• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው

April 13, 2023 08:56 am by Editor Leave a Comment

ጦርነት ባሕላችን ነው፣ ተራራ ያንቀጠቀጠ ትውልድ፣ ወዘተ በሚሉ ባዶ ዲስኩሮችና ከንቱ ልፈፋዎች ትውልድን በስሁት ትርክት ሲነዳ የኖረው ትህነግ የሚፈራው ጥያቄ እየቀረበለት ነው። “ልጆቻችን የት ናቸው?” “ልጆቻችንን መልሰን ማግኘት እንፈልጋለን” ወዘተ የሚሉ የወላጆች ጥያቄ በትግራይ እየተሰማ ነው።

አቶ ገብረመስቀል አበበ የተባሉት ሌላኛው ነዋሪም የአንድ ወንድ ልጅ አባት ሲሆኑ “ከአንድ ቤት አንድ ሰው ወደ ጦርነት መግባት አለበት፣ ካልሆነ እርዳታ አይሰጠውሙ” በተባለ ጊዜ አንዱ ልጃቸው በግዳጅ ወደ ውጊያ ማምራቱን በሀዘን ድባብ ውስጥ ሆነው ነግረውናል። 

አሁን በተደረሰው ስምምነት መሰረት “ልጄ ከዛሬ ነገ ይመጣል እያልኩ በሀዘንና በተስፋ እገኛለሁ” የሚሉት አቶ ገብረመስቀል ልብ በሚሰብር ሁኔታ እያለቀሱ ልጄ ካለ መንግስት ምላሽ ይስጠኝ ሲሉ ይማፀናሉ።  

ወ/ሮ ለምለም ኃይሉ የመቀሌ ከተማ ነዋሪ ናቸው። ለሁለት ዓመታት በቆየው ጦርነት ሁለት ልጆቻቸው ወደበረሃ ወርደው ጦርነቱን እንደተቀላቀሉ ይገልፃሉ። ጦርነቱ በሰላም ስምምነት ተቋጭቶ ግልፅነት ይጎድለዋል የሚሉ አካላት ቢኖሩም አንፃራዊ ሰላም ሰፍኖ ክልሉም ጊዜያዊ አስተዳደር ተሹሞለታል። 

ይሁን እንጂ ወ/ሮ ለምለም ሁለት ልጆቻቸው እስካሁን ድረስ የት እንዳሉ እንደማያውቁ ገልፀው የልጆጃቸውን መገኛ በጉጉት እንደሚጠብቁ ነግረውናል። ከቤት በወጡበት ሰሞን ልጆቻቸው ደብዳቤ ይሉኩላቸው እንደነበር ለአዲስ ዘይቤ የተናገሩት አዛውንቷ፣ ለመጨረሻ ጊዜ የልጆቻቸውን ወሬ ከሰሙ 1 ዓመት ከ8 ወር ማለፉንም ገልፀዋል።

ወ/ሮ ለምለም ኃይሉ እንደሚናገሩት “ልጆቼን ለመፈለግ ያልደረሱስኩበት ቦታ የለም፣ መረጃ ላገኝ ግን አልቻልኩም” ብለው ወ/ሮ ለምለም ልብ በሚሰብርና ተስፋና ፍራቻ በተቀላቀለበት ሁኔታ ስለልጆቻቸው ይጠይቃሉ። 

በተመሳሳይ የመቀሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ሃረግ ተሰማ በተፈጠረው ጦርነት የአራት ልጆቿ አባት ወደ ጦርነት መቀላቀሉን ትገልፃለች። ባለቤቷ አቶ ግርማይ ፈቃዱ በመምህርነት እየሰራ ልጆቹንና ቤተሰቦቹን ያስተዳድር ነበር። 

ጦርነቱ ከጀመረ በኋላ በ2013 ዓ.ም. ከቤት እንደወጣ ወጣ እስካሁን ድረስ አድራሻው አይታወቅም። ወ/ሮ  ሃረግ አሁን ላይ የቀን ስራ እየሰራች ልጆቿን ለማስተዳደር ተገድዳለች። “ስራ ካልተገኘ ደግሞ ቤቴ ነው የምውለው፣ ልጆችን ማስተዳደር ከባድ ነው” የምትለው የመቀሌ ከተማ ነዋሪዋ ለመጨረሻ ጊዜ የቤት ኪራይ ከከፈለች 2 ዓመታት ከግማሽ ስለማለፉ እንባ እየተናነቃት ነግራናለች። የባለቤቷ የት እንዳለ አለመታወቅ ለራሷ እና ለልጆቿ ሃዘን እንደሆነባቸውም ለአዲስ ዘይቤ ተናግራለች።

ሌላኛዋ የመቀሌ ነዋሪ ወይዘሮ ክንደሓፍቲ ባለቤታቸው በ2013 ዓ.ም ልጃቸው ደግሞ በ2014 ዓ.ም ለጦርነቱ ከቤት እንደወጡ እስካሁን በህይወት ስለመኖራቸውም ሆነ ስለመሞታቸው ምንም ወሬ የለም ይላሉ። “ያልሄድኩበትና ያልጠየቅኩበት ቦታ የለም” የሚሉት ወ/ሮ ክንደሓፍቲ አሁን ላይ መንግስት የት እንዳሉ ምላሽ ቢሰጠን ሲሉ በሀዘን ተናግረዋል።

አዲስ ዘይቤ የክልሉን የአስተዳደርና ጸጥታ ተቋም አስተያየት ለማካተት ያደረገችው ሙከራ ባይሳካም በጉዳዩ ዙሪያ መረጃዎችን ለማገኘት ጥረታችን ቀጥሏል።

ይህ የወላጆች ጥያቄ ባለፈው ሰሞን መለስ “ቆሻሻ” ብሎ በሚጠራቸው የአካል ጉዳተኞች ከተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ጋር የሚመሳሰል ነው። ሰላም ከመጣና ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎቹ ከተሟሉ እነዚህ መሰል የሰብዓዊ መብቶች ጥያቄ እንደሚያነሳ ይጠበቃል። ትህነግ ውጊያና ጦርነትን የሙጥኝ ብሎ ይዞ የቀጠለው ይህንን መሰል ጥያቄዎች ላለመጋፈጥ ነበር። አሁን ነገሮች ዓይናቸውን አፍጥጠው መጥተዋል። ይህንን መሰል ጥያቄዎች መበራከት ትህነግ መቼም ቢሆን ማንሰራራት የማይችል ቡድን ሆኖ የሚያፈራርሰው ይሆናል ተብሎ ይገመታል። በትግራይ ለዘመናት የገነባውም ስሁት ትርክት፣ ዓላማውም፣ ፕሮግራሙም፣ ባንዲራውም፣ መዝሙሩም አብሮ የሚቀበር ይሆናል የሚሉ አስተያየቶች ይደመጣሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics, Slider, Social Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule