• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ

April 16, 2025 11:44 pm by Editor Leave a Comment

በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ወታደራዊ ሥልጠና የወሰዱ መሪዎች ሥልጠናቸውን አጠናቅቀው ተመርቀዋል።

በሥልጠናው የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አሥተዳዳሪ አሸተ ደምለው፣ የዞኑ ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን ጨምሮ የዞኑ መካከለኛና ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ወታደራዊ ሥልጠና ወስደዋል።

ሥልጠናው በዕውቀት ላይ ተመሥርቶ ሕዝቡን ለማገልገል እና የጸጥታ መዋቅሩን አደራጅቶ ለመደገፍ እና ለመምራት ዓላማ አድርጎ መሰጠቱ ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የተደራጀና የተቀናጀ ሕዝብ ችግሮችን መቋቋምና ፈተናዎችን ማለፍ ይችላል ብለዋል። ለዚህም ከላይ እስከ ታች ያለውን መሪ ወታደራዊ ሳይንስ አሠልጠኖ ማደራጀት አስፈላጊ ኾኖ መገኘቱን ተናግረዋል።

ለማንነታችን እና ለወሰናችን ዘብ የምንኾነው ሕዝቡ እና መሪው በወታደራዊ እና ስነ ልቦናዊ ቁመና የተሻለ ሲኾን ነው ብለዋል። ሁሉም ራሱን ለማብቃት በቁርጠኝነት ሥልጠናውን መውሰዱ የሚደነቅ መኾኑንም ተናግረዋል።

ሥልጠናው መሪዎች ሁለገብ እንዲኾኑ ያስቻለ መኾኑን የጠቁሙት ኮሎኔሉ ማንነታችንን ለማጽናት መደራጀት እና መሠልጠን የዘወትር ተግባራችን ነው ብለዋል።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አሸተ ደምለው ከአባቶቻችን በወረስነው አርበኝነት መሠረት በሀሳብ እና በብረት ትጥቅ መጠናከር የተከዜን አዳኝ ትውልድ ግብ ማሳካት ነው ብለዋል።

የዚህ ትውልድ ተልዕኮ ለመጭው ትውልድ ነጻነትን እንጂ ተሻጋሪ እዳ አለማውረስ መኾኑን ያስረዱት አሥተዳዳሪው እውነታችንን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚረዳው ቢኾንም ማንነታችንን በኀይል ለመንጠቅ ለሚሞክር ኀይል ራሳችንን የመከላከል መብታችንን ለመጠቀም እንገደዳለን ነው ያሉት።

ትግላችን ራስን የመኾን፤ የራስን እድል በራስ የመወሰን እና አማራነትን የማስከበር ትግል ነው ብለዋል። ለዘላቂ የሕግ አሸናፊነት የሚያበቃን ሰላማዊ የትግል መንገድን መከተል መኾኑንም አመላክተዋል።

ከዚህ ውጭ በኀይል ተከዜን መሻገር የሚሞክር ኀይል ካለ ይህ የተከዜ ትውልድ የተከዜ ዘብነቱን በተግባር ማሳየት ይጠበቅበታል ብለዋል።

ተመራቂ መሪዎችም ከዚህ በፊት መሪ ኾነን መሳሪያ ብንታጠቅም የወታደራዊ ሳይንስ ልምድ አልነበረንም ነው ያሉት።

ከሥልጠናው ሰፊ ልምድ እና ዕውቀት ማግኘታቸውንም ተናግረዋል። ከውስጥ እና ከውጭ ለሚገጥም ፈተና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ያስችለናል ነው ያሉት።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሰላም አስከባሪ አስተባባሪ እና አሠልጣኝ ኮማንደር ድንቁ ቢረሳው መሪዎች እንደ ማንኛውም ሠልጣኝ ዝቅ ብሎ ምሽግ ውስጥ በማደር ሥልጠናውን ማጠናቀቅ መቻላቸው የሚደነቅ መኾኑን ገልጸዋል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: operation dismantle tplf, Tekeze Guard, wolkayit

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule