• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በመከላከያ ውስጥ ለትህነግ ሲሰልሉ የነበሩ ጽኑ እስራት ቅጣት ተላለፈባቸው

August 27, 2021 11:56 am by Editor Leave a Comment

ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባላቸው የሰራዊት አባላት ላይ ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት የሚደርስ የፅኑ እስራት ውሳኔ ተላለፈ።

የደቡብ ዕዝ ቀዳማዊ ወታደራዊ ፍርድ ቤት በተለያዩ ወንጀሎች ተሳትፎ በነበራችውና ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባላቸው የሰራዊት አባላት ላይ ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት በሚደርስ የፅኑ እስራት  ውሳኔ ማስተላለፉ ተገለፀ።

ነሐሴ 20 ቀን 2013 ዓ.ም በዕዙ ጠቅላይ መምሪያ በዋለው ችሎት የተሰየመው የዳኞች ምድብ 8 የክስ መዝገቦችን መርምሮ ነው ውሳኔ የሰጠው።

በዚህ መሰረት፣

በ1ኛ መዝገብ እነ ኮሎኔል ካህሱ ሀብቱ ፀልይ፣ ኮሎኔል ሀጎስ አሰፋ ወልደንጉሴ እና ሌተናል ኮሎኔል ሀይላይ ገብሩ ገብረተክላይ

በ2ኛ መዝገብ ሻምበል ባሻ ክፍሌ ፍስሃ

በ3ኛ መዝገብ ኮሎኔል ክፍሌ ፍስሃ

በ4ኛ መዝገብ ሃምሳ አለቃ መብርሃቱ ጥላየ

በ5ኛ መዝገብ መሰረታዊ ወታደር መኮነን ክንፈ

በ6ኛ መዝገብ ሃምሳ አለቃ ፈረደ ይባስ

በ7ኛ መዝገብ ምክትል አስር አለቃ ሀጎስ በርሄ

በ8ኛ መዝገብ ምክትል አስር አለቃ ክፍሌ ንጉሴ የክስ መዝገባቸው እንዲታይ መደረጉም ታውቋል።

በዚህ መሰረት በ1ኛ መዝገብ ክሳቸው ሲታይ የነበረው እነ ኮሎኔል ካህሱ ሀብቱ ፀልይ ጥቅምት 27 ቀን 2013 ዓ.ም ሰራዊቱ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በግዳጅ ላይ ተሰማርቶ እያለ የትግርኛ ተናጋሪ የሰራዊት አባላትን ብቻ ነጥሎ በመሰብሰብ ከተቋሙ የአመራር እርከን ውጪ ለጥፋት ስራዎች የሚያግዝ አደረጃጀት ፈጥረዋል ተብሏል።

በዚህ አደረጃጀት በመታገዝም በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ የተፈፀመውን ዘግናኝ ድርጊት በሚመሯቸው የሰራዊት አባላት ዘንድ ለመድገም አቅደው ሲሰሩ መቆየታቸው በክስ መዝገባቸው ሰፍሯል።

ተከሳሾቹ ከእነሱ ብሄር ውጪ አብረዋቸው የሚሰሩ ከፍተኛ አመራሮችን በመግደል ሙሉ ሰራዊቱን ወደትግራይ ይዘው ለመግባት አቅደው እንደነበርም በችሎቱ ተነስቷል።

በተለይም የህግ ማስከበር ዘመቻው እንደተጀመረ የትግራይ ተወላጅ የሰራዊት አባላት ወደ አንድ ማዕከል መሰብሰባቸውን ተከትሎ ተከሳሾቹ የተመደቡላቸውን ጥበቃዎች በመግደልና ወደ ኬኒያ በመውጣት ኤምባሲ ሄደው የትግራይ ህዝብ እየተበደለ ነው በማለት የሃገራቸውን ስምና ዝና ለማጉደፍ ሲሰሩ ነበር ብሏል ችሎቱ ።

በቀሩት 7 መዝገቦች የታዩት የሰራዊት አባላት ሰራዊቱን ወደትግራይ ልዩ ሃይል በመመልመል፣ የሽብር ወሬዎችን በመንዛት፣ ተቋሙን በሚያፈርሱ ተግባራት ላይ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን፣ በህጋዊ ፍቃድ ሽፋን የትግራይን ልዩ ሃይል የሚያሰለጥኑ አባላትን ወደቦታው በመላክ፣ በሰራዊቱ ውስጥ አንድነት እንዳይኖር ስጋቶችን በማስፈን፣ በህቡዕ ተደራጅቶ ሰራዊቱን ለማፍረስ በመጣር እና መላው የሰራዊት አባል በመንግስት ላይ እምነት እንዳይኖረው የሚያደርጉ ተግባራትን በሰፊው ሲተገብሩ መቆየታቸው በችሎቱ ተጠቅሷል።

በዚህ መሰረት የግራ ቀኙን የተመለከተው ፍርድ ቤት የአቃቤ ህግን የቅጣት ማክበጃ እንዲሁም የተከላካይ ጠበቃን የቅጣት ማቅለያ ከግምት ውስጥ በማስገባት ተከሳሾችን ያስተምራል፣ ሌሎች የሰራዊት አባላትን ያስጠነቅቃል በሚል ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Middle Column, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule