* በ“ጋዜጠኛነት” ስም የሚፈጸመው የሚዲያ ሸፍጥ በትግራይ ክልል "ከ200 በላይ ኢንዱስትሪዎች ሥራ ጀምረዋል" በሚል ፓርላማ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበው ሪፖርት "ከእውነት የራቀ ነው" ሲሉ የከሰሱት የትግራይ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ 212 ኢንዱስትሪዎች ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ሥራ እንዲጀመሩ ክስ ባቀረቡበት ዜና ጎን ለጎን አስታወቁ። ዜናው የክስ ሳይሆን አሃዱና ቲክቫህ በቅብብሎሽ አንዱ ሌላውን ዋቢ አድርገው ባሰራጩት ዜና መግቢያና ርዕስ ቀዳሚ ያደረጉት "ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፓርላማ ያቀረቡት ሪፖርት ከዕውነት የራቀ ነው" በሚል ነው። ዜናው በመሪ ርዕሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የቀረበውን ክስ አላብራራም፣ እርሳቸው ካሉት ጋርም አላነጻጸረም። የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ መሐሪ ገብረሚካኤል "በአሁኑ ወቅት በክልሉ ሥራ የጀመሩት ለትላልቅ … [Read more...] about የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ማረጋገጫ ሰጠ
News
ዜና
የዓድዋ ድል መታሰቢያ ዛሬ ይመረቃል
ኢትዮጵያ ነጻነቷን ጠብቃ እንድትኖር ያደረጓት አባቶቻችንን የሚዘክር የዓድዋ ድል መታሰቢያ በአዲስ አበባ ፒያሳ ተገንብቶ ዛሬ ይመረቃል። መታሰቢያው የተገነባው ጀግኖች ወደ ጦርነቱ ሲተሙ በአንድነት ተሰባስበው ጉዟቸውን የጀመሩበት ቦታ ላይ ነው። የዓድዋ ድል መታሰቢያ ላይ የሚታየው 00 ኪሎ ሜትር መነሻ ቦታ የኮምፓስ ምልክት በአዲስ አበባ እንዲሁም በመላ ኢትዮጵያ ለሚገኙ ቦታዎች የርቀት መለኪያ መነሻ ነው። የዓድዋ ድል መታሰቢያ በ5 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን 5 ወለል እና 8 በሮች አሉት። አጠቃላይ ከታች እስከ ላይ በ5ቱ ወለል ላይ ያለዉ መሬት ስፋት 12 ሄክታር ነው። ሙዚየሙ ከምድር በታች ያለውን ሁለት ደረጃዎችን ጨምሮ 5 ወለሎች አሉት። ከ1 ሺህ በላይ የመኪና ማቆሚያ፣ ሲሲቲቪ ካሜራ፣የራሱ መቆጣጠሪያ ያለው ስማርት ፓርኪን ሥርዓት … [Read more...] about የዓድዋ ድል መታሰቢያ ዛሬ ይመረቃል
37 ቢሊዮን ብር የት ገባ? “ትግራይ ውስጥ አዲስ አጀንዳ ተተከለ”
ትግራይን ማቃናት ያቃተው ካድሬ - አቅቶሃል ተባለ “ሰላሳ ሰባት ሚሊዮን ብር ለትግራይ አስተዳደር መሰጠቱን ስንሰማ ደንገጠናል። ዜናውን የሰሙ ሁሉ ብሩ የት ገባ? የሚል ጉምጉምታ እያሰሙ ነው። አካል ጉዳተኞች ጸጉራቸውን እየነጩ ነው። ጉዳዩን ትግራይ ያሉ ፖለቲከኞችም እየመከሩበት ነው። ሕዝብ ተናድዷል” ስትል ተቀማጭነቷ አዲስ አበባ የሆነ የትግራይ ተወላጅ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ተባባሪ ነግራዋለች። ወጣቷ በጦርነቱ አንድ ወንድሟን አጥታለች። ኮምቦልቻ እስከሚደርስ በሕይወት ስለመኖሩ መረጃ እንደነበራት፣ ከዚያ በኋላ ደብዛው ጠፍቶባት መጨረሻ ላይ እናቷ መርዶ እንደተነገራቸው የምትናገረዋ ወጣት፣ ስለ ትሕነግ (የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር) ስትናገር ያንዘዘርታል። ኃላፊዎቹን ስታያቸው ያማታል። ኃፍረትና ጸጸት የሚባል ነገር ያልፈጠረባቸው መሆናቸውን ስታስብ... “ትግራይን … [Read more...] about 37 ቢሊዮን ብር የት ገባ? “ትግራይ ውስጥ አዲስ አጀንዳ ተተከለ”
አወዛጋቢው የአቡነ ጴጥሮስ የጉዞ ሰነድ
የአሜሪካንን ዜግነት ለመውሰድ ቀኝ እጅን ወደ ላይ ቀስሮ መማል ግድ ነው። እከሌ ከገሌ ሳይባል “ቀደም ሲል የነበረኝን ዜግነት እክዳለሁ” በማለት የሚከናወነው ምህላ “እግዚአብሔር ይርዳኝ” በሚል ማሳረጊያ ይቋጫል። “ቀደም ሲል የነበረኝን ዜግነቴን፣ የማንኛውንም የልዑል፣ የግዛት፣ የአገር፣ ወይም የሉዓላዊ መንግሥት ተገዢነቴን በሙሉና በፍጹም መካዴን በምሕላ አውጃለሁ" በሚል የሚከናወነው የመሐላ አሰጣጥ፣ ምሕላውን በፍጹምና ያለምንም ማወላዳት መቅበልን የሚጠይቅ ሲሆን ይህንንም ቀኝ እጅ በማውጣት የሚከናወን ሥርዓት ነው። Oath"I hereby declare, on oath, that I absolutely and entirely renounce and abjure all allegiance and fidelity to any foreign prince, potentate, state, or … [Read more...] about አወዛጋቢው የአቡነ ጴጥሮስ የጉዞ ሰነድ
ትህነግ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያካሂደውን ሽብር እንደሚቀጥል አስታወቀ
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትሕነግ) በማለት ራሱን የሚጠራው ቡድን በዓለምአቀፉ የአሸባሪ ቋት ተመዝግቦ የሚገኘው የወንበዴዎች ስብስብ ነው። ከስድሳ ቀናት በላይ ስብሰባ ተቀምጦ የነበረው ትህነግ የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደሚገባው አልተተገበረም በሚል በመንግሥት ላይ የተቃውሞ መግለጫ አውጥቶ ነበር። በቀጣይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በጥር 23 ቀን 2016 ዓም ለትሕነግ መግለጫ አጸፋ ምላሽ የሰጠ ሲሆን በዋነኝነት ስምምነቱን ለመተግበር መንግሥት እንዴት ከሚገባው በላይ ርቀት እንደሄደ የጠቆመ ነበር። እንደ ማሳያም ከስምምነቱ ወዲህ መንግሥት ለትግራይ ክልል ከ37 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን ገልጾዋል። ለዚህ የመንግሥት ምላሽ ትሕነግ የአጸፋ ምላሽ ሰኞ የሰጠ ሲሆን ለክልሉ የተደረገውን 37 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ምንም ዓይነት ዕውቅና ሳይሰጥ የፕሪቶሪያው … [Read more...] about ትህነግ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያካሂደውን ሽብር እንደሚቀጥል አስታወቀ
ከትሕነግ ጋር ለማበር ወልቃይትን መስዋዕት የሚያደርጉ የ”አማራ ነጻ አውጪዎች”
ከትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትሕነግ) ጋር አብሮ "የጠብ መንጃ ትግሉን ማጧጧፍ" በሚል ከውሳኔ የደረሱ ክፋይ የ"አማራ ነጻ አውጪ" ኃይሎች መኖራቸው ተሰማ። ለስምምነቱ ትሕነግ ምዕራብ ትግራይ የሚለውንና አሁን "ነጻ ወጥቷል" የሚባለውን ወልቃይት ተላልፎ እንዲሰጥ ፈቃደኝነት ያለበት እንደሆነ ተመልክቷል። ራሳቸውን በተለያዩ አካባቢያዊና አደረጃጀት ከሰየሙት መካከል አሁን አንድ ለመሆን እየሠሩ እንደሆነ የሚነገርላቸው በዝናቡ የሚመራው የጎጃም ዕዝና የዘመነ ካሴ ኃይል ነው ይህን ስምምነት ለማድረግ እየሠራ እንደሆነ የተሰማው። “ጊዜው አሁን ነው፤ ይህንን ጊዜ ልንጠቀምበት ይገባል” በሚል በገሃድ ወልቃይትን ዳግም በኃይል ለመያዝ ደብረጽዮን በቅርቡ መናገሩ ይታወሳል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ከሕዝብ ጋር በተለያዩ ከተሞች ውይይት ያደረገው ጌታቸው ረዳም “እኛ ሥራችንን መሥራት … [Read more...] about ከትሕነግ ጋር ለማበር ወልቃይትን መስዋዕት የሚያደርጉ የ”አማራ ነጻ አውጪዎች”
ፋኖና ኦነግ ሸኔ “ነውጠኛ ቡድኖች” በመባላቸው ለጥገኝነት ማመልከቻ ተቀባይ እንደማይሆኑ ተሰማ
ፋኖና ኦነግ ሸኔ በማጣቀስ በውጭ አገራት የሚቀርቡ የጥገኝነት መጠየቂያ ማመልከቻዎች ተቀባይነት እንደማያገኙ ይህንኑ ጉዳይ በማስፈጸም የሚሠሩ አንድ ባለሙያ ለጎልጉል ጥቆማ ሰጡ። ድርጅቶቹ “ነውጥ ቡድኖች" ወይም “violent group s” በሚል የተፈረጁበት አግባብ መኖሩንም አክለው ገልጸዋል። ከአገራቸው በተለያዩ ምክንያቶች ተሰድደው ጥገኝነት የሚጠይቁ ወገኖች ከለላ ለማግኘት በሚያስገቡት የስደተኝነት ማመልከቻ በአሁኑ ሰዓት እንደየብሔራቸው ወይም ብሔራቸውን በመቀየር በብዛት በማስረጃነት የሚጠቀሙት የፋኖና የኦነግ ሸኔን ትግል እንደሆነ ይታወቃል። “ለምሳሌ በካናዳ ድርጅቶቹ “violent groups” ተብለዋል" የሚሉት የሕግ ባለሙያ ይህን የተረዱት በሥራቸው አማካይነት የደንበኞቻቸውን ጉዳይ ሲከታተሉ ነው። ባለሙያው ከተሞቹን ለይተው በስም ባይጠሩም መረጃውን የሰሙት … [Read more...] about ፋኖና ኦነግ ሸኔ “ነውጠኛ ቡድኖች” በመባላቸው ለጥገኝነት ማመልከቻ ተቀባይ እንደማይሆኑ ተሰማ
“ዐቢይን ግንባሩን ብለህ ዳዊት ሁን” ያሉት አቡነ ሉቃስ ክስ ተመሰረተባቸው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን እንደ ጎልያድ በማስመሰል በአንድ ምሳሌያዊ ዳዊት እንዲግደሉ የሃይማኖታዊ ግድያ ጥሪ ያስተላለፉት አቡን ሉቃስ የወንጀል ክስ ተመሠረተባቸው። አቡነ ሉቃስ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 247 እና 251 ድንጋጌ ተላልፈዋል በሚል ክስ ተመሰረተባቸው፡፡ ክሱ የቀረበባቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ሕገመንግስታዊና በሕገመንግስት ስርዓት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮች ችሎት ነው። በአቡነ ሉቃስ ላይ ሁለት ክሶችን ያቀረበው የፍትሕ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ ነው፡፡ ይህም ተከሳሽ አቡነ ሉቃስ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 247 (ሐ) እና አንቀጽ 258(ሀ) ስር የተደነገገውን ድንጋጌ እንዲሁም የወንጀል ህግ አንቀጽ 251 (ሐ) እና አንቀጽ 258 ስር … [Read more...] about “ዐቢይን ግንባሩን ብለህ ዳዊት ሁን” ያሉት አቡነ ሉቃስ ክስ ተመሰረተባቸው
አል ሸባብ ሦስት የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ካምፖችን ተቆጣጠረ
አልሸባብ ጋልሙዱግ በሚባል ክልል ከሶማሌ ጦር ጋር ባደረገው ውጊያ ሶስት የሶማሊያ ጦር ካምፖችን በቁጥጥሩ ስር አድርጓል። አል ሸባብ ከሶማሊያ ጦር ጋር አምስት ሰዓታት ያህል የቆየ ከባድ ጦርነት ካካሄደ በኋላ ከጥቃቱ የተረፉ የሶማሌ ብሄራዊ ጦር የ"ጎርጎር ኮማንዶ" መኮንኖችና ወታደሮች እንደተናገሩት በውጊያው ከ230 በላይ የሶማሊያ ወታደሮች መሞታቸውን እንዳረጋገጡና ስፍር ቁጥር የሌላቸው መቁሰላቸውን ገልፀዋል። የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር በቦታው ያሰፈራቸው ወታደሮቹ 4 ሻለቃ የ"ጎርጎር ኮማንዶዎችን" ሲሆን 15 የአል ሸባብ አሸባሪዎች ጋር ባደረገው ውጊያ ከፍተኛ ሞትና የአካል ጉዳት አስተናግዷል።የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር በአል ሸባብ ከበባ ውስጥ ሆኖ ምንም ዓይነት የሽፋን ኃይል ማሰማራት አልተቻለውም ተብሏል።ፕሬዝደንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በአል ሸባብ የሽብር ቡድን ላይ … [Read more...] about አል ሸባብ ሦስት የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ካምፖችን ተቆጣጠረ
ፑንትላንድ ለኢትዮጵያ ወደብ በነጻ እሰጣለሁ አለች
የሶማሊላንድና አሜሪካ የጦር ሰፈር ስምምነት ያደርጋሉ ከሶማሊያ ራሷን ለይታ በራስ ገዝነት የምትተዳደረዋ ፑንትላንድ “ኢትዮጵያ የባህር ዳርቻዎቼን አልምታ መጠቀም ትችላለች፤ እኛ በየትኛውም ኢትዮጵያ ወጪ ገቢ ላይ ምንም ዓይነት ቀረጥ አንጥልም” ስትል በባለስልጣኗ አማካይነት መናገሯ ጫጫታ አስነሳ። የሶማሊላንድ መሪ ወደ አረብ ኢምሬትስና አሜሪካ አቅንተው ከፍተኛ የተባለ የጦር ሰፈር ግንባታ ውል እንደሚፈራረሙ ታውቋል። ፑንትላንድ በምታሳያቸው እንቅስቃሴ ክፉኛ ያናደዳቸው የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ለፑንትላንድ መንግሥት የማስጠንቀቂያ መልዕክት ልከዋል። የሶማሌላንድንና የፑንትላንድን አካቶ ይቅርና መቀመጫቸውን ያለ ድጋፍ ማስተዳደር ያልቻሉት ሀሰን ሼክ ኢትዮጵያን ጨምሮ ዛቻ ሲያሰሙ በርካቶችን እያስገረመ ነው። የፑንትላንድ ፕሬዚዳንት ቀጣይ ሳምንት በሚያከብሩት በዓለ … [Read more...] about ፑንትላንድ ለኢትዮጵያ ወደብ በነጻ እሰጣለሁ አለች