በክምር ድንጋይ አንድ የአማራ ጀግና 11 የአሸባሪው ትህነግ ታጣቂዎችን ደመሰሰ። የአሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ታጣቂዎች በክምር ድንጋይ ከተማ ወደ አንድ ግለሰብ ቤት በመሄድ ለማጥቃትና ለመዝረፍ ተዘጋጁ። ታጣቂዎች ግለሰቡ ቤት ደረሱ። ይህንን ቀድሞ የተረዳው ግለሰብም በጥበብና በብልሃት የመጡትን የአሸባሪውን ቡድን ታጣቂዎች አዘናጋቸው። ሌላ ኃይል አብሯቸው እንደሌለ ወደ ውጪ ወጣ በማለት ካረጋገጠ በኋላ ወደ ጓዳው በመግባት ተቀባብሎ የነበረውን መሣሪያ ይዞ በመውጣት እርምጃ ወስዶባቸዋል። ሊያጠቁትና ሊዘርፉት እንደመጡ የተረዳው ይህ ግለሰብ ያለውን መሣሪያ በመጠቀም በቤቱ የተሰበሰቡትን 11 የአሸባሪውን ትህነግ ታጣቂዎች እንዳልሆኑ በማድረግ ጀግንነቱን አሳይቷል። አሁን ላይም ይህ ጀግና ቀሪ የአሸባሪውን ቡድን አባላትን እያሳደደ ይገኛል። ጠላትን አይቀጡ … [Read more...] about በክምር ድንጋይ የተሠራ ጀብድ
tplf terrorist
የሁርሶ ሠልጣኞች በብቃት እየተዘጋጁ ነው
"ሀገርን ለማዳን እዘምታለሁ የትም መቼም በምንም" በሚል መሪ ቃል ፀረ ሰላም ሀይሎችን ለመፋለም ቆርጠው የተነሱ የቁርጥ ቀን ልጆች በሀገሪቷ በሚገኙ የውትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች በመግባት ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡ የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ከዚህ ቀደም በርካታ የሰራዊት አባላትን በሁለት ዙሮች አሰልጥኖ ያስመረቀ ሲሆን÷ በአሁኑ ጊዜም የ3ኛ ዙር ሰልጣኞችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡ አሰልጣኝ የ22ኛ ሻለቃ ዘመቻ ሀላፊ መቶ አለቃ ዲኔ መሀመድ የዚህ ዙር ሰልጣኞች ከሁለቱ ዙር ሰልጣኞች ለየት የሚያደርገው ሀገርን ለማፈራረስ የተነሱት የሀገር ሀዲዎች የህወሓት እና የሸኔ የሽብር ቡድኖችን ለመፋለምና ሀገርን ከመፈራረስ ታድጎ አንድነቷን ለማስቀጠል ለሀገሬ እዘምታለሁ በማለት ሀገራዊ ጥሪውን ተቀብለው ወደ ስልጠናው የተካተቱ መሆናቸው ነው … [Read more...] about የሁርሶ ሠልጣኞች በብቃት እየተዘጋጁ ነው
በጁባ የተበጣጠሰው የጁንታው የሽብር መረብ
ኢትዮጵያ ባለብዙ ጀግኖች ሃገር ናት ኢትዮጵያ ሃገራችን ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር ተግባር ከ1951 በኮርያ የጀመረው የሰላም አምባሳደርነት በሩዋንዳ በኮንጎ በቡርንዲ በላይቤርያ በዳርፉር በአብዬ በሱማሊያ እና ደቡብ ሱዳን ሰላም ላጡ ህዝብ ሰላምን አስፍኖ ለተራበው አጉርሶ ለተጠማው አጠጥቶ ዛሬም በአለም አደባባይ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ብሎ ለሰላም ተመራጭ የሆነ ሃይል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ነው። ታድያ ዛሬም በቡዙ ሺዎች የሚቆጠር የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በአለም ሰላም ማስከበር ላይ ተሰማርቶ በጀግንነትና በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን በከፍታ ማማ ላይ ያለ ሠራዊትን ሊነቀንቁት አስበው በደቡብ ሱዳን ጁባ የሚገኝውን የ13ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃን ላይ ደም ለማፋሰስ የሽብር ተግባር ለመፈፀምና የኢትዮጵያ ሃገራችንን ገፅታ ለማበላሸት … [Read more...] about በጁባ የተበጣጠሰው የጁንታው የሽብር መረብ



