ይህ ለውጥ እውን ከሆነ በኋላ ሕዝብን ስሜታዊ የሚያደረጉ ተግባራት ናቸው በቅስቀሳ መልኩ የሚሰራጩት። ሰው ይገደልና ይሰቀላል። ተሰቅሎ ሲወገር ፊልም ይቀረጻል። ወዲያው ለሕዝብ ላይቭ ይለቀቃል። “እኔ ከእገሌ ብሔር አልተወለድኩም በል” እየተባለ ሰው በማንነቱ ሲገደል የሚያሳይ ፊልም በቅጽበት አየር ላይ እንዲውልና በብርሃን ፍጥነት እንዲሰራጭ ይደረጋል። ንጹሐን እንዲታገቱ ይደረግና እገታው በሚፈለገው መንገድ ተቀነባብሮ በማኅበራዊ ሚዲያ እንዲጎን ይደረጋል። ነፍሰጡር ስትሞት፣ ሕጻን እያየ አባት ሲገደል፣ ንብረት ሲቃጠልና ሌሎች በሟችና በሚወድመው ንብረት ሲዛበቱ የሚያሳይ ምስል በተቀናበረ ሁኔታ በማኅበራዊ ሚዲያዎች ይጦዛል። ይህ በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በማራ፣ አፋር … ሆኗል። አሁን ደግሞ መልኩን ቀይሮ እየሆነ ነው። ሲሆን ንጹሐን ላይ የደረሰን ጉዳት ለፖለቲካ ገበያ ለማዋል … [Read more...] about በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር
tplf terrorist
የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ
ለዘመናት የአፍሪካ ኅብረት ዋና ጽሕፈት ቤትን ከኢትዮጵያ ለማንሳት እጅግ በርካታ ሙከራዎች ተደርገዋል። ይቀርቡ የነበሩት ምክንያቶች ውሃ የማይቋጥሩ ሆነው በመገኘታቸው ሁሉም ስኬት እንደናፈቃቸው መና ሆነው ቀርተዋል። ሙከራው ግን አላቆመም፤ አሁንም ቀጥሏል። ኢትዮጵያ ከትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ የወንበዴ ቡድን ጋር ጦርነት የገጠመች ጊዜ ይኸው አጀንዳ ቀጠለ። ጦርነቱ ከነበረው በርካታ ድብቅ ዓላማዎች በዋነኛነት የሚጥቀሰው ይህ እንደነበር ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ይመሰክራሉ። በተለይ በኮቪድ ምክንያት የኅብረቱ ስብሰባ ለሁለት ዓመታት በመስተጓጎሉ በዚያው ከኢትዮጵያ ምድር ተረስቶ እንዲቀር ያልተፈነቀለ ድንጋይ አልነበረም። በተለይ የሰሜኑ ጦርነት "በአገሪቱ መረጋጋት የለም" ለሚለው አመክንዮ እንደ ማሳያ ተቆጥሮ ስብሰባው እንዳይካሄድ ከፍተኛ ጫና፣ ግፊት ሲደረግ በነበረበት ወቅት … [Read more...] about የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ
የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል
የኮማንዶ ብርጌዱ የተሣካ የተልዕኮ አፈፃፀሙ ታይቶና ተገምግሞ በ1992 ዓ.ም በክፍለጦር ደረጃ ማደጉ ይታወቃል፡፡ ከ2009 ዓ.ም ወዲህ ከክፍለጦር በላይ ሆኖ መደራጀቱም እንዲሁ፡፡ በሀገራችን ላይ የሚፈፀም ማንኛውንም ትንኮሳ መመከት እና መደምሰስ የሚችል አደረጃጀት ለመፍጠር በማሰብ የልዩ ኃይልና የአየር ወለድ አሃዱዎችን በማሥፋት የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የሚለውን ስያሜ እና አደረጃጀት አሁን ላይም ይዞ ይገኛል፡፡ የሚሠጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በእምነት የሚፈፅምና በከፍተኛ ፅናት ዘብ የሚቆም እንዲሁም በተሰማራበት የውጊያ ውሎ የውጊያው ማርሽ ቀያሪ እና አይበገሬ ሠራዊት በመገንባት ባሳለፍናቸው ዘመቻዎች አኩሪ የጀግንነት ገድል እንደ ዕዝ በመፈፀም የላቀ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል፡፡ በኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ሥር ካሉት ወታደራዊ የአቅም ግንባታ … [Read more...] about የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል
በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ
ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትና የሌሎች መንግሥታዊ ተቋማት አባል ነን በማለት ኅብረተሰቡን እያጭበረበሩ በሚገኙ ግለሰቦች ላይ ጥብቅ ክትትል በማድረግ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ ተገለጸ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢፕድ በላከው መረጃ እንዳመለከተው፤ ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት የደኅንነትና የሌሎች መንግሥታዊ ተቋማት አባል ነን የሚሉ ግለሰቦችን በተመለከተ በተለያዩ መንገዶች ክትትል ሲደረግ ቆይቷል። ሰሞኑን በተደረጉ ጥብቅ ክትትሎችም ፈለቀ ዴብሳ ደማ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02፤አስፋው አዳማ ሙታ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01፤ሳምሶን ገነነ መንገሻ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5፤ተስፋ ሀተው ገምቴሳ … [Read more...] about በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ
ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር”
የተፈራው የጦርነቱ የዜና መረጃዎች ብቅ ብቅ እያሉ ነው። ሆድ አስፍቶ፣ ጥርስን ነክሶ ሃቁን መቀበል ግድ ነው። ከልብ ሰባሪ የጦርነት ውጤት እውነተኛ ዜና ጦርነትን ለትርፍ ስትገለገሉበት የነበራችሁ ቢያንስ ዛሬ ላይ ተማሩ። ልጆቻችሁን በሙቅ ዕቅፋችሁ ይዛችሁ ደሃን ስታስጨርሱ የነበራችሁ ይብቃችሁ። “በዩትዩብ ስለፈልፍ ልጆቼ ተሳቀቁብኝ፤ ቤት መከራየት አለብኝ” ብለህ ዲሲ ምድር ቤት የተከራየኸውም ባክህን ይብቃህ። ምን ፈልገህና በየትኛው ብቃትህ አገር ለመምራት እንደምትቋምጥ የተረዳህ ሰው አይደለህምና ይብቃህ አቁም። ይህን ሁሉ እያየህ ዛሬም ታጋድላለህ። ዛሬም በየቀኑ መርዝህን ትረጫለህ። ከፍጹም ጥሪ ተማር። “በለው፣ ስበረው፣ ጀግና፣ ጥይት የማይነካህ … እያሉ ምክንያቱና ውጤቱ በውል በማይታወቅ ጉዳይ ወጣቱን ሲማግዱ የነበሩ ምን ይሉ ይሆን?” በሚል ከሰላም አማራጭ ስምምነቱ በኋላ … [Read more...] about ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር”
የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ!
የአማራ ልዩ ኃይል፣ ኢትዮጵያ ችግር በገጠማት ወቅት እንደ ብሔራዊ ጦር ያገለገለ የአገር ዘብ ነው። አማራን አዋርዳለሁ ብሎ የመጣውን ደግሞ ልኩን አሳይቶታል። የዘንድሮው ጀብዱማ ልዩ ነው። ትህነግ በሰላም ስምምነት ከባድ መሳርያ ጠጋግኖ አስረከብኩ ከማለቱ በፊት የአማራ ልዩ ኃይል በቡድን መሳርያ ከባድ መሳርያ ማርኮታል። በአስቸጋሪው ወቅት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የአማራ ልዩ ኃይልን አምኖበት "ከባድ መሳርያውን እንካ ተዋጋበት" ብሎት ተዋግቶ ድል አምጥቶበታል። ይህ ሰራዊት ኢትዮጵያን ለማዳን ከትህነግ ጋር ተናንቆ ክብር ያስጠበቀ የአገር ባለውለታ ነው። ትህነግ ከባድ መሳርያ ለመስጠት ብቻ አይደለም፤ በክፋቱ ባያስረክብ እንኳ ትጥቅ ለመደበቅም የተገደደው በእነዚህ ነብሮች መስዋዕትነት ጭምር ነው። ትህነግ ዓለምን ለምኖ ተኩስ ይቁምልኝ ያለው የእነዚህን ጀግኖች ተኩስንም … [Read more...] about የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ!
መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ
ክፍለ ጦሩ በሸኔ ላይ እየተወሠደ ያለውን ወታደራዊ እርምጃ ለማጠናከር በጉጂ ዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ ሚሊሻዎችን በማሰልጠን የቀጠናውን ሠላምና ፀጥታ በማረጋገጡ ረገድ ውጤታማ ሥራ መሠራቱን አሥታውቋል፡፡የስልጠናው ዋና አስተባባሪ ሻምበል ባቡ ባላባት እንደገለፁት የፀረ ሽምቅ ግዳጅን በብቃት ከመወጣት ጎን ለጎን የዞኑን የፀጥታ ሀይል ለማጠናከር በርካታ ሚሊሻዎችን የአካል ብቃት የስልት እንዲሁም የተኩስ ልምምድ ሥልጠና በመስጠት ማሥመረቅ ተችሏል፡፡በአካባቢው በንፁሃን ላይ የሽብር ተግባር ሲፈፅም በቆየው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ላይ እየተወሠደ ለሚገኘው የተጠናከረ ዘመቻ ሠልጣኝ የሚሊሻ ሃይሉ እገዛ ከፍተኛ መሆኑንም የሥልጠና አሥተባባሪው ገልፀዋል፡፡አሰልጣኝ ዋና ሳጅን ዝናው በበኩላቸው እንደገለፁት የሚሊሻ አባላቱን አሠልጥኖ ማሥመረቁ በቀጠናው የሚገኘውን የፀጥታ ሃይል የሚያጠናክር … [Read more...] about መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ
“ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ
የግሪጎርያኑን የቀን መቁጠሪያ የሚጠቀሙት የኤርትራውያን ፕሬዚዳንት በዚሁ “በነጮች አዲስ ዓመት” ተብሎ በሚጠራው ቀን ስም ”[ትህነግን] ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” ዓይነት ንግግር አሰምተዋል። ስጋት እንደሌለ ማስታወቃቸው እንደሆነ ተመልክቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሚመራው ጥምር ጦር ሽሬን መቆጣጠሩን ተከትሎ ትህነግ የወሰደውና እንዲወስድ የተመከረው ምክር ከደርግ ጋር እንደሚመሳሰል ተጠቆመ። “ቢሆንም ቅሉ፣ ይሁን እንጂ” በሚሉ መገጣጠሚያዎች አጅቦ፣ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ “ትንኮሳንና ጸብ አጫሪዎችን” ሲሉ በደፈናው አስታውቀው ሰራዊታቸው እንዳስተነፈሰ መናገራቸውን ቀድሞ የዘገበው ቢቢሲ ነው። የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባርን (ትህነግን) በስም መጥራት ያልፈጉት ኢሳያስ ፀብ ጫሪና ተንኳሽ ኃይል መሆኑን ጠቅሰው አሁን ግን ነገሮች መቀየራቸውን አመልክተዋል። ጦራቸውን አመስግነው … [Read more...] about “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ
[ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም”
የኤርትራን “ውለታ መርሳት ነውር ነው” “ውለታን መርሳት ነውር ነው” በሚል የመንግሥት ቁርጥ ያለ አቋም የተገለጸው “ተቃዋሚ” ፓርቲዎችን በመሰብሰብ “የኤርትራ ሠራዊት ከትግራይ ለምን አይወጡም በሚል ተደራራቢ ጥያቄ መልስ ሲሰጥ ነው። “በሦስተኛው ዙር አገሪቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለማፍረስ በተካሄደው ጦርነት” አሉ አቶ ሬድዋን፣ “የፌዴራል መንግሥት በቆቦ በኩል ባለው ዳገት ወደ ላይ መውጣት ስላዳገተው፣ ትህነግ ያለውን መልክዓ ምድራዊ ጠቀሜታ ተጠቅሞ ቆቦን ተቆጣጥሮ ነበር” ሲሉ ኤርትራን እንደ ጠላት በማየት ጥያቄ ላቀረቡት ምስላዊ ማብራሪያ ሰጡ። ይህ ሲሆን ወቅቱ ክረምት መሆኑ ችግሩን እንዳባባሰው ካስታወሱ በኋላ “በዝናብ ምክንያት በምዕራብ በኩል ተከዜን የኢትዮጵያ ሠራዊት ማቋረጥ ባለመቻሉ፣ አቅጣጫ ቀይሮ ያለ ሥጋት በዛላምበሳና በአዲግራት በኩል ተከዜን እንዲሻገር የኤርትራ … [Read more...] about [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም”
የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ
ትግራይ አሁን ያለችበት ሁኔታ እንዴት እንደደረሰችና በትህነግ የተፈጸመውን ከአእምሮ ያለፈ ግፍ ምን እንደ ሆነ በጥቂቱ ለማወቅ ይህንን ፕሮፌሰር ሐረገወይን አሰፋ የሰጡትን ቃለምልልስ መስማት የግድ ይላል። ባለ ማህተምነታቸው አንገታቸው ላይ የሚታይና ሃይማኖተኛ ነን ለማለት ቀዳሚ ተሰላፊ የሚሆኑት ትህነግ የላካቸው የትግራይ ወራሪዎች በአማራና በአፋር ክልል መነኩሴ እስከመድፈር የደረሱት ለምን ይሆን ለሚለው ጥያቄ በቂ ፍንጭ የሚሰጥ ነው ቃለ ምልልሱ። እውነተኛው የትግራይ ባሕል ሌላ ሳይሆን ይኽ ወረርሽኝ ነው። ሌላው ሥር የሰደደ ነውረኝነትን ለመሸፈን የሚሰጥ ማባበያ ነው። ትግራይ በዚህ ልክ ከሞራል ልዕልና የወረደች ሆና ትጥቅ መፍታትም ሆነ ለውጥ ማምጣት የማይታሰብ ነው። ሐረገወይን እንደሚሉት በትግራይ በተለይ በእናቶችና ሴቶች ላይ ሥርነቀል የባሕል አቢዮት ማካሄድ የግድ … [Read more...] about የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ