* የተዘነጋው የኢህአፓ ነጭ ሽብርና የወቅቱ ኢህአፓ አካሄድ ነጭ ሽብርም ሆነ ቀይ ሽብር በቀለም መጠሪያቸው ካልተለያዩ በቀር ሁለቱም ሽብር ናቸው። መስከረም 21 ቀን 1969 ዓ.ም. አዲስ አበባ ሞርጌጅ ህንጻ ውስጥ ትሠራ የነበረችውን ባለቤታቸውን መኪናቸው ውስጥ ሆነው በመጠባበቅ ላይ እያሉ አድብተው ይጠብቁ በነበሩ የኢሕአፓ ነፍሰ ገዳዮች በቅርብ ርቀት በተተኮሰ ጥይት ሕይወታቸው ያለውፈው በወቅቱ በሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት የጊዜያዊ ጉዳዮች ሰብሳቢ የነበሩት ዶ/ር ፍቅሬ መርዕድ ነጭ ሽብር ከበላቸው ዜጎች አንዱና ነጭ ሽብር ራሱን ያስተዋወቀበት ኦፕሬሽኑ ነው። ሚስታቸውን ጋንዲ ሆስፒታል ጠይቀው ሲወጡ ቀይ መስቀል አካባቢ አድፍጠው ሲጠብቋቸው በነበሩ የኢህአፓ ነፍሰ ገዳዮች የተገደሉት ሌላው ነጭ ሽብር የበላቸው ዜጋ የወቅቱ የኢሰማኮ ሊቀመንበር የነበሩት ተመስገን … [Read more...] about ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር?

