• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ

March 21, 2023 11:01 pm by Editor Leave a Comment

ከለውጥ ወዲህ መላው የኢትዮጵያ ክፍል ሲታመስ ሰላሙ ተጠብቆ የነበረው በትግራይ ነበር። በአገሪቷ ውስጥ እየተከሰተ ያለው የሰላም መታጣት ያሳሰባቸው እናቶች ወደ ተለያዩ ክልሎች ሄደው ስለ ሰላም ሲማጸኑ ቆይተው ትግራይ ሲደርሱ የተነገራቸው እነርሱንም ያስደመመ ነበር። በወቅቱ ከታቦት እኩል ለአምልኮ የደረሰው ደብረጽዮን የመለሰላቸው በትግራይ ሰላም ነው፤ ሰው ወጥቶ ይገባል፤ ሰላም የታጣው በሌላ ክልል ነው፤ እዚያ ሄዳችሁ ብታለቅሱ ይሻላል ነበር ያላቸው። ሌላው የአገሪቱ ክልል ቀውስ ውስጥ መግባት ዋናው መሪ እና ግጭት ቀማሚ ህወሓት መሆኑን የካደ ግብዝነት የተሞላበት ምላሽ ነበር።

እጅግ ከፍተኛ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ፣ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያለችው ትግራይ እስካሁን ድምጽ ሳይሰማባት ቆይቶ ዛሬ በተቃውሞ ስትናወጥ ውላለች። በጦርነቱ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው በመለስ ዜናዊ አነጋገር “ቁሻሻ” የሚባሉት ዛሬ የምንበላው አጣን ብለው መቀሌ ሰልፍ ወጥተዋል።

የትግራይ ፖለቲካ አንጻራዊ መረጋጋት ያሳያል ተብሎ በተገመተበት ወቅት የዛሬው ትዕይንት ተጠባቂ አይደለም። ሰሞኑን ትህነግ ምርጫ አካሂዶ ጌታቸው ረዳ በድምጽ ብልጫ ማለፉ ይታወቃል። በቀጣይም የክልሉ የሽግግር ጊዜ ርዕሰ መስተዳድር ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። ሆኖም ለዘመናት በዓድዋ ያውም በአንድ ቤተሰብ ተይዞ የነበረው በዚህ መልኩ ማፈትለኩ የራያውን ጌታቸው ሹመት “በአማራ አንመራም” እንዲሉት አድርጓቸዋል። የዛሬውም ሰልፍ ይህንኑ ተከትሎ የጌታቸውን ሥልጣን ቀውስ ውስጥ ለመክተት የታሰበ ነው ተብሎ ይነገራል።

ዛሬ ከመቀሌ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው መለስ ካምፓስ የጦር ጉዳተኞች ማዕከል ተሰባስበው በመነሳት እስከ የትግራይ ክልል አስተዳደር መሥርያ ቤት የተለያዩ መፈክሮች እያሰሙ የተጓዙት እነዚህ የጦር ጉዳተኞች፥ ደረሰብን ያሉዋቸውን የአስተዳደር ችግሮች «ሕዝብ ይስማልን፣ ይወቅልን» ብለዋል ። «በኛ ስም ከሕዝብ የሚሰበሰብ መዋጮ እኛጋ እየደረሰ አይደለም»፣ «በተደጋጋሚ ጥያቄ ብናቀርብም ምላሽ አጥተናል» የሚሉት እነዚህ በአብዛኛው ወጣት የጦር ጉዳተኞች፥ «በቂ ምግብና ውኃ እንኳን አጥተን የከፋ ሁኔታ ላይ ነን» ሲሉ ገልፀዋል።

«የታጋዮች ድምፅ ይሰማ»፣ «ትኩረት ለጦር ጉዳተኞች»፣ «ተክደናል» የሚሉና ሌሎች ብልሹ አሠራሮች የሚያወግዙ መፈክሮች የጦር ጉዳተኞቹ ያሰሙ ነበር።

ሰልፈኞቹ «ድምፃችንን ለማሰማት ወደ ከተማ እንዳንገባ መቐለ ዩኒቨርስቲ አሪድ ካምፓስ አካባቢ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ጭምር እንድንበተን ሙከራ ተደርጓል» ሲሉ ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል።

ከፍተኛ የቁጣ ስሜት ይታይበት የነበረው የጦር ጉዳተኞቹ ሰልፍ በሃይማኖት አባቶች ሸምጋይነት እንዲረጋጋ ተደርጓል። ሰልፈኞቹ የክልሉ አስተዳደር መሥርያ ቤት በሆነው ደጀን ቢሮ በር በነበራቸው ቆይታ የሕወሓት ከፍተኛ አመራር ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ከሌሎች ወታደራዊ መሪዎች ጋር በችግሮቻቸው ዙሪያ ተወያይተዋል።

ሰልፈኞቹ ወራት ካለፈ በኋላ ዛሬ ጉዳታቸው ለምን እንደተሰማቸው ግልጽ ባይሆን የተቀናጀ የፖለቲካ ሤራ ይኖርበታል የሚል አስተያየት ይሰጣል። ከፌደራል መንግሥት የሚፈለጉት ነገሮ እየቀረቡና አንጻራዊ የኑሮ መረጋጋት በሚይታይበት ወቅት አካል ጉዳተኞቹ «ተክደናል» ብለው መውጣታቸው እስካሁን መከዳታቸውን እንዴት አላወቁም የሚል ጥያቄ ያስነሳ ሆኗል። ምክንያቱም አንድ ሚሊዮን የትግራይ ሰው በጦርነቱ መሞቱ በተለያዩ መንገዶች ሲገለጽ የሰነበተ ጉዳይ ነውና።

ከዚህ የአካል ጉዳየኞቹ ሰልፍ ሌላ በተናበበ መልኩ በሚመስል እስካሁን ሥልጣን በቁጥጥሩ ሥር ያደረገው የዓድዋው ቡድን ትናንት ባወጣው መግለጫ በትግራይ ሕዝብ ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ወንጀሎች ይቆሙ ዘንድ የአፍሪካ ኅብረትና የዓለም ማኅበረሰብ ትርጉም ያለው እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቋል። አሁንም ድረስ የኤርትራ ጦርና ሌሎች ታጣቂዎች በትግራይ ሕዝብ ላይ ወንጀል እየፈጸሙ ነው ያለው ድርጅቱ፣ ይህንን ለማስተካከል የአፍሪካ ኅብረትና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት እርምጃዎችን ሊወስዱ ይገባል ብሏል።

ባለፈው ሳምንት ኢትዮጵያን የጎበኙት የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን በሰብዓዊ መብቶች ስብሰባ ላይ ይህንኑ የህወሓት/ትህነግን ዓይነት ንግግር አድርገዋል። “ምንም ዓይነት የውጪ ሠራዊት በኢትዮጵያ የለም” ብለው የተናገሩ ብሊንከን ከትህነግ መግለጫ የተወሰደ የሚመስል ንግግር ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢቃወምም ሰውየውን ለዚህ መሰል የፖለቲካ አክሮባት ያበቃቸው ጉዳይ ሰሞኑን በአላማጣ ከተደረገውና የራያንና የወልቃይትን ጉዳይ ዕልባት ከተጠየቀው ትዕይንተ ሕዝብ ጋር ቁርኝት እንዳለው ይነገራል።

ብሊንከን በትዊተር መልዕክታቸው የጦር ወንጀል ተፈጽሟል ብለው ዛሬ የጻፉት መልዕክት በአብዛኛው ኢትዮጵያን በጎበኙብት ወቅት ከተናገሩት የተለየ ባይሆንም የቆየውን ነገር አሁን የተከሰተ አስመስለው የጻፉበት ሥልት ግን ማንን ለማስደሰት ያለመ እንደሆነ ከጽሁፋቸው መረዳት ይቻላል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይን (ህወሓት) ከአሸባሪነት ለመሰረዝ ነገ ረቡዕ መጋቢት 13፤ 2015 “ልዩ ጉባኤ” ሊያካሄድ መሆኑን የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ምንጮች ገለጹ። ሰባት የፓርላማ አባላት፤ ለነገው ልዩ ጉባኤ “ማንም አባል እንዳይቀር” ከሚል ማሳሰቢያ ጋር ጥሪ እንደተደረገላቸው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

እነዚሁ የምክር ቤት አባላት በነገው ዕለት “ልዩ ጉባኤ” እንደሚካሄድ ቢያረጋግጡም፤ ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር እንደሚደረገው የስብሰባው አጀንዳ አስቀድሞ እንዳልተላከላቸው አስታውቀዋል። የፓርላማ አባላቱ ይህን ቢሉም፣ የተወካዮች ምክር ቤት የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ምንጮች ግን በነገው ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኝነት የሚሰረዝ የውሳኔ ሃሳብ ይቀርባል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል።

የጌታቸው መመረጥ ይፋ ከሆነ ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያ ኢትዮጵያን የሚያናውጥ እና ዕረፍት የሚነሳ ሰበር ዜና በእጅጉ የቀነሰ ሲሆን ምንም የማይሰማባት ትግራይ ግን የማኅበራዊ ሚዲያ ትኩዳት እየሆነች መጥታለች። ከዚህ በፊት በትግራይ ፖለቲካ ብዙ ሲሉ የነበሩና በቅርቡ ግን ከሚዲያው ጠፍተዋል ወይም ሞተዋል ሲባሉ ከነበሩትም የዓድዋው ቡድን ደጋፊዎች ጥቂቶቹ ብቅ ማለት ጀምረዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Slider Tagged With: ethiopian terrorists, getachew reda, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule