• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው

March 18, 2020 08:37 pm by Editor 1 Comment

በትግራይ የሚገኘውና 18 ሺሕ ገደማ ኤርትራውያን የሚኖሩበት ሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ሊዘጋ መሆኑን ስደተኞች ለዶይቼ ቬለ ተናገሩ።

በመጠለያው የሚኖሩ በአስር ቀናት ሕንፃጽ መጠለያን እንዲለቁ በኢትዮጵያ ስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር ባለፈው ሐሙስ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው ለዶይቼ ቬለ አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ ከሚገኙ ስድስት ኤርትራውያን ስደተኞች ከሚያስተናግዱ መጠለያ ጣብያዎች መካከል አንዱ የሆነው በትግራይ ክልል ሽረ ከተማ አቅራቢያ የሚገኘው ሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ ከሰባት ዓመት በፊት ተቋቁሞ 18 ሺህ ገደማ ኤርትራውያን ስደተኞች እያስተናገደ የሚገኝ ማእከል ነው።

በስደተኞች መጠልያ ጣብያው ሕንፃፅ የሚኖሩ ኤርትራውያን እንደሚሉት ባለፈው ዕለተ ሐሙስ ነበር የሚኖሩበት መጠልያ እንደሚዘጋና በአስር ቀናት ውስጥ ቦታ እንዲቀይሩ የተነገራቸው።

በሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ጣብያ የሚኖር ኤርትራዊ ስደተኞ ሓዱሽ ታደለ እንደሚለው በኢትዮጵያ መንግስታት የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር በኩል የመጣው ይኽ ውሳኔ በካምፑ የሚኖሩ በርካታ ስደተኞችን ያሳዘነ እንደሆነ ይገልፃል። የስደተኞቹ ተወካዮችም ውሳኔው ከተነገረ በኋላ ከUNHCR ተወካዮችና ከትግራይ ክልል የአስተዳደር አካላት ጋር ትላንት መወያየታቸው ጠቅሶ መጠልያው እንደሚዘጋ አስቀድሞ የተነገራቸው ነገር አለመኖሩ መረዳታቸው የሕንፃፅ ስደተኞች መጠለያ ነዋሪው ሓዱሽ ታደለ ነግሮናል።

18 ሺህ ገደማ ኤርትራውያን የሚኖሩበት ሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ጣብያ ይዘጋል የተባለው ከፋይናንስ ጋር በተያያዘ ምክንያት መሆኑ አንድ ስሙ መጥቀስ ያልፈለገ በጣቢያው የሚሰራ የአንድ ውጭ ድርጅት ተቀጣሪ ይገልፃል። ይሁንና ስደተኞቹ ወደ ማይዓይኒ እና ዓዲሓርሽ የተባሉ ሌሎች በአቅራቢያው የሚገኙ መጠልያዎች ለመቀየር ሀሳብ መኖሩ መረዳቱ ጨምሮ ይገልፃል።

ኤርትራውያን ስደተኞቹ ግን ሕንፃፅ መጠለያ ካምፕ ለመዝጋት የተፈለገው በኢትዮጵያና ኤርትራ መንግስታት የውስጥ ስምምነት ሊሆን እንደሚችል ይጠረጥራሉ። ሕንፃፅ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ ወደ ኤርትራ ድንበር የቀረበ በመሆኑ በርካታ ድንበር አቋርጠው የሚጓዙ ስደተኞች ወደ ካምፑ ለመግባት ተስፋ አድርገው ከሀገራቸው እንደሚወጡ ያስረዳሉ።

በዚህ ጉዳይ ዙርያ የኢትዮጵያ መንግስት የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር የስራ ሐላፊዎች ለማነጋገር በተደጋጋሚ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

የትግራይ ክልል መንግስት ኤርትራውያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ፣ የተቋቋሙ የስደተኞች መጠልያ ጣብያዎች እንዲዘጉ መንግስታት “እያሴሩ ነው” ሲል ሲከስ ቆይቷል። የትግራይ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል 45ኛ ዓመት የህወሓት ምስረታ የካቲት 11 በሚከበርበት ወቅት ባደረጉት ንግግር “ማነኛውም ኃይል” የኤርትራ ስደቸኞች መጠለያ ጣብያዎች መዝጋት አይችልም ሲሉ ገልፀው እንደነበረ ይታወሳል።

© ለዶይቼ ቬለ

ከዝግጅት ክፍሉ፤ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከተለያዩ ወገኖች የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው በዚህ “ኤርትራውያን” ይኖሩበታል በሚባለው የስደተኞች መጠለያ በአብዛኛው እየተጠቀሙ የነበሩት ከህወሓት ጋር የጥቅም ግንኙነት ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ነበሩ። ከኢትዮጵያ ውደ አውሮጳ የሚፈልሱ የትግራይ ተወላጆች በተለይም ከህወሓት ሹሞች ጋር ቀጥተኛ ወይም ተዘዋዋሪ ግንኙነት ያላቸው አውሮጳ ከመሰደዳቸው በፊት ኤርትራውያን እንደሆኑና አውሮጳ ሲደርሱ በቀላሉ የመኖሪያ ፈቃድ ሊያስገኝላቸው የሚችል ሰነድ ይዘው የሚወጡት ከዚህ የስደተኞች ማዕከል ነው። ከአገር አስቀድመው ሰነዶችን አዘጋጅተው ከወጡ በኋላ ከአውሮፓ አገራት በአንዱ የመኖሪ ፈቃድ ጠይቀው በርካቶች ዓመታት የሚወስድባቸውን በጥቂት ወራት ለማግኘት ሲችሉ ቆይተዋል። ከዚህ ሌላ እነዚሁ የህወሃት ሰዎች ወረቀታቸውን ካገኙ በኋላ ቀጣዩ ሥራቸው ባሉበት የአውሮጳ ከተማ ወይም አገር ማን ምን እንደሚያደርግ፤ ማን ሰልፍ እንደሚወጣ፤ ስብሰባ እንደሚደራጅ፤ ወዘተ መረጃ እየሰበሰቡ ወደ ኢትዮጵያ በመላክ ትልቅ የስለላ ሥራ ሲሠሩ ቆተዋል። የደብረጽዮን “ማንኛውም ኃይል” ሊዘጋው አይችልም ፍርሃት ከዚህ ጋር የተቆራኘ ሊሆን ይችላል የሚል አስተያየት ይሰጣል።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column, Slider, Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar, tigray camp

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    March 19, 2020 09:54 pm at 9:54 pm

    በኤርትራ ስደተኞች ስም ወደ ውጭ የሚወጡት የትግራይ ሰዎች የTPLF agent ሆነው ውጭ ሐብት እንዲዘዋወርና ሱቅ እንዲከፍቱና ሕወኣት እንዲረዱ ይደረግ የነበረው ከ80 ሺህ በላይ ስደተኛ ተብሎ የጠፋው በየ አገሩ ተበትኖ ያለው ሕወኣት በቂ የፓለቲካ case በመስጠት በስውር የተሰራውን ሁሉንም ነገር ለተለያየ case አገራት እንደ ኣስቸኳይ ኬዝ ታይቶ ጉዳያቸው እንዲፈጥን ተደስጎ በካናዳ በኣሜሪካ፣በተለያየ ረገር ገብተው እቸኖሩ ነው። የሕወኣት ወንጀል አለምአቀፋውም ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule