• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ?

February 19, 2025 06:00 pm by Editor Leave a Comment

ቴድሮስ አድሃኖም አዲስ አበባ አልመጣም!

መሠረተቢሱ መሠረት ሚዲያ!

ራሱን “ዓለምአቀፋዊ ጋዜጠኛ” ብሎ በመሰየም ለፈረንጅ ሚዲያ መሥራት እና አገርን መሸጥ፣ ባንዳ መሆንን ጌጡ ያደረገው ኤሊያስ መሠረት ህወሃት/ትህነግ ከመንበሯ ከተነቀለች ጊዜ ጀምሮ በዋንኛነት የያዘው አጀንዳ መርዘኛ ፕሮፓጋንዳውን በ“መረጃ” ስም መትፋት ነው።

ከጥቂት ሳምንታት በፊት የፋኖ ትግል መሪ የሆነውን እስክንድር ነጋን ፊት ለፊት በማድረግ “ከመንግሥት ጋር በውጪ ድርድር እንዲደረግ የፋኖ ክንፍ ጠየቀ” ብሎ የሐሰት ወሬ በትኖ ነበር። ይህ ሆን ብሎ የፋኖ ኃይሎችን ለመበታተን እና አንድነት በመካከላቸው እንዳፈጠር ያስወራው ተራ አሉባልታ እንደሆነ ራሱ እስክንድር ወጥቶ ተናግሯል። መሠረተ ቢሱ ኤሊያስ ይህንን መረጃ ካወጣ በኋላ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ “ይህ ሰው ያኔ ለወያኔ እንደሠራ አሁንም ለብልፅግና መሥራት ጀመረንዴ” ብለው አስተያየት የሰጡ ተስተውለዋል።

ከዚህ በፊት ኤሊያስ ከወያኔዎች ጋር በተለይም አየር መንገዱን የግል ቤቱ ካደረገው ተወልደ ገብረመድኅን ጋር በቅርበት ይሠራ እንደነበር ብዙ ሲባልበት ነበር። ተወልደም ለውለታው ኤሊያስን ለጫጉላው ሞሪሺየስ የነጻ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት እንደሰጠው ስዩም ተሾመ ማስረጃዎቹን በማሳየት በገሃድ የተናገረው እውነታ ነው። የመረጃ ተዓማኒነትን እመዝናለሁ (ፋክት ቼክ) የሚለው ኤሊያስ፤ ተወልደ ቦሌ ኤርፖርት እስር ቤት እንደነበረው አንድም ጊዜ ሳይነግረን ለመቅረቱ ምንም ያለው ነገር የለም። መቼም አያፍርም “አላውቅም ነበር” ነው የሚለው።

ኤሊያስ ግን ሌላ የሚያውቀው መረጃ አለ፤ ያውም ከማንም በፊት የሚሰማው መረጃ። ያው እንደተመለደው “ምንጮቻችን” ነው የሚላቸው። ተወልደ አየር መንገዱን ዘርፎ ከአገር ሲኮበልል ቀድሞ ያወቀው ኤሊያስ ነበር። ከዚያም አሜሪካ ሲገባ፤ ከዚያም ዴልታ አየር መንገድ ሲቀጥረው ከተወልደ ቤተሰቦች ቀድሞ መረጃውን የሰበረው ኤሊያስ ነበር። ማን ይሆን የነገረው?

ኤሊያስ ለአሶሺየትድ ፕሬስ ሲዘግብ በነበረበት ዘመን ወያኔ /ትህነግ ሰዎች በየእስር ቤቱ እጅግ ሰቅጣጭ በሆነ መንገድ ያሰቃይ እንደነበር አንዴም ተናግሮ አያውቅም። ያው “አላውቅም ነበር” ነው የሚለው። እውነት ነው ሞሪሺየስ ሲዝናና ስለነበር አያውቅም።

ትህነግ/ህወሃት በየቀኑ ሚዲያ በሚባለው በሙሉ ሙልጭ ያለ የሐሰት ዜና ሲያቀርብ፤ በጋምቤላ 424 ንጹሐንን ከመሬታቸው ለማፈናቀል ብሎ ሲጨፈጭፋቸው አንዴም ለየትኛውም የውጪ ዜና አገልግሎት ዘግቦ አያውቅም። ያው “አላውቅም ነበር” ነው የሚለው። ግን የጋምቤላ ጭፍጨፋ በየዓመቱ ታኅሳስ ወር ሲከበር አንዴም ሰምቶ አያውቅም? ወያኔ በሚሰፍርለት ዳረጎት ከርሱን እየሞላ ስለነበር አይታየውም ነበር።

ሰሞኑን የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ከመጀመሩ 15 ቀናት በፊት ኤሊያስ የትህነጉን ሰው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም አዲስ አበባ ይመጣል ብሎ በእርግጠኛነት አወራ። ዜና ብሎ አወጣ፤ በዜናው ላይም “ለመሠረት ሚዲያ የደረሰው መረጃ” ብሎ የቴድሮስን መምጣት አስረግጦ ተናገረ። ይህም ሳያንሰው በዚሁ “ዜናው” ላይ ቴድሮስ ዳግም እንዳይመረጥ “የመንግሥት ሚዲያዎችና የመንግሥት ባለሥልጣናት ዘመቻ ከፍተውባቸው” ነበር ብሎ አስተዛዘነለት። ግን ለምን እንዳይመረጥ እንደዘመቱበት ትንፍሽ አላለም። ለምን ይሆን?

ቴድሮስ አድሃኖም ገብረኢየሱስ ድጋሚ እንዳይመረጥ ከመንግሥት ይልቅ በርትተው የሠሩት የማኅበራዊ ሚዲያ ሰዎች ናቸው። ወይም በሌላ አነጋገር የዓለም ሕዝብ ነው። ከኢትዮጵያ ሕዝብ በላይ ከኮሮና ጋር በተያያዘ ቴድሮስ ከሥልጣኑ እንዲለቅቅ ዘመቻ የከፈተበት የዓለም ሕዝብ ነው። ከአንድ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ቴድሮስ ይልቀቅ ብሎ ፔቲሽን የፈረመበት ወንጀለኛ ነው። ይህንን ባንዳው ኤሊያስ አይጽፍም። ለምን ይሆን?

እኔ እንደ ኤሊያስ ስላልሆንሁ ሌላውንም መረጃ ልንገራችሁ፤ ቴድሮስ ከሥልጣን መልቀቅ የለበትም ብለው “ኤሊያስና ጓደኞቹ” የድጋፍ ፊርማ አሰባስበውለታል። ፔቲሽኑን የጀመረለት ሚካኤል ገብረኢየሱስ ነው ይላል፤ 18ሺ ያልሞላ ፊርማ ተሰብስቦለታል፤ ያው ኤሊያስ ካለው የጥቅም ትሥሥርና ዝምድ አኳያ አልፈረምም ትላላችሁ?   

ወደ ጉዳዩ ስመለስ ቴድሮስ አድሃኖም ገብረኢየሱስ፤ ኤሊያስ መሠረት አዲስ አበባ ይመጣል ብሎ እንዳወራለት ሳይመጣ ቀርቷል። ለምን ቀረ? ማን ጠየቀ? ደጋፊዎቹ ብቻ “መረጃ” እያለ የሚለቅላቸውን እያጋበሱ “ኤላ አንተ ትለያለህ” እያሉ ሳክስ ይነፉታል፤ እሱም እንደ ፊኛ ዝም ብሎ ይነፋል፤ ያብጣል።

ቴድሮስ ያልመጣው ግን በብዙ ምክንያቶች ነው። አንዳንዶቹ አስቂኝ ሌሎቹ ደግሞ አዛኝና አሳፋሪ ስለሆኑ እዚህ ላይ ለመናገር ስለማይመጥኑ ትቼዋለሁ። ሌላው ግን የወያኔ/ትህነግ (የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር) ዓለምአቀፍ አሸባሪ የወንበዴ ቡድን የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት ለማክበር በአስመራጭ ኮሚቴነት እያገለገለ ስለነበር ሥራ በዝቶበት ነው ብለው “ምንጮቼ ነግረውኛል” ልበል እንደ ኤሊያስ? ምን ያንሰኛል?

ኤሊያስ “ፋክት ቼክ” አድራጊ ነኝ ብሎ ራሱን ሾሞ በዚህ በገነባው ስም አሁን ደግሞ ትክክለኛ መረጃ አቅራቢ ነኝ ብሎ ዓይኑን በጨው አጥቦ የመጣ ድንቁርናው በረከት የሆነለት የተሸጠ ባንዳ ነው። እውነተኛ ፋክት ቼክ አድራጊ ቢሆን የቴድሮስን አለመምጣት በተመለከተ ማስተካከያ መስጠት ነበረበት። ይህንን ካነበብህ በኋላ ቀኑን ወደኋላ አድርገህ ከሰጠህ በዚህ ዲጂታል ዘመን አታመልጥም፤ ትያዛለህ።  

ቴድሮስ ይመጣል ብሎ ማን ነገረህ? መረጃህ ትክክል ከነበረና ከቀረ ለምንድነው የቀረበትን ምክንያት ያልተናገርኸው? እኔው ልመልስልህ፤ አንተ ዓላማህ አጀንዳ መስጠት፤ ሕዝብን የሚጠቅም ሥራና አሠራር ማንቋሸሽ፣ ማራከስ ነው። ይህንን ደግሞ ለከፋዮችህ ተጠንቅቀህ የምትሠራው ነው። እነሱ ደግሞ ለባንዳነትህ ዳረጎት ይወረውሩልሃል፤ በዚያች ከርስህን ትሞላና አገር ላይ ትተፋለህ። አቤት ውርደት! አቤት ዝቅጠት!

ከመጨረሴ በፊት አንድ ነገር ልጠይቅህና ላብቃ፤ “ዓለምአቀፉ ጋዜጠኛ እያለ የሚያሞካሽህ” ቲክቫህ ለምንድነው “የመሠረት ሚዲያን” ዜና የማያትመው? ወይም ጠቅሶ የማይጽፈው? መሠረተቢስ ሆኖበት ይሆን? ኤላ ፋክት ቼክ ላድርግልንዴ?

ወዳጆቼ፤ ስለ ኤሊያስ የባንዳነት ተግባር፤ አሁን የት እንዳለ፤ ኬኒያ ከነማን ጋር እንደሚሠራ፤ መረጃ የሚጽፉለት እነማን እንደሆኑ የምመለስበት ጉዳይ ነው።

አሁንም ግን ደግሜ እላለሁ፤ ቴድሮስ አድሃኖም አዲስ አበባ አልመጣም፤ ኤሊያስ መሠረት “መረጃ አለኝ” ብሎ ያወራው ውሸት ነው፤ መሠረት ሚዲያ የዘገበው መሠረተ ቢስ መረጃ ነው። (ሁሉም ፎቶዎች በጸሐፊው የተላኩ ናቸው)

መሠረት አታላይ ነኝ ከዴንቨር


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: Elias Meseret, fake news, Meseret Media, Misleading News

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule