• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ

April 16, 2025 11:44 pm by Editor Leave a Comment

በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ወታደራዊ ሥልጠና የወሰዱ መሪዎች ሥልጠናቸውን አጠናቅቀው ተመርቀዋል።

በሥልጠናው የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አሥተዳዳሪ አሸተ ደምለው፣ የዞኑ ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን ጨምሮ የዞኑ መካከለኛና ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ወታደራዊ ሥልጠና ወስደዋል።

ሥልጠናው በዕውቀት ላይ ተመሥርቶ ሕዝቡን ለማገልገል እና የጸጥታ መዋቅሩን አደራጅቶ ለመደገፍ እና ለመምራት ዓላማ አድርጎ መሰጠቱ ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የተደራጀና የተቀናጀ ሕዝብ ችግሮችን መቋቋምና ፈተናዎችን ማለፍ ይችላል ብለዋል። ለዚህም ከላይ እስከ ታች ያለውን መሪ ወታደራዊ ሳይንስ አሠልጠኖ ማደራጀት አስፈላጊ ኾኖ መገኘቱን ተናግረዋል።

ለማንነታችን እና ለወሰናችን ዘብ የምንኾነው ሕዝቡ እና መሪው በወታደራዊ እና ስነ ልቦናዊ ቁመና የተሻለ ሲኾን ነው ብለዋል። ሁሉም ራሱን ለማብቃት በቁርጠኝነት ሥልጠናውን መውሰዱ የሚደነቅ መኾኑንም ተናግረዋል።

ሥልጠናው መሪዎች ሁለገብ እንዲኾኑ ያስቻለ መኾኑን የጠቁሙት ኮሎኔሉ ማንነታችንን ለማጽናት መደራጀት እና መሠልጠን የዘወትር ተግባራችን ነው ብለዋል።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አሸተ ደምለው ከአባቶቻችን በወረስነው አርበኝነት መሠረት በሀሳብ እና በብረት ትጥቅ መጠናከር የተከዜን አዳኝ ትውልድ ግብ ማሳካት ነው ብለዋል።

የዚህ ትውልድ ተልዕኮ ለመጭው ትውልድ ነጻነትን እንጂ ተሻጋሪ እዳ አለማውረስ መኾኑን ያስረዱት አሥተዳዳሪው እውነታችንን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚረዳው ቢኾንም ማንነታችንን በኀይል ለመንጠቅ ለሚሞክር ኀይል ራሳችንን የመከላከል መብታችንን ለመጠቀም እንገደዳለን ነው ያሉት።

ትግላችን ራስን የመኾን፤ የራስን እድል በራስ የመወሰን እና አማራነትን የማስከበር ትግል ነው ብለዋል። ለዘላቂ የሕግ አሸናፊነት የሚያበቃን ሰላማዊ የትግል መንገድን መከተል መኾኑንም አመላክተዋል።

ከዚህ ውጭ በኀይል ተከዜን መሻገር የሚሞክር ኀይል ካለ ይህ የተከዜ ትውልድ የተከዜ ዘብነቱን በተግባር ማሳየት ይጠበቅበታል ብለዋል።

ተመራቂ መሪዎችም ከዚህ በፊት መሪ ኾነን መሳሪያ ብንታጠቅም የወታደራዊ ሳይንስ ልምድ አልነበረንም ነው ያሉት።

ከሥልጠናው ሰፊ ልምድ እና ዕውቀት ማግኘታቸውንም ተናግረዋል። ከውስጥ እና ከውጭ ለሚገጥም ፈተና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ያስችለናል ነው ያሉት።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሰላም አስከባሪ አስተባባሪ እና አሠልጣኝ ኮማንደር ድንቁ ቢረሳው መሪዎች እንደ ማንኛውም ሠልጣኝ ዝቅ ብሎ ምሽግ ውስጥ በማደር ሥልጠናውን ማጠናቀቅ መቻላቸው የሚደነቅ መኾኑን ገልጸዋል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: operation dismantle tplf, Tekeze Guard, wolkayit

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule