደተኞች መጠልያ ጣብያው ሕንፃፅ የሚኖሩ ኤርትራውያን እንደሚሉት ባለፈው ዕለተ ሐሙስ ነበር የሚኖሩበት መጠልያ እንደሚዘጋና በአስር ቀናት ውስጥ ቦታ እንዲቀይሩ የተነገራቸው።

በሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ጣብያ የሚኖር ኤርትራዊ ስደተኞ ሓዱሽ ታደለ እንደሚለው በኢትዮጵያ መንግስታት የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር በኩል የመጣው ይኽ ውሳኔ በካምፑ የሚኖሩ በርካታ ስደተኞችን ያሳዘነ እንደሆነ ይገልፃል። የስደተኞቹ ተወካዮችም ውሳኔው ከተነገረ በኋላ ከUNHCR ተወካዮችና ከትግራይ ክልል የአስተዳደር አካላት ጋር ትላንት መወያየታቸው ጠቅሶ መጠልያው እንደሚዘጋ አስቀድሞ የተነገራቸው ነገር አለመኖሩ መረዳታቸው የሕንፃፅ ስደተኞች መጠለያ ነዋሪው ሓዱሽ ታደለ ነግሮናል።

18 ሺህ ገደማ ኤርትራውያን የሚኖሩበት ሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ጣብያ ይዘጋል የተባለው ከፋይናንስ ጋር በተያያዘ ምክንያት መሆኑ አንድ ስሙ መጥቀስ ያልፈለገ በጣቢያው የሚሰራ የአንድ ውጭ ድርጅት ተቀጣሪ ይገልፃል። ይሁንና ስደተኞቹ ወደ ማይዓይኒ እና ዓዲሓርሽ የተባሉ ሌሎች በአቅራቢያው የሚገኙ መጠልያዎች ለመቀየር ሀሳብ መኖሩ መረዳቱ ጨምሮ ይገልፃል።

ኤርትራውያን ስደተኞቹ ግን ሕንፃፅ መጠለያ ካምፕ ለመዝጋት የተፈለገው በኢትዮጵያና ኤርትራ መንግስታት የውስጥ ስምምነት ሊሆን እንደሚችል ይጠረጥራሉ። ሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ ወደ ኤርትራ ድንበር የቀረበ በመሆኑ በርካታ ድንበር አቋርጠው የሚጓዙ ስደተኞች ወደ ካምፑ ለመግባት ተስፋ አድርገው ከሀገራቸው እንደሚወጡ ያስረዳሉ።

በዚህ ጉዳይ ዙርያ የኢትዮጵያ መንግስት የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር የስራ ሐላፊዎች ለማነጋገር በተደጋጋሚ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

የትግራይ ክልል መንግስት ኤርትራውያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ፣ የተቋቋሙ የስደተኞች መጠልያ ጣብያዎች እንዲዘጉ መንግስታት “እያሴሩ ነው” ሲል ሲከስ ቆይቷል። የትግራይ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል 45ኛ ዓመት የህወሓት ምስረታ የካቲት 11 በሚከበርበት ወቅት ባደረጉት ንግግር “ማነኛውም ኃይል” የኤርትራ ስደቸኞች መጠለያ ጣብያዎች መዝጋት አይችልም ሲሉ ገልፀው እንደነበረ ይታወሳል።

© ለዶይቼ ቬለ

ከዝግጅት ክፍሉ፤ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከተለያዩ ወገኖች የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው በዚህ “ኤርትራውያን” ይኖሩበታል በሚባለው የስደተኞች መጠለያ በአብዛኛው እየተጠቀሙ የነበሩት ከህወሓት ጋር የጥቅም ግንኙነት ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ነበሩ። ከኢትዮጵያ ውደ አውሮጳ የሚፈልሱ የትግራይ ተወላጆች በተለይም ከህወሓት ሹሞች ጋር ቀጥተኛ ወይም ተዘዋዋሪ ግንኙነት ያላቸው አውሮጳ ከመሰደዳቸው በፊት ኤርትራውያን እንደሆኑና አውሮጳ ሲደርሱ በቀላሉ የመኖሪያ ፈቃድ ሊያስገኝላቸው የሚችል ሰነድ ይዘው የሚወጡት ከዚህ የስደተኞች ማዕከል ነው። ከአገር አስቀድመው ሰነዶችን አዘጋጅተው ከወጡ በኋላ ከአውሮፓ አገራት በአንዱ የመኖሪ ፈቃድ ጠይቀው በርካቶች ዓመታት የሚወስድባቸውን በጥቂት ወራት ለማግኘት ሲችሉ ቆይተዋል። ከዚህ ሌላ እነዚሁ የህወሃት ሰዎች ወረቀታቸውን ካገኙ በኋላ ቀጣዩ ሥራቸው ባሉበት የአውሮጳ ከተማ ወይም አገር ማን ምን እንደሚያደርግ፤ ማን ሰልፍ እንደሚወጣ፤ ስብሰባ እንደሚደራጅ፤ ወዘተ መረጃ እየሰበሰቡ ወደ ኢትዮጵያ በመላክ ትልቅ የስለላ ሥራ ሲሠሩ ቆተዋል። የደብረጽዮን “ማንኛውም ኃይል” ሊዘጋው አይችልም ፍርሃት ከዚህ ጋር የተቆራኘ ሊሆን ይችላል የሚል አስተያየት ይሰጣል።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Right Column, Slider, Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar, tigray camp

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    March 19, 2020 09:54 pm at 9:54 pm

    በኤርትራ ስደተኞች ስም ወደ ውጭ የሚወጡት የትግራይ ሰዎች የTPLF agent ሆነው ውጭ ሐብት እንዲዘዋወርና ሱቅ እንዲከፍቱና ሕወኣት እንዲረዱ ይደረግ የነበረው ከ80 ሺህ በላይ ስደተኛ ተብሎ የጠፋው በየ አገሩ ተበትኖ ያለው ሕወኣት በቂ የፓለቲካ case በመስጠት በስውር የተሰራውን ሁሉንም ነገር ለተለያየ case አገራት እንደ ኣስቸኳይ ኬዝ ታይቶ ጉዳያቸው እንዲፈጥን ተደስጎ በካናዳ በኣሜሪካ፣በተለያየ ረገር ገብተው እቸኖሩ ነው። የሕወኣት ወንጀል አለምአቀፋውም ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule