• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በመከላከያ ውስጥ ለትህነግ ሲሰልሉ የነበሩ ጽኑ እስራት ቅጣት ተላለፈባቸው

August 27, 2021 11:56 am by Editor Leave a Comment

ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባላቸው የሰራዊት አባላት ላይ ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት የሚደርስ የፅኑ እስራት ውሳኔ ተላለፈ።

የደቡብ ዕዝ ቀዳማዊ ወታደራዊ ፍርድ ቤት በተለያዩ ወንጀሎች ተሳትፎ በነበራችውና ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባላቸው የሰራዊት አባላት ላይ ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት በሚደርስ የፅኑ እስራት  ውሳኔ ማስተላለፉ ተገለፀ።

ነሐሴ 20 ቀን 2013 ዓ.ም በዕዙ ጠቅላይ መምሪያ በዋለው ችሎት የተሰየመው የዳኞች ምድብ 8 የክስ መዝገቦችን መርምሮ ነው ውሳኔ የሰጠው።

በዚህ መሰረት፣

በ1ኛ መዝገብ እነ ኮሎኔል ካህሱ ሀብቱ ፀልይ፣ ኮሎኔል ሀጎስ አሰፋ ወልደንጉሴ እና ሌተናል ኮሎኔል ሀይላይ ገብሩ ገብረተክላይ

በ2ኛ መዝገብ ሻምበል ባሻ ክፍሌ ፍስሃ

በ3ኛ መዝገብ ኮሎኔል ክፍሌ ፍስሃ

በ4ኛ መዝገብ ሃምሳ አለቃ መብርሃቱ ጥላየ

በ5ኛ መዝገብ መሰረታዊ ወታደር መኮነን ክንፈ

በ6ኛ መዝገብ ሃምሳ አለቃ ፈረደ ይባስ

በ7ኛ መዝገብ ምክትል አስር አለቃ ሀጎስ በርሄ

በ8ኛ መዝገብ ምክትል አስር አለቃ ክፍሌ ንጉሴ የክስ መዝገባቸው እንዲታይ መደረጉም ታውቋል።

በዚህ መሰረት በ1ኛ መዝገብ ክሳቸው ሲታይ የነበረው እነ ኮሎኔል ካህሱ ሀብቱ ፀልይ ጥቅምት 27 ቀን 2013 ዓ.ም ሰራዊቱ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በግዳጅ ላይ ተሰማርቶ እያለ የትግርኛ ተናጋሪ የሰራዊት አባላትን ብቻ ነጥሎ በመሰብሰብ ከተቋሙ የአመራር እርከን ውጪ ለጥፋት ስራዎች የሚያግዝ አደረጃጀት ፈጥረዋል ተብሏል።

በዚህ አደረጃጀት በመታገዝም በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ የተፈፀመውን ዘግናኝ ድርጊት በሚመሯቸው የሰራዊት አባላት ዘንድ ለመድገም አቅደው ሲሰሩ መቆየታቸው በክስ መዝገባቸው ሰፍሯል።

ተከሳሾቹ ከእነሱ ብሄር ውጪ አብረዋቸው የሚሰሩ ከፍተኛ አመራሮችን በመግደል ሙሉ ሰራዊቱን ወደትግራይ ይዘው ለመግባት አቅደው እንደነበርም በችሎቱ ተነስቷል።

በተለይም የህግ ማስከበር ዘመቻው እንደተጀመረ የትግራይ ተወላጅ የሰራዊት አባላት ወደ አንድ ማዕከል መሰብሰባቸውን ተከትሎ ተከሳሾቹ የተመደቡላቸውን ጥበቃዎች በመግደልና ወደ ኬኒያ በመውጣት ኤምባሲ ሄደው የትግራይ ህዝብ እየተበደለ ነው በማለት የሃገራቸውን ስምና ዝና ለማጉደፍ ሲሰሩ ነበር ብሏል ችሎቱ ።

በቀሩት 7 መዝገቦች የታዩት የሰራዊት አባላት ሰራዊቱን ወደትግራይ ልዩ ሃይል በመመልመል፣ የሽብር ወሬዎችን በመንዛት፣ ተቋሙን በሚያፈርሱ ተግባራት ላይ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን፣ በህጋዊ ፍቃድ ሽፋን የትግራይን ልዩ ሃይል የሚያሰለጥኑ አባላትን ወደቦታው በመላክ፣ በሰራዊቱ ውስጥ አንድነት እንዳይኖር ስጋቶችን በማስፈን፣ በህቡዕ ተደራጅቶ ሰራዊቱን ለማፍረስ በመጣር እና መላው የሰራዊት አባል በመንግስት ላይ እምነት እንዳይኖረው የሚያደርጉ ተግባራትን በሰፊው ሲተገብሩ መቆየታቸው በችሎቱ ተጠቅሷል።

በዚህ መሰረት የግራ ቀኙን የተመለከተው ፍርድ ቤት የአቃቤ ህግን የቅጣት ማክበጃ እንዲሁም የተከላካይ ጠበቃን የቅጣት ማቅለያ ከግምት ውስጥ በማስገባት ተከሳሾችን ያስተምራል፣ ሌሎች የሰራዊት አባላትን ያስጠነቅቃል በሚል ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Law, Middle Column, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • ሰብዓዊ እርዳታ ወደ መቀሌ መግባት መቀጠሉ ተገለጸ May 16, 2022 03:07 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule