• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

News
ዜና

ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ 

August 8, 2023 05:47 pm by Editor 1 Comment

ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ 

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) ወይም ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ተብሎ በሚጠራው የወንበዴ ቡድን ስም አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ለመመስረት የቀረበውን ውሳኔ ፍርድ ቤት ውድቅ አደረገ። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የምርጫ ጉዳይ ክርክር ችሎት በምርጫ ቦርድና እነ’ገ/ሚካኤል ተስፋዬ መካከል የተደረገው ክርክር ውሣኔ አግኝቷል። በህወሓት ስም የሚጠራ ለረጅም ዓመታት የሚታወቅ ፓርቲ የነበረ በመሆኑ በዚሁ ስም አዲስ ፓርቲ ማቋቋም መራጩን ያደናግራል ተብሏል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ስም ክልላዊ ፓርቲ ለመመሥረት የቀረበለትን የቅድመ ዕውቅና ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል። ይህንን ተከትሎ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ያቀና ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና በእነ’ገ/ሚካኤል ተስፋዬ መካከል … [Read more...] about ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ 

Filed Under: Middle Column, News, Uncategorized Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

“ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት

August 1, 2023 09:25 am by Editor 1 Comment

“ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት

አሁናዊ የመከላከያ ሠራዊቱን ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ የኢፌዴሪ የመከላከያ ሠራዊት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የሠራዊቱ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ፣ መግለጫው በተለያዩ አካላት በሠራዊቱ ላይ እየተናፈሱ ያሉ ብዥታዎችን ለማጥራት የተሰጠ ነው ብለዋል። ሠራዊቱ ካለፉት ዓመታት በነበረበት ቁመና ላይ እንዳለ የሚያስቡ አካላት ካሉ የቆሙት እነርሱ እንጂ ሠራዊቱ ተራማጅ ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት፣ ሠራዊቱ ዘርፈ ብዙ ግዳጁን እየተወጣ ነው ብለዋል። "ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ" የሚል አካል ላይ ሠራዊቱ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል። ሠራዊቱን መቋቋም ያልቻሉ አካላት በሠራዊቱ ላይ ሰፊ የስም ማጥፋት ዘመቻ ላይ ይገኛሉም ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት። በተለይ አሁን ላይ … [Read more...] about “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው

July 31, 2023 09:27 am by Editor Leave a Comment

ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው

ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን አሳልፎ ለመስጠት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። አራተኛው የኢትዮ-ደቡብ አፍሪካ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በስብሰባው ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነቶችና ትብብር ሚኒስትር ዶክተር ናሌዲ ፓንዶር እንዲሁም የሁለቱ አገራት ባለስልጣናት ተሳታፊ ሆነዋል። በዚህ ወቅት ሁለቱ አገራት በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን አሳልፎ ለመስጠት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የፍትሕ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ እና የደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነቶችና ትብብር ሚኒስትር ዶክተር ናሌዲ ፓንዶር ተፈራርመዋል። ሁለቱ አገራት በስብሰባው ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ሳይንስ፣ ኢኖቬሽን፣ ትምህርት፣ … [Read more...] about ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

“ከማንም ጋር ግጭት አንፈልግም በማንነታችን ላይ ግን ዳግም ለአፍታ እንኳን ተዘናግተን የተራዘመ መከራ እና ባርነት ለመቀበል ፍጹም” አንፈቅድም ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ

July 27, 2023 04:19 pm by Editor 2 Comments

“ከማንም ጋር ግጭት አንፈልግም በማንነታችን ላይ ግን ዳግም ለአፍታ እንኳን ተዘናግተን የተራዘመ መከራ እና ባርነት ለመቀበል ፍጹም” አንፈቅድም ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ

የግማሽ ምዕተ ዓመት ገደማ ሴራ እና ተንኮል መጋለጫ፣ የሩብ ምዕተ ዓመት አምባገነናዊ አገዛዝ መሸኛ፣ የሦስት አስርት ዓመታት የጨለማ ጉዞ ምዕራፍ መቋጫ እና የአዲሱ ትውልድ የነጻነት አደራ ርክክብ ትናንት በቅርቡ የተስተዋለ ክስተት ነበር፡፡ እልፎች ማንነታችን ይከበር ብለው አደባባይ ድረስ ዘልቀው በመውጣት የከበረ መስዋዕትነት ሲከፍሉ ከተፈጥሯዊ ነጻነት ባሻገር የጠየቋቸው እና ለትግል የሚያበቁ አያሌ ምክንያቶች ነበሯቸው፡፡ ማኀበረሰባዊ ማንነትን የሚያስቀጥል ትግል ደግሞ በትውልድ ቅብብሎሽ መካከል የሚጸና የነጻነት መርከብ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ለማንነት መከበር በሚደረግ ትግል ውስጥ ውስኖች እንደ አብሪ ኮከብ ጎልተው ቢታዩም የትግሉ ባለቤት እና ሞተር ግን ሕዝብ መኾኑ አይካድም፡፡ የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት እና ራያ ሕዝብ የዘመናት የነጻነት ትግል መልህቅ በታሪክ አጋጣሚ በአዲሱ … [Read more...] about “ከማንም ጋር ግጭት አንፈልግም በማንነታችን ላይ ግን ዳግም ለአፍታ እንኳን ተዘናግተን የተራዘመ መከራ እና ባርነት ለመቀበል ፍጹም” አንፈቅድም ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: demeke zewdu, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist, wolkayit

የተሰረቁ የሞባይል ስልኮች (215) በህጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋሉ

July 27, 2023 03:56 pm by Editor Leave a Comment

የተሰረቁ የሞባይል ስልኮች (215) በህጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋሉ

በተለያዩ አካባቢዎች የተሰረቁ ከሁለት መቶ በላይ የሞባይል ስልኮችን በህጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖለስ አስታውቋል፡፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ በህጋዊ የሞባይል ስልክ እና የቴሌቪዥን ጥገና ሱቅ ሽፋን ከግለሰቦች የተሰረቁ ስልኮችን እየገዙ ሲሸጡ ከነበሩ ግለሰቦች ሱቅ ውስጥ 215 ሞባይል ስልኮች መያዛቸው ታውቋል፡፡ የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ እና ባደረገው ክትትል በወረዳ 3 ኤድናሞል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሞባይል ጥገና ስራ በሚሰሩ አራት የንግድ ሱቆች ላይ ትናንት ሃምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም በህግ አግባብ በተከናወነ ብርበራ ነው ከተለያዩ ቦታዎች ተሰርቀው የተከማቹ ሞባይል ስልኮች ሊያዙ የቻሉት፡፡ ከሞባይል ስልኮቹ በተጨማሪ የወንጀል ፍሬ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ እና በጥገና ቤቶቹ ውስጥ የተገኙ የተለያየ … [Read more...] about የተሰረቁ የሞባይል ስልኮች (215) በህጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋሉ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: Edna Mall, stolen cell phones

የዓለም ባንክ የ400 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ሰጠ

July 27, 2023 10:06 am by Editor Leave a Comment

የዓለም ባንክ የ400 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ሰጠ

ኢትዮጵያ ከዓለምአቀፍ ተቋማት ምንም ዓይነት ብርድም ሆን ድጋፍ እንዳታገኝ ከአገር ውስጥ የራሷ ልጆችና ከውጭ ውድቀቷን የሚመኙ አገራት የተለያየ ተጽዕኖ ሲያደርሱባት ቆይተዋል። የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) ኢትዮጵያን የአንድ ቤተሰብ ጥቅም ማስጠበቂያ አድርጓት በነበረበት ጊዜ ከበጀት ድጎማ ጀምሮ ማንኛውንም ዓይነት ብድር፣ ዕርዳታ፣ ድጋፍ ወዘተ ለአጋዚ ጦር ደመወዝ የሚከፍለው ጭምር ዓለምአቀፋዊ የገንዘብ ተቋማት ድጎማ ሲደርግለት መቆየቱ የሚታወስ ነው። ትህነግ ከአራት ኪሎ ከለቀቀ ወዲህ ግን እሹሩሩ ሲሉት የነበሩት ዓለምአቀፋዊ የገንዘብ ተቋማት የተለያየ ምክንያት በመሰጠት ተገቢው ድጋፍ አቁመዋል፤ ብድር ለማግኘት እንኳን ትህነግ ሲዘርፍ የኖረውን ብድር እንደ ምክንያት በመጥቀስ ለዓቅመ ብድር አልደረሳችሁም እያሉ ኢትዮጵያን ለማዳከም ብዙ ጥረዋል። በውጪ ያሉት … [Read more...] about የዓለም ባንክ የ400 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ሰጠ

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist, world bank

የማዳበሪያ ዕጥረት አለ በሚባልበት የአማራ ክልል 400 ኩንታል ማዳበሪያ ተያዘ

July 24, 2023 09:55 am by Editor Leave a Comment

የማዳበሪያ ዕጥረት አለ በሚባልበት የአማራ ክልል 400 ኩንታል ማዳበሪያ ተያዘ

አቶ ዮሐንስ ቧያለው በክልላቸው ምክር ቤት ፊት ስለ ማዳበሪያ አቅርቦት ዕጥረት አምርረው በተናገሩና የክልሉ ገብርና ቢሮ ሥራ መሥራት ያልቻለ ደመወዝ በነጻ የሚበላ ነው ብለው ባፌዙበት ማግስት በአማራ ክልል 400 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ በሕገወጥ መልኩ ሲሰራጭ መያዙን ኢቢሲ ዘግቧል። በአማራ ክልል ማዳበሪያን የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ ሲወራ የሰነበተው ሤራ ምን እንደሆነ ማሳያ ነው። የዜናው ሙሉ መረጃ ከዚህ በታች ቀርቧል። 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ሥር ዋለ መነሻውን ከጅቡቲ ወደብ አድርጎ መዳረሻውን ወረታ ከተማ ለማድረግ የተንቀሳቀሰው 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ የጫነ ተሳቢ ተሽከርካሪ፤ ከታሰበው ቦታ ሳይደርስ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ ሕገ ወጥ ድርጊቱ የተፈጸመው በባህርዳር ከተማ … [Read more...] about የማዳበሪያ ዕጥረት አለ በሚባልበት የአማራ ክልል 400 ኩንታል ማዳበሪያ ተያዘ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: amhara region, operation dismantle tplf, push and pull conspiracy, yohannes buwayalew

33.5 ሚሊዮን ሕዝብ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥሪ መቀበሉ ታወቀ

July 17, 2023 04:10 pm by Editor 2 Comments

33.5 ሚሊዮን ሕዝብ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥሪ መቀበሉ ታወቀ

በሕዝቡ ተሳትፎ እጅግ ከፍተኛ ኩራት ተሰምቶኛል ሞራልም ሰጥቶኛል በማለት አድንቀዋል ሲነጋ … በመላ ሀገሪቱ በአንድ ቀን ውስጥ 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ዘመቻ ከጥዋት አንስቶ እየተካሄደ ይገኛል። ዘመቻው እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ እንደሚቆይ ነው የተነገረው። በችግኝ ተከላ ዘመቻው ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ እናቶች ፣ ህፃናት፣ ታዳጊዎች፣ ወጣቶች፣ የተለያዩ ተቋማት ሰራተኞች፣ የውጭ ሀገር ዲፕሎማቶች እና ሌሎችም እየተሳተፉበት ይገኛሉ። የኢፌዲሪ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ስራ የፖለቲካ ጉዳይ ፣ የፓርቲያቸው ፕሮግራም እንዲሁም የመንግሥት ጉዳይ እንዳልሆነ ከዚህ ቀደም ገልጸዋል። ይህ ጉዳይ " የኢትዮጵያ ጉዳይ " እንደሆነና በዚህ የችግኝ ተከላ ዘመቻ አረንጓዴ የምትለብሰው ኢትዮጵያ … [Read more...] about 33.5 ሚሊዮን ሕዝብ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥሪ መቀበሉ ታወቀ

Filed Under: Left Column, News Tagged With: Carbon, Ethiopia, Green Legacy, Planting Trees

“ዛሬ መጻሕፍት የሚያነቡ ህፃናት ነገ አይሰርቁም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

July 16, 2023 12:24 pm by Editor 2 Comments

“ዛሬ መጻሕፍት የሚያነቡ ህፃናት ነገ አይሰርቁም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

“ዛሬ መጻሕፍት የሚያነቡ ህፃናት ነገ አይሰርቁም፤ በሙስና እና በሌብነት ቀንበር ስር አይወድቁም” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ። "መጻሕፍት የህይወት ዘመን ጓደኛ ናቸው" እንዳሉት ከተሽከርካሪ ነፃ (car free) መንገድ ያስፈልጋል፤ ከሀሳብ እና ከመጻሕፍት ነፃ የሆነ ጎዳና ግን ሊኖር አይገባም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት አብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ከመደበኛ ስፍራው ባለፈ በአዲስ አበባ የተለያዩ ጎዳናዎች ላይ ለታዳጊ ህፃናት መጻሕፍት ያቀርባል ደግሞም ያነባል፤ ያስነብባልም። ዛሬ መጻሕፍት የሚያነቡ ህፃናት ነገ አይሰርቁም፤ በሙስና እና በሌብነት ቀንበር ስር አይወድቁም ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ታነባለች ጎዳናዋም በመጻሕፍት ተሞልቶ ይትረፈረፋል። “እኛ ኢትዮጵያውያን ካለብን ችግር የምንወጣው … [Read more...] about “ዛሬ መጻሕፍት የሚያነቡ ህፃናት ነገ አይሰርቁም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: Abrhot Library, Ethiopia Reads, operation dismantle tplf, Reading

ታከለ ኡማ የዳያስፖራ አኩራፊዎችን ሰብስበው ድርጅት እየመሠረቱ ነው፣ ሚዲያም አቋቁመዋል 

July 11, 2023 01:00 am by Editor 1 Comment

ታከለ ኡማ የዳያስፖራ አኩራፊዎችን ሰብስበው ድርጅት እየመሠረቱ ነው፣ ሚዲያም አቋቁመዋል 

ከኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ወደ ኦህዴድ ከለወጡት የዶክተር መረራ ወጣቶች ክንፍ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ታከለ ኡማ አዲስ የትግል ኅብረት በመፍጠር ላይ መሆናቸው ተሰማ። ለዚህ እንቅስቃሴ የሚሆናቸው የመደበኛ ሚዲያና የማኅበራዊ ሚዲያ ትሥሥር ገጽ ሠራዊት እንዳመቻቹም ታውቋል። መነሻቸው ፖለቲካዊ ኩርፊያ ነው ተብሏል። ጎልጉልን ያነጋገሩ የመረጃው ባለቤቶች እንዳሉት የቀድሞው የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የማዕድን ሚኒስትር መንግሥት ላይ አቂመዋል። የለውጡ የምሥጢር ታጋይ እንደነበሩ የሚናገሩት ታከለ አሜሪካ ከተሻገሩ በኋላ በዳያስፖራ ከሚገኙ ዋነኛ አኩራፊዎች ጋር በማበር ጠበቅ ባለ እንቅስቃሴ ተጠምደዋል።     ጥያቄው ከቀረበላቸው መካከል አንዱ የሆኑት የኦህዴድ የቀድሞ አመራር እንዳሉት ታከለ ኡማ ከአማራ፣ ከኦሮሞና የሰላም ስምምነቱን … [Read more...] about ታከለ ኡማ የዳያስፖራ አኩራፊዎችን ሰብስበው ድርጅት እየመሠረቱ ነው፣ ሚዲያም አቋቁመዋል 

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, takele uma, takele umma, tplf terrorist

  • « Previous Page
  • Page 1
  • Page 2
  • Page 3
  • Page 4
  • …
  • Page 130
  • Next Page »

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule