• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በመከላከያ ውስጥ ለትህነግ ሲሰልሉ የነበሩ ጽኑ እስራት ቅጣት ተላለፈባቸው

August 27, 2021 11:56 am by Editor Leave a Comment

ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባላቸው የሰራዊት አባላት ላይ ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት የሚደርስ የፅኑ እስራት ውሳኔ ተላለፈ።

የደቡብ ዕዝ ቀዳማዊ ወታደራዊ ፍርድ ቤት በተለያዩ ወንጀሎች ተሳትፎ በነበራችውና ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባላቸው የሰራዊት አባላት ላይ ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት በሚደርስ የፅኑ እስራት  ውሳኔ ማስተላለፉ ተገለፀ።

ነሐሴ 20 ቀን 2013 ዓ.ም በዕዙ ጠቅላይ መምሪያ በዋለው ችሎት የተሰየመው የዳኞች ምድብ 8 የክስ መዝገቦችን መርምሮ ነው ውሳኔ የሰጠው።

በዚህ መሰረት፣

በ1ኛ መዝገብ እነ ኮሎኔል ካህሱ ሀብቱ ፀልይ፣ ኮሎኔል ሀጎስ አሰፋ ወልደንጉሴ እና ሌተናል ኮሎኔል ሀይላይ ገብሩ ገብረተክላይ

በ2ኛ መዝገብ ሻምበል ባሻ ክፍሌ ፍስሃ

በ3ኛ መዝገብ ኮሎኔል ክፍሌ ፍስሃ

በ4ኛ መዝገብ ሃምሳ አለቃ መብርሃቱ ጥላየ

በ5ኛ መዝገብ መሰረታዊ ወታደር መኮነን ክንፈ

በ6ኛ መዝገብ ሃምሳ አለቃ ፈረደ ይባስ

በ7ኛ መዝገብ ምክትል አስር አለቃ ሀጎስ በርሄ

በ8ኛ መዝገብ ምክትል አስር አለቃ ክፍሌ ንጉሴ የክስ መዝገባቸው እንዲታይ መደረጉም ታውቋል።

በዚህ መሰረት በ1ኛ መዝገብ ክሳቸው ሲታይ የነበረው እነ ኮሎኔል ካህሱ ሀብቱ ፀልይ ጥቅምት 27 ቀን 2013 ዓ.ም ሰራዊቱ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በግዳጅ ላይ ተሰማርቶ እያለ የትግርኛ ተናጋሪ የሰራዊት አባላትን ብቻ ነጥሎ በመሰብሰብ ከተቋሙ የአመራር እርከን ውጪ ለጥፋት ስራዎች የሚያግዝ አደረጃጀት ፈጥረዋል ተብሏል።

በዚህ አደረጃጀት በመታገዝም በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ የተፈፀመውን ዘግናኝ ድርጊት በሚመሯቸው የሰራዊት አባላት ዘንድ ለመድገም አቅደው ሲሰሩ መቆየታቸው በክስ መዝገባቸው ሰፍሯል።

ተከሳሾቹ ከእነሱ ብሄር ውጪ አብረዋቸው የሚሰሩ ከፍተኛ አመራሮችን በመግደል ሙሉ ሰራዊቱን ወደትግራይ ይዘው ለመግባት አቅደው እንደነበርም በችሎቱ ተነስቷል።

በተለይም የህግ ማስከበር ዘመቻው እንደተጀመረ የትግራይ ተወላጅ የሰራዊት አባላት ወደ አንድ ማዕከል መሰብሰባቸውን ተከትሎ ተከሳሾቹ የተመደቡላቸውን ጥበቃዎች በመግደልና ወደ ኬኒያ በመውጣት ኤምባሲ ሄደው የትግራይ ህዝብ እየተበደለ ነው በማለት የሃገራቸውን ስምና ዝና ለማጉደፍ ሲሰሩ ነበር ብሏል ችሎቱ ።

በቀሩት 7 መዝገቦች የታዩት የሰራዊት አባላት ሰራዊቱን ወደትግራይ ልዩ ሃይል በመመልመል፣ የሽብር ወሬዎችን በመንዛት፣ ተቋሙን በሚያፈርሱ ተግባራት ላይ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን፣ በህጋዊ ፍቃድ ሽፋን የትግራይን ልዩ ሃይል የሚያሰለጥኑ አባላትን ወደቦታው በመላክ፣ በሰራዊቱ ውስጥ አንድነት እንዳይኖር ስጋቶችን በማስፈን፣ በህቡዕ ተደራጅቶ ሰራዊቱን ለማፍረስ በመጣር እና መላው የሰራዊት አባል በመንግስት ላይ እምነት እንዳይኖረው የሚያደርጉ ተግባራትን በሰፊው ሲተገብሩ መቆየታቸው በችሎቱ ተጠቅሷል።

በዚህ መሰረት የግራ ቀኙን የተመለከተው ፍርድ ቤት የአቃቤ ህግን የቅጣት ማክበጃ እንዲሁም የተከላካይ ጠበቃን የቅጣት ማቅለያ ከግምት ውስጥ በማስገባት ተከሳሾችን ያስተምራል፣ ሌሎች የሰራዊት አባላትን ያስጠነቅቃል በሚል ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Middle Column, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule