• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ

April 16, 2025 11:44 pm by Editor Leave a Comment

በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ወታደራዊ ሥልጠና የወሰዱ መሪዎች ሥልጠናቸውን አጠናቅቀው ተመርቀዋል።

በሥልጠናው የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አሥተዳዳሪ አሸተ ደምለው፣ የዞኑ ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን ጨምሮ የዞኑ መካከለኛና ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ወታደራዊ ሥልጠና ወስደዋል።

ሥልጠናው በዕውቀት ላይ ተመሥርቶ ሕዝቡን ለማገልገል እና የጸጥታ መዋቅሩን አደራጅቶ ለመደገፍ እና ለመምራት ዓላማ አድርጎ መሰጠቱ ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የተደራጀና የተቀናጀ ሕዝብ ችግሮችን መቋቋምና ፈተናዎችን ማለፍ ይችላል ብለዋል። ለዚህም ከላይ እስከ ታች ያለውን መሪ ወታደራዊ ሳይንስ አሠልጠኖ ማደራጀት አስፈላጊ ኾኖ መገኘቱን ተናግረዋል።

ለማንነታችን እና ለወሰናችን ዘብ የምንኾነው ሕዝቡ እና መሪው በወታደራዊ እና ስነ ልቦናዊ ቁመና የተሻለ ሲኾን ነው ብለዋል። ሁሉም ራሱን ለማብቃት በቁርጠኝነት ሥልጠናውን መውሰዱ የሚደነቅ መኾኑንም ተናግረዋል።

ሥልጠናው መሪዎች ሁለገብ እንዲኾኑ ያስቻለ መኾኑን የጠቁሙት ኮሎኔሉ ማንነታችንን ለማጽናት መደራጀት እና መሠልጠን የዘወትር ተግባራችን ነው ብለዋል።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አሸተ ደምለው ከአባቶቻችን በወረስነው አርበኝነት መሠረት በሀሳብ እና በብረት ትጥቅ መጠናከር የተከዜን አዳኝ ትውልድ ግብ ማሳካት ነው ብለዋል።

የዚህ ትውልድ ተልዕኮ ለመጭው ትውልድ ነጻነትን እንጂ ተሻጋሪ እዳ አለማውረስ መኾኑን ያስረዱት አሥተዳዳሪው እውነታችንን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚረዳው ቢኾንም ማንነታችንን በኀይል ለመንጠቅ ለሚሞክር ኀይል ራሳችንን የመከላከል መብታችንን ለመጠቀም እንገደዳለን ነው ያሉት።

ትግላችን ራስን የመኾን፤ የራስን እድል በራስ የመወሰን እና አማራነትን የማስከበር ትግል ነው ብለዋል። ለዘላቂ የሕግ አሸናፊነት የሚያበቃን ሰላማዊ የትግል መንገድን መከተል መኾኑንም አመላክተዋል።

ከዚህ ውጭ በኀይል ተከዜን መሻገር የሚሞክር ኀይል ካለ ይህ የተከዜ ትውልድ የተከዜ ዘብነቱን በተግባር ማሳየት ይጠበቅበታል ብለዋል።

ተመራቂ መሪዎችም ከዚህ በፊት መሪ ኾነን መሳሪያ ብንታጠቅም የወታደራዊ ሳይንስ ልምድ አልነበረንም ነው ያሉት።

ከሥልጠናው ሰፊ ልምድ እና ዕውቀት ማግኘታቸውንም ተናግረዋል። ከውስጥ እና ከውጭ ለሚገጥም ፈተና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ያስችለናል ነው ያሉት።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሰላም አስከባሪ አስተባባሪ እና አሠልጣኝ ኮማንደር ድንቁ ቢረሳው መሪዎች እንደ ማንኛውም ሠልጣኝ ዝቅ ብሎ ምሽግ ውስጥ በማደር ሥልጠናውን ማጠናቀቅ መቻላቸው የሚደነቅ መኾኑን ገልጸዋል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News Tagged With: operation dismantle tplf, Tekeze Guard, wolkayit

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule