• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ

February 25, 2026 11:24 am by Editor 2 Comments

በ1980ዎቹ ነበር፤ በዘመኑ ቀልድ የሚያበዛ ታዋቂ ጋዜጠኛ በአንድ የታወቀ ሪዞርት ሽንት ቤት ውስጥ አሳማ ያስቀምጣል። አሳማዋንም የከንፈር ቀለም (ሊፕስቲክ) ቀብቶ እንደ ሰው አስመስሎ። ዓላማው ሌላ ሳይሆን ፕራንክ ነበር። ክስተቱ የሪዞርቱን ባለቤት ፕራንክ አድርጎ ቢያልፍም ከዚያ በኋላ ግን አሳማ የከንፈር ቀለም ቢቀባ እንደ አሳማ መጮኹ (ኦይንክ ማድረጉ)፣ ጭቃ ላይ መንከባለሉ፣ አሰሱንም ገሰሱንም መብላቱ፣ … ባጠቃላይ አሳማነቱ አይቀርም ማለት ነው በሚል አባባል ተተካ።

ከዚያም በ90ዎቹ ለቴክሳስ ሀገረግዢነት ይወዳደሩ የነበሩት አን ሪቻርድስ አባባሉን ተጠቀሙበት። ትልቁ ቡሽ በምርጫ ውድድር በነበሩበት ጊዜ የቡሽ አስተዳደር ለውጥ እንደማያመጣ አን ሲናገሩ “ዌል የአሳማዋን ከንፈር ሊፕስቲክ ቀብቶ ሞኒካ ነሽ ሊሏት ይቻላሉ፤ ግን አሳማነቷ ፈጽሞ አይቀየርም” ነበር ያሉት።

በሀገራችን ፖለቲካ ከንፈሯን ቀለም ተቀብታ የመጣች ፓርቲ ኢህአፓ ነች። የሚገርመው ደግሞ አለማፈሯ፤ እና አሳማ አይደለሁም ብላ ለማሳመን መላላጧ።

የተማሪዎች እንቅስቃሴ የሚባለው እየተጋጋለ ሲሄድ ያንን ደሙ የተቆጣ ወጣት ጠልፋ ኢህአፓ የምትባል ፓርቲ ተመሠረተች። ማንነቷ አሁን ሊያሰማምሯት እንደሚፈልጉት ሳይሆን ለማስመሰልና ለማደናገር “ኢትዮጵያ” የሚል ስም የያዘች ግን ጸረ ኢትዮጵያ፣ ሀገር ከፋፋይና እና ተገንጣይ ፓርቲ ነበረች። ይህንን አባላቷ ብቻ ሳይሆኑ ሊቀ ተገንጧዮቹ ሻዕቢያና ትህነግም የሚመሰክሩት ነው።

በሶማሊያ ጦርነት ከወራሪው የሶማሊያ ጦር ጋር በማበር ስንቅና ትጥቅ ውስጥ የተፈጨ ጠርሙስና አሸዋ በመጨመር ኢህአፓ ጸረ ኢትዮጵያዊ ዓላማዋን ለማሳካት ሞክራለች። ስታዲየም ሶማሊያን የተቃወመ ትዕይንት ሲካሄድ ሶማሊያን ደግፋ ጩኸቷን አሰምታለች። ከሰሜን ተገንጣዮች ጋር እጅና ጓንት ሆና ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ተግታ ሠርታለች፤ ይህ ፈጠራ ሳይሆን የቀድሞ አባሎቿ የሚናገሩት ሐቅ ነው፤ ስፍር ቁጥር ከሌለው የኢህአፓ የክህደት ማንነት በጣም ጥቂቱ።

“የራስን ዕድል በራስ እስከ መገንጠል” የሚል መርዝ ኢትዮጵያ ውስጥ በመትከል የአንበሳውን ድርሻ የምትወስደው አሳማዋ ኢህአፓ ነች። ግን ስሟ ውስጥ “ኢትዮጵያ” የሚል ስለጨመረች ብቻ ኢትዮጵያዊነት አንግቤአለሁ በማለት ከንፈሯን ቀለም ስትቀባ የኖረችው ከቀድሞ እንደሆነ ያስመሰከረች ፓርቲ ነች።

የሻዕቢያው አንበል ኢሳያስ አፈወርቅ ለኢትዮጵያ ያዘነ ይመስል “የብሔር ፖለቲካ ለኢትዮጵያ አይመጥንም” ሲል ሁልጊዜ ይሰማል። ትህነግንም ሲያራክስ “የብሔር ፖለቲካ በኢትዮጵያ ላይ ሲያመጡ ልክ አይደለም ብዬ ረቂቅ ሕገመንግሥቱን ተቃውሜአለሁ” ይላል። ነግርግን ሸኔ፣ ፋኖ፣ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ትህነግ፣ … ማንኛውንም ኢትዮጵያን ለመገነጣጠል የሚሠራ ስሙ በ“ግ” የሚያልቅ ድርጅት ያስታጥቃል፣ ያደራጃል፣ ገዢ መሬት ይሰጣል፤ ወዘተ። አሳማዋ ኢህአፓ ውስጥ ያለው “ኢትዮጵያ” የሚለው ስምም እንዲሁ ነው።  

ኢህአፓ ሲበዛ ጨካኝ ናት። የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎችን ሳይቀር ምንም በማያውቁት የሚበተን ወረቀት ቦርሳቸው ውስጥ እያስደረገች በደርግ ታጣቂ በግፍ እንዲገደሉና ያንን ደግሞ ለፖለቲካ ዓላማ የተጠቀመች ስሜት ዓልባ፣ ርኅራኄ ዓልባ ፓርቲ ነች። እነ ጃዋርም እንዲሁ ነበር ያደረጉት፤ አሁንም እንዲሁ ለማድረግ ነው የተለያዩ አሳማዎች ዙሪያ የሚታዩት።

ኢህአፓ የወሰደችው የጭካኔ መንገድ ይህ ብቻ ሳይሆን መፍትሔ ጠብመንጃ አፈሙዝ ላይ ብቻ እንዳለ ዕድሜ ልኩን ሲሰለጥን ከኖረ የወታደር ስብስብ፣ ደርግ ጋር፣ የከተማው ውስጥ ሽብር፣ ነጭ ሽብር በማለት ግድያ የጀመረች ደም አፍሳሽ አሳማ ነች። ከዚያ ደግሞ ደርግ ቀይ ሽብር ፈጸመብኝ ብላ ከቀድሞ የፍቅር ጓደኛዋ ትህነግ ጋር ተስማምታ የነጭ ሽብር ሰለባዎች የሚል ሙዚየም ያስከፈተች ዓይንአውጣ ድርጅት ነች። ተመስገን ማዴቦ የማርያም አራስ ሚስቱን ጋንዲ ሆስፒታል ጠይቆ ሲወጣ አስፋልት ላይ የደፋው ማነው? ነው ወይስ ለቲክቶክ ፖስት በውሃ ሽጉጥ ፕራንክ ነው ያደረጉትና ድራማው ሲያልቅ ተነስቶ ሄዷል?

በሰው በላዋ ኢህአፓ ነጭ ሽብር የተጨፈጨፉትን ማን ያስታውሳቸው? ማን ሙዚየም ይሥራላቸው? ማን ሃውልት ያቁምላቸው? ቤተሰቦቻቸው ጭምር እንዳይናገሩና እንዳይመሰክሩ በኃፍረት ተሸማቅቀው፣ በጥፋተኝነት ስሜት አንገታቸውን ደፍተው እየኖሩ ነው።

ከኢህአፓ ጋር መቃረን አይቻልም። ይቺ ባህርይዋ አሁንም ከንፈሯን ቀይ ቀለም ተቀብታ ወደ አደባባይ ብቅ ያለችው ኢህአፓ ላይም በስፋት ይታያል። ኢህአፓን መቃወም ዋጋ ይስከፍላል፤ ሒደት አለው፤ አንድ ሰው በሃሳብ ማፈንገጥ ወይም ለየት ማለት ሲጀምር አንጃ በሚል ይፈረጃል፤ ከዚያ ጠላት ተብሎ ዒላማ ውስጥ ይገባል፤ ቀጣዩ ግምባሩን ብሎ መድፋት ነው። እነ ብርሃነመስቀል እና እጅግ ብዙዎች ለምንና በማን እንደተገደሉ ሞት የረሳቸው ኢህአፓዎች በራሳቸው አንደበት አሁንም የሚመሰክሩት ነው።  

ኮሚኒስቷ ኢህአፓ ጸረ ሃይማኖት ነች። ሞራል የሚባል ነገር ከውስጧ ተመጥጦ የወጣባት፤ የሰብዓዊነት ጠብታ የሌለባት፣ ጭከና ዋነኛ መሣሪያዋ የሆነ ድርጅት ናት። ሞራልና ሃይማኖትን ከወጣቱ አእምሮ ማጥፋታቸው በብዙ መልኩ ተገልጿል። ልጆች አዛውንት እናትና አባታቸውን፣ ዘመዶቻቸውን፣ አጎቶቻቸውን፣ ወዘተ ደርግ፣ ቡርዧ፣ ወዘተ እያስባሉ አሳልፈው ሰጥተዋል፤ ገድለዋል፤ አስገድለዋል። ይቺ ከጭከና ክምራቸው ቁልል አንዷ ሰበዝ ናት።

የሚገርመው ግን ቀይ ቀለም ተቀብተው የመጡት ያሁኖቹ አሳማዎች “ሃይማኖተኛ” መሆናቸው ነው። መሪው “መጋቢ ብሉይ” ተብለው ነው የሚጠሩት። ይህ የሃይማኖት ማዕረግ ነው። ብሉይ ኪዳንን የሚያስተምር አዋቂ፣ ምሑር ማለት ነው። ሰሞኑን “የዘመናችን ልደቱ” እየተባለች (ስያሜው ትንቢታዊ ይመስላል) የማኅበራዊ ሚዲያ ትኩሳት የሆነችው የምርጫ ክርክሩ ምሽት ባለማተብነቷን በገሃድ ማሳየት በጣም መፈለጓ ሌላ ጥያቄ የሚያጭር ጉዳይ ነው። ሤራ ቀለቧ የሆነው ባለሊፕስቲኳ ኢህአፓ ምን አስባ ይሆን?

ከንፈሯን ቀይ ቀለም በደማቁ ተቀብታ፣ ዓይኗን በጨው አጥባ ኮሚኒስት ሳልሆን ሶሻል ዴሞክራት ነኝ ብላ ስለመጣችው አሳማዋ ኢህአፓ የዱሮም ሆነ ያሁኑ ማንነት ማውራት እጅግ ይደክማል። ደግነቱ በሊፕስቲክ አይደለም በእንዶድ ሆነ ዓለም ላይ ባለ ቆሻሻ ማስለቀቂያ ቢያጥቡት የማይጸዳው ታሪካቸው ይጮኻል። ስለዚህ ብዙ ማለት አያስፈልግም። ግን በአንድ ነገር ላብቃ …

የቀድሞዋ ዋና ጸሐፊ ደስታ ጥላሁን ለሦስት ጊዜ መልቀቂያ አቅርባ በሦስተኛው ወጥታለች። የለቀቀችበት ምክንያቶች በቀጥታም በተዘዋዋሪ መንገድ ያለችው፤ ድርጅቱ አዲስ ሃሳብ ለመቀበል ራሱን ያላበቃ፣ የተቸከለ፣ ውስጣዊ ዴሞክራሲ የሌለው፣ አሁንም በሤራ የሚንቀሳቀስ፣ መረጃ የሚያፍን፣ ወገንተኛ፣ የሚቃወሙትን በአንጃነት የሚያይ፣ ለዘመናዊ አስተሳሰብ ራሱን ያላበቃ፣ በቀድሞው መሪዎቹ የሚዘወር፣ ወዘተ ነው።

ባጭሩ ኢህአፓ ቦጌ ቀይ ቀለም ከንፈሯን ተቀብታ ብትመጣም አሁንም ያው አሳማ ነች ማለት ነው።

ከጾታ እስከ ሥልጣን ደስታ ጥላሁን የተተካችው በባለማተቧ ሚስጥረሥላሴ ነው። 

መክብብ ማሞ

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: Desta Tilahun, eprp, Mistreselassie, red terror, That Generation, White Terror

Reader Interactions

Comments

  1. Mark says

    February 25, 2026 10:41 pm at 10:41 pm

    Yes, in 70s you had massacred 1000s with the Derg. You thought you have whipped out EPRP from the face of the earth; but now when you know that EPRP survived, the nightmare becomes real and haunts you. Even if you do not publicly declare it to do what you had done before, you continued carrying out the massacre as you are accustomed to with prosperity party day and night. That’s because the Sun is setting on you, and your end has coming with the prosperity.

    Reply
  2. Yared says

    March 28, 2026 10:04 am at 10:04 am

    In my opinion, in late 1970’s EPRP attempt to overthrow the Derg was so radical. and it’s subsequent

    Derg’s infamous Red terror brought EPRP leaders demise and almost a million lives. But, I don’t

    think it’s fair to criminate them based on their past. The current leader’s shall not be accountable.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule