የአሜሪካንን ዜግነት ለመውሰድ ቀኝ እጅን ወደ ላይ ቀስሮ መማል ግድ ነው። እከሌ ከገሌ ሳይባል “ቀደም ሲል የነበረኝን ዜግነት እክዳለሁ” በማለት የሚከናወነው ምህላ “እግዚአብሔር ይርዳኝ” በሚል ማሳረጊያ ይቋጫል። “ቀደም ሲል የነበረኝን ዜግነቴን፣ የማንኛውንም የልዑል፣ የግዛት፣ የአገር፣ ወይም የሉዓላዊ መንግሥት ተገዢነቴን በሙሉና በፍጹም መካዴን በምሕላ አውጃለሁ" በሚል የሚከናወነው የመሐላ አሰጣጥ፣ ምሕላውን በፍጹምና ያለምንም ማወላዳት መቅበልን የሚጠይቅ ሲሆን ይህንንም ቀኝ እጅ በማውጣት የሚከናወን ሥርዓት ነው። Oath"I hereby declare, on oath, that I absolutely and entirely renounce and abjure all allegiance and fidelity to any foreign prince, potentate, state, or … [Read more...] about አወዛጋቢው የአቡነ ጴጥሮስ የጉዞ ሰነድ
News
ዜና
ትህነግ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያካሂደውን ሽብር እንደሚቀጥል አስታወቀ
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትሕነግ) በማለት ራሱን የሚጠራው ቡድን በዓለምአቀፉ የአሸባሪ ቋት ተመዝግቦ የሚገኘው የወንበዴዎች ስብስብ ነው። ከስድሳ ቀናት በላይ ስብሰባ ተቀምጦ የነበረው ትህነግ የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደሚገባው አልተተገበረም በሚል በመንግሥት ላይ የተቃውሞ መግለጫ አውጥቶ ነበር። በቀጣይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በጥር 23 ቀን 2016 ዓም ለትሕነግ መግለጫ አጸፋ ምላሽ የሰጠ ሲሆን በዋነኝነት ስምምነቱን ለመተግበር መንግሥት እንዴት ከሚገባው በላይ ርቀት እንደሄደ የጠቆመ ነበር። እንደ ማሳያም ከስምምነቱ ወዲህ መንግሥት ለትግራይ ክልል ከ37 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን ገልጾዋል። ለዚህ የመንግሥት ምላሽ ትሕነግ የአጸፋ ምላሽ ሰኞ የሰጠ ሲሆን ለክልሉ የተደረገውን 37 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ምንም ዓይነት ዕውቅና ሳይሰጥ የፕሪቶሪያው … [Read more...] about ትህነግ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያካሂደውን ሽብር እንደሚቀጥል አስታወቀ
ከትሕነግ ጋር ለማበር ወልቃይትን መስዋዕት የሚያደርጉ የ”አማራ ነጻ አውጪዎች”
ከትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትሕነግ) ጋር አብሮ "የጠብ መንጃ ትግሉን ማጧጧፍ" በሚል ከውሳኔ የደረሱ ክፋይ የ"አማራ ነጻ አውጪ" ኃይሎች መኖራቸው ተሰማ። ለስምምነቱ ትሕነግ ምዕራብ ትግራይ የሚለውንና አሁን "ነጻ ወጥቷል" የሚባለውን ወልቃይት ተላልፎ እንዲሰጥ ፈቃደኝነት ያለበት እንደሆነ ተመልክቷል። ራሳቸውን በተለያዩ አካባቢያዊና አደረጃጀት ከሰየሙት መካከል አሁን አንድ ለመሆን እየሠሩ እንደሆነ የሚነገርላቸው በዝናቡ የሚመራው የጎጃም ዕዝና የዘመነ ካሴ ኃይል ነው ይህን ስምምነት ለማድረግ እየሠራ እንደሆነ የተሰማው። “ጊዜው አሁን ነው፤ ይህንን ጊዜ ልንጠቀምበት ይገባል” በሚል በገሃድ ወልቃይትን ዳግም በኃይል ለመያዝ ደብረጽዮን በቅርቡ መናገሩ ይታወሳል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ከሕዝብ ጋር በተለያዩ ከተሞች ውይይት ያደረገው ጌታቸው ረዳም “እኛ ሥራችንን መሥራት … [Read more...] about ከትሕነግ ጋር ለማበር ወልቃይትን መስዋዕት የሚያደርጉ የ”አማራ ነጻ አውጪዎች”
ፋኖና ኦነግ ሸኔ “ነውጠኛ ቡድኖች” በመባላቸው ለጥገኝነት ማመልከቻ ተቀባይ እንደማይሆኑ ተሰማ
ፋኖና ኦነግ ሸኔ በማጣቀስ በውጭ አገራት የሚቀርቡ የጥገኝነት መጠየቂያ ማመልከቻዎች ተቀባይነት እንደማያገኙ ይህንኑ ጉዳይ በማስፈጸም የሚሠሩ አንድ ባለሙያ ለጎልጉል ጥቆማ ሰጡ። ድርጅቶቹ “ነውጥ ቡድኖች" ወይም “violent group s” በሚል የተፈረጁበት አግባብ መኖሩንም አክለው ገልጸዋል። ከአገራቸው በተለያዩ ምክንያቶች ተሰድደው ጥገኝነት የሚጠይቁ ወገኖች ከለላ ለማግኘት በሚያስገቡት የስደተኝነት ማመልከቻ በአሁኑ ሰዓት እንደየብሔራቸው ወይም ብሔራቸውን በመቀየር በብዛት በማስረጃነት የሚጠቀሙት የፋኖና የኦነግ ሸኔን ትግል እንደሆነ ይታወቃል። “ለምሳሌ በካናዳ ድርጅቶቹ “violent groups” ተብለዋል" የሚሉት የሕግ ባለሙያ ይህን የተረዱት በሥራቸው አማካይነት የደንበኞቻቸውን ጉዳይ ሲከታተሉ ነው። ባለሙያው ከተሞቹን ለይተው በስም ባይጠሩም መረጃውን የሰሙት … [Read more...] about ፋኖና ኦነግ ሸኔ “ነውጠኛ ቡድኖች” በመባላቸው ለጥገኝነት ማመልከቻ ተቀባይ እንደማይሆኑ ተሰማ
“ዐቢይን ግንባሩን ብለህ ዳዊት ሁን” ያሉት አቡነ ሉቃስ ክስ ተመሰረተባቸው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን እንደ ጎልያድ በማስመሰል በአንድ ምሳሌያዊ ዳዊት እንዲግደሉ የሃይማኖታዊ ግድያ ጥሪ ያስተላለፉት አቡን ሉቃስ የወንጀል ክስ ተመሠረተባቸው። አቡነ ሉቃስ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 247 እና 251 ድንጋጌ ተላልፈዋል በሚል ክስ ተመሰረተባቸው፡፡ ክሱ የቀረበባቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ሕገመንግስታዊና በሕገመንግስት ስርዓት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮች ችሎት ነው። በአቡነ ሉቃስ ላይ ሁለት ክሶችን ያቀረበው የፍትሕ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ ነው፡፡ ይህም ተከሳሽ አቡነ ሉቃስ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 247 (ሐ) እና አንቀጽ 258(ሀ) ስር የተደነገገውን ድንጋጌ እንዲሁም የወንጀል ህግ አንቀጽ 251 (ሐ) እና አንቀጽ 258 ስር … [Read more...] about “ዐቢይን ግንባሩን ብለህ ዳዊት ሁን” ያሉት አቡነ ሉቃስ ክስ ተመሰረተባቸው
አል ሸባብ ሦስት የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ካምፖችን ተቆጣጠረ
አልሸባብ ጋልሙዱግ በሚባል ክልል ከሶማሌ ጦር ጋር ባደረገው ውጊያ ሶስት የሶማሊያ ጦር ካምፖችን በቁጥጥሩ ስር አድርጓል። አል ሸባብ ከሶማሊያ ጦር ጋር አምስት ሰዓታት ያህል የቆየ ከባድ ጦርነት ካካሄደ በኋላ ከጥቃቱ የተረፉ የሶማሌ ብሄራዊ ጦር የ"ጎርጎር ኮማንዶ" መኮንኖችና ወታደሮች እንደተናገሩት በውጊያው ከ230 በላይ የሶማሊያ ወታደሮች መሞታቸውን እንዳረጋገጡና ስፍር ቁጥር የሌላቸው መቁሰላቸውን ገልፀዋል። የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር በቦታው ያሰፈራቸው ወታደሮቹ 4 ሻለቃ የ"ጎርጎር ኮማንዶዎችን" ሲሆን 15 የአል ሸባብ አሸባሪዎች ጋር ባደረገው ውጊያ ከፍተኛ ሞትና የአካል ጉዳት አስተናግዷል።የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር በአል ሸባብ ከበባ ውስጥ ሆኖ ምንም ዓይነት የሽፋን ኃይል ማሰማራት አልተቻለውም ተብሏል።ፕሬዝደንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በአል ሸባብ የሽብር ቡድን ላይ … [Read more...] about አል ሸባብ ሦስት የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ካምፖችን ተቆጣጠረ
ፑንትላንድ ለኢትዮጵያ ወደብ በነጻ እሰጣለሁ አለች
የሶማሊላንድና አሜሪካ የጦር ሰፈር ስምምነት ያደርጋሉ ከሶማሊያ ራሷን ለይታ በራስ ገዝነት የምትተዳደረዋ ፑንትላንድ “ኢትዮጵያ የባህር ዳርቻዎቼን አልምታ መጠቀም ትችላለች፤ እኛ በየትኛውም ኢትዮጵያ ወጪ ገቢ ላይ ምንም ዓይነት ቀረጥ አንጥልም” ስትል በባለስልጣኗ አማካይነት መናገሯ ጫጫታ አስነሳ። የሶማሊላንድ መሪ ወደ አረብ ኢምሬትስና አሜሪካ አቅንተው ከፍተኛ የተባለ የጦር ሰፈር ግንባታ ውል እንደሚፈራረሙ ታውቋል። ፑንትላንድ በምታሳያቸው እንቅስቃሴ ክፉኛ ያናደዳቸው የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ለፑንትላንድ መንግሥት የማስጠንቀቂያ መልዕክት ልከዋል። የሶማሌላንድንና የፑንትላንድን አካቶ ይቅርና መቀመጫቸውን ያለ ድጋፍ ማስተዳደር ያልቻሉት ሀሰን ሼክ ኢትዮጵያን ጨምሮ ዛቻ ሲያሰሙ በርካቶችን እያስገረመ ነው። የፑንትላንድ ፕሬዚዳንት ቀጣይ ሳምንት በሚያከብሩት በዓለ … [Read more...] about ፑንትላንድ ለኢትዮጵያ ወደብ በነጻ እሰጣለሁ አለች
የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ
በ116ኛው የሠራዊት ቀን ሲከበር ንግግር ያደረጉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ “ዐጼ ምኒልክ የጦር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ያቋቋሙበትን ቀን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን ኾኖ እንዲከበር ተደርጓል” በማለት ቀኑ ለምን እንደተመረጠ ይፋ አደረጉ። ከዚህ ሌላ ፊልድ ማርሻሉ በንግግራቸው፤ ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ ከጀግኖች የተረከብናትን ኢትዮጵያ እንደተከበረች እና ማንነቷ እንደተጠበቀ ለማስቀጠል ወታደራዊ ዝግጁነታችንን አሳድገንና ቁመናችንን አዘምነን ማንኛውንም ተልዕኮ በላቀ ብቃት ለመፈጸም ሠራዊቱ ዝግጁ መሆኑን አሣውቀዋል። የሠራዊቱ አባላት የተሠጣቸውን ታላቅ አደራ በድል ለመወጣት የመፈጸም ብቃታቸውን በማሣደግ በዓላማ ጽናታቸው እንዲቀጥሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አሳስበዋል፡፡ ሠራዊቱ ሀገሩን እና ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱን … [Read more...] about የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ
መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው
አየር ኃይል የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን አስተማማኝና ዘመናዊ አየር ኃይል የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በተለይም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ አየር ኃይሉ በሁሉም ረገድ በመዘመንና ስኬታማ በመሆን ሀገር የምትኮራበት ታላቅ ተቋም መሆኑንም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አሁን ላይ በውጊያ መሠረተ-ልማት፣ በሰው ኃይል ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራና አጠቃቀም በአጭር ጊዜ ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቡን በተቋሙ የተለያዩ ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስተማማኝ የሀገር መከታ በመሆን ለየትኛውም ግዳጅ አፈጻጸም ብቁና ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ዘመናዊ ተቋም የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በአየር ኃይል … [Read more...] about መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው
“ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለፓርላማ በሰጡት ማብራሪያ፤ የተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ በአግባቡ እንደሚሰራበት አመልክተዋል። "በምንም አይነትና መስፈርት አግባብ የሌለውና አድሎ ላይ የተመሰረተ ምደባ አይኖርም" ሲሉ ተናግረዋል። "እያንዳንዱ ተማሪ በጠየቀው በችሎታው፣ በሚገባው ቦታ እንዲመደብ እናደርጋል" ያሉት ሚኒስትሩ "አንድና ብቸኛው ከዛ የምንወጣበት አስቸኳይ የሆነና ቅርብ የሆነ ክትትል የሚያስፈልጋቸው የህክምና ጉዳይ ሲኖር ነው" ብለዋል። "የህክምና ኬዞችንም ስንመለከት ከዶክተር ወረቀት ማምጣት ብቻ ሳይሆን በቦርድ ደረጃ ተነጋግረውበት ያ የህክምና ጉዳይ ሌላ ቦታ ሄዶ ለመማር የማያስችል ነው፤ ለህይወቱ/ቷ አስቸጋሪ ነገር ያመጣል ከተባለ ብቻና ብቻ ነው" ሲሉ አስገንዝበዋል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፤ "ለአንድ የመንግሥት ባለስልጣን ፣ አንድ የምክር … [Read more...] about “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ