• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ

February 25, 2026 11:24 am by Editor 1 Comment

በ1980ዎቹ ነበር፤ በዘመኑ ቀልድ የሚያበዛ ታዋቂ ጋዜጠኛ በአንድ የታወቀ ሪዞርት ሽንት ቤት ውስጥ አሳማ ያስቀምጣል። አሳማዋንም የከንፈር ቀለም (ሊፕስቲክ) ቀብቶ እንደ ሰው አስመስሎ። ዓላማው ሌላ ሳይሆን ፕራንክ ነበር። ክስተቱ የሪዞርቱን ባለቤት ፕራንክ አድርጎ ቢያልፍም ከዚያ በኋላ ግን አሳማ የከንፈር ቀለም ቢቀባ እንደ አሳማ መጮኹ (ኦይንክ ማድረጉ)፣ ጭቃ ላይ መንከባለሉ፣ አሰሱንም ገሰሱንም መብላቱ፣ … ባጠቃላይ አሳማነቱ አይቀርም ማለት ነው በሚል አባባል ተተካ።

ከዚያም በ90ዎቹ ለቴክሳስ ሀገረግዢነት ይወዳደሩ የነበሩት አን ሪቻርድስ አባባሉን ተጠቀሙበት። ትልቁ ቡሽ በምርጫ ውድድር በነበሩበት ጊዜ የቡሽ አስተዳደር ለውጥ እንደማያመጣ አን ሲናገሩ “ዌል የአሳማዋን ከንፈር ሊፕስቲክ ቀብቶ ሞኒካ ነሽ ሊሏት ይቻላሉ፤ ግን አሳማነቷ ፈጽሞ አይቀየርም” ነበር ያሉት።

በሀገራችን ፖለቲካ ከንፈሯን ቀለም ተቀብታ የመጣች ፓርቲ ኢህአፓ ነች። የሚገርመው ደግሞ አለማፈሯ፤ እና አሳማ አይደለሁም ብላ ለማሳመን መላላጧ።

የተማሪዎች እንቅስቃሴ የሚባለው እየተጋጋለ ሲሄድ ያንን ደሙ የተቆጣ ወጣት ጠልፋ ኢህአፓ የምትባል ፓርቲ ተመሠረተች። ማንነቷ አሁን ሊያሰማምሯት እንደሚፈልጉት ሳይሆን ለማስመሰልና ለማደናገር “ኢትዮጵያ” የሚል ስም የያዘች ግን ጸረ ኢትዮጵያ፣ ሀገር ከፋፋይና እና ተገንጣይ ፓርቲ ነበረች። ይህንን አባላቷ ብቻ ሳይሆኑ ሊቀ ተገንጧዮቹ ሻዕቢያና ትህነግም የሚመሰክሩት ነው።

በሶማሊያ ጦርነት ከወራሪው የሶማሊያ ጦር ጋር በማበር ስንቅና ትጥቅ ውስጥ የተፈጨ ጠርሙስና አሸዋ በመጨመር ኢህአፓ ጸረ ኢትዮጵያዊ ዓላማዋን ለማሳካት ሞክራለች። ስታዲየም ሶማሊያን የተቃወመ ትዕይንት ሲካሄድ ሶማሊያን ደግፋ ጩኸቷን አሰምታለች። ከሰሜን ተገንጣዮች ጋር እጅና ጓንት ሆና ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ተግታ ሠርታለች፤ ይህ ፈጠራ ሳይሆን የቀድሞ አባሎቿ የሚናገሩት ሐቅ ነው፤ ስፍር ቁጥር ከሌለው የኢህአፓ የክህደት ማንነት በጣም ጥቂቱ።

“የራስን ዕድል በራስ እስከ መገንጠል” የሚል መርዝ ኢትዮጵያ ውስጥ በመትከል የአንበሳውን ድርሻ የምትወስደው አሳማዋ ኢህአፓ ነች። ግን ስሟ ውስጥ “ኢትዮጵያ” የሚል ስለጨመረች ብቻ ኢትዮጵያዊነት አንግቤአለሁ በማለት ከንፈሯን ቀለም ስትቀባ የኖረችው ከቀድሞ እንደሆነ ያስመሰከረች ፓርቲ ነች።

የሻዕቢያው አንበል ኢሳያስ አፈወርቅ ለኢትዮጵያ ያዘነ ይመስል “የብሔር ፖለቲካ ለኢትዮጵያ አይመጥንም” ሲል ሁልጊዜ ይሰማል። ትህነግንም ሲያራክስ “የብሔር ፖለቲካ በኢትዮጵያ ላይ ሲያመጡ ልክ አይደለም ብዬ ረቂቅ ሕገመንግሥቱን ተቃውሜአለሁ” ይላል። ነግርግን ሸኔ፣ ፋኖ፣ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ትህነግ፣ … ማንኛውንም ኢትዮጵያን ለመገነጣጠል የሚሠራ ስሙ በ“ግ” የሚያልቅ ድርጅት ያስታጥቃል፣ ያደራጃል፣ ገዢ መሬት ይሰጣል፤ ወዘተ። አሳማዋ ኢህአፓ ውስጥ ያለው “ኢትዮጵያ” የሚለው ስምም እንዲሁ ነው።  

ኢህአፓ ሲበዛ ጨካኝ ናት። የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎችን ሳይቀር ምንም በማያውቁት የሚበተን ወረቀት ቦርሳቸው ውስጥ እያስደረገች በደርግ ታጣቂ በግፍ እንዲገደሉና ያንን ደግሞ ለፖለቲካ ዓላማ የተጠቀመች ስሜት ዓልባ፣ ርኅራኄ ዓልባ ፓርቲ ነች። እነ ጃዋርም እንዲሁ ነበር ያደረጉት፤ አሁንም እንዲሁ ለማድረግ ነው የተለያዩ አሳማዎች ዙሪያ የሚታዩት።

ኢህአፓ የወሰደችው የጭካኔ መንገድ ይህ ብቻ ሳይሆን መፍትሔ ጠብመንጃ አፈሙዝ ላይ ብቻ እንዳለ ዕድሜ ልኩን ሲሰለጥን ከኖረ የወታደር ስብስብ፣ ደርግ ጋር፣ የከተማው ውስጥ ሽብር፣ ነጭ ሽብር በማለት ግድያ የጀመረች ደም አፍሳሽ አሳማ ነች። ከዚያ ደግሞ ደርግ ቀይ ሽብር ፈጸመብኝ ብላ ከቀድሞ የፍቅር ጓደኛዋ ትህነግ ጋር ተስማምታ የነጭ ሽብር ሰለባዎች የሚል ሙዚየም ያስከፈተች ዓይንአውጣ ድርጅት ነች። ተመስገን ማዴቦ የማርያም አራስ ሚስቱን ጋንዲ ሆስፒታል ጠይቆ ሲወጣ አስፋልት ላይ የደፋው ማነው? ነው ወይስ ለቲክቶክ ፖስት በውሃ ሽጉጥ ፕራንክ ነው ያደረጉትና ድራማው ሲያልቅ ተነስቶ ሄዷል?

በሰው በላዋ ኢህአፓ ነጭ ሽብር የተጨፈጨፉትን ማን ያስታውሳቸው? ማን ሙዚየም ይሥራላቸው? ማን ሃውልት ያቁምላቸው? ቤተሰቦቻቸው ጭምር እንዳይናገሩና እንዳይመሰክሩ በኃፍረት ተሸማቅቀው፣ በጥፋተኝነት ስሜት አንገታቸውን ደፍተው እየኖሩ ነው።

ከኢህአፓ ጋር መቃረን አይቻልም። ይቺ ባህርይዋ አሁንም ከንፈሯን ቀይ ቀለም ተቀብታ ወደ አደባባይ ብቅ ያለችው ኢህአፓ ላይም በስፋት ይታያል። ኢህአፓን መቃወም ዋጋ ይስከፍላል፤ ሒደት አለው፤ አንድ ሰው በሃሳብ ማፈንገጥ ወይም ለየት ማለት ሲጀምር አንጃ በሚል ይፈረጃል፤ ከዚያ ጠላት ተብሎ ዒላማ ውስጥ ይገባል፤ ቀጣዩ ግምባሩን ብሎ መድፋት ነው። እነ ብርሃነመስቀል እና እጅግ ብዙዎች ለምንና በማን እንደተገደሉ ሞት የረሳቸው ኢህአፓዎች በራሳቸው አንደበት አሁንም የሚመሰክሩት ነው።  

ኮሚኒስቷ ኢህአፓ ጸረ ሃይማኖት ነች። ሞራል የሚባል ነገር ከውስጧ ተመጥጦ የወጣባት፤ የሰብዓዊነት ጠብታ የሌለባት፣ ጭከና ዋነኛ መሣሪያዋ የሆነ ድርጅት ናት። ሞራልና ሃይማኖትን ከወጣቱ አእምሮ ማጥፋታቸው በብዙ መልኩ ተገልጿል። ልጆች አዛውንት እናትና አባታቸውን፣ ዘመዶቻቸውን፣ አጎቶቻቸውን፣ ወዘተ ደርግ፣ ቡርዧ፣ ወዘተ እያስባሉ አሳልፈው ሰጥተዋል፤ ገድለዋል፤ አስገድለዋል። ይቺ ከጭከና ክምራቸው ቁልል አንዷ ሰበዝ ናት።

የሚገርመው ግን ቀይ ቀለም ተቀብተው የመጡት ያሁኖቹ አሳማዎች “ሃይማኖተኛ” መሆናቸው ነው። መሪው “መጋቢ ብሉይ” ተብለው ነው የሚጠሩት። ይህ የሃይማኖት ማዕረግ ነው። ብሉይ ኪዳንን የሚያስተምር አዋቂ፣ ምሑር ማለት ነው። ሰሞኑን “የዘመናችን ልደቱ” እየተባለች (ስያሜው ትንቢታዊ ይመስላል) የማኅበራዊ ሚዲያ ትኩሳት የሆነችው የምርጫ ክርክሩ ምሽት ባለማተብነቷን በገሃድ ማሳየት በጣም መፈለጓ ሌላ ጥያቄ የሚያጭር ጉዳይ ነው። ሤራ ቀለቧ የሆነው ባለሊፕስቲኳ ኢህአፓ ምን አስባ ይሆን?

ከንፈሯን ቀይ ቀለም በደማቁ ተቀብታ፣ ዓይኗን በጨው አጥባ ኮሚኒስት ሳልሆን ሶሻል ዴሞክራት ነኝ ብላ ስለመጣችው አሳማዋ ኢህአፓ የዱሮም ሆነ ያሁኑ ማንነት ማውራት እጅግ ይደክማል። ደግነቱ በሊፕስቲክ አይደለም በእንዶድ ሆነ ዓለም ላይ ባለ ቆሻሻ ማስለቀቂያ ቢያጥቡት የማይጸዳው ታሪካቸው ይጮኻል። ስለዚህ ብዙ ማለት አያስፈልግም። ግን በአንድ ነገር ላብቃ …

የቀድሞዋ ዋና ጸሐፊ ደስታ ጥላሁን ለሦስት ጊዜ መልቀቂያ አቅርባ በሦስተኛው ወጥታለች። የለቀቀችበት ምክንያቶች በቀጥታም በተዘዋዋሪ መንገድ ያለችው፤ ድርጅቱ አዲስ ሃሳብ ለመቀበል ራሱን ያላበቃ፣ የተቸከለ፣ ውስጣዊ ዴሞክራሲ የሌለው፣ አሁንም በሤራ የሚንቀሳቀስ፣ መረጃ የሚያፍን፣ ወገንተኛ፣ የሚቃወሙትን በአንጃነት የሚያይ፣ ለዘመናዊ አስተሳሰብ ራሱን ያላበቃ፣ በቀድሞው መሪዎቹ የሚዘወር፣ ወዘተ ነው።

ባጭሩ ኢህአፓ ቦጌ ቀይ ቀለም ከንፈሯን ተቀብታ ብትመጣም አሁንም ያው አሳማ ነች ማለት ነው።

ከጾታ እስከ ሥልጣን ደስታ ጥላሁን የተተካችው በባለማተቧ ሚስጥረሥላሴ ነው። 

መክብብ ማሞ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: Desta Tilahun, eprp, Mistreselassie, red terror, That Generation, White Terror

Reader Interactions

Comments

  1. Mark says

    February 25, 2026 10:41 pm at 10:41 pm

    Yes, in 70s you had massacred 1000s with the Derg. You thought you have whipped out EPRP from the face of the earth; but now when you know that EPRP survived, the nightmare becomes real and haunts you. Even if you do not publicly declare it to do what you had done before, you continued carrying out the massacre as you are accustomed to with prosperity party day and night. That’s because the Sun is setting on you, and your end has coming with the prosperity.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule