የዛሬ ስድስት ዓመት የግንቦት 20 መርዛማ ፍሬዎች በሚል ርዕስ በአምስት ተከታታይ ጽሑፎች የግንቦት 20ን አስራ አምስት መርዛማ ፍሬዎች አስነብ በን ነበር። ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር በማለት የሚጠራውና አሁን ምንም ዓይነት ሕጋዊ ማንነት የሌለው የበረሃ ወንበዴዎች ስብስብ የተከለው መርዛማ ዛፍ ያበቀላቸው መርዛማ ፍሬዎች አሁን ላይ በገሃድ የሚታዩ መሆናቸው ተረስቶ ትርክቱ ሌላ በሆነበትና በወያኔ በርበሬ የታጠኑ አንዳንዶች ትሕነግ ናፈቀን እያሉ ሲሰሙ ባለበት ጊዜ ይህንን ጽሑፍ መልሶ መቃኘት አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት ድጋሚ ታትሟል። ይህ የመጨረሻው ጽሑፍ ሲሆን ከዚህ በፊት የታተሙትን አራት ተከታታይ ጽሑፎች አንባቢያን እንዲያነቡ እንጋብዛለን። የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! (ክፍል 1)የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመሬት ነጠቃና ስደት (ክፍል … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! “ክፋት” – በሁሉም መስክ!!
tplf terrorist
“ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
በሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር / ትህነግ መገኘቱ ይፋ መሆኑን ተከትሎ አማራ ክልል ውስጥ ያሉ ታጣቂዎችን ከፍፍሏል። ትህነግ በድርጅት ደረጃ በውስጡ አለመጋባባት እንዳለበት፣ ከጊዜያዊ አስተዳደሩም ጋር ስምምነት እንደሌለው ይፋ መሆኑንን ተከትሎ ዳዊት ከበደ አቶ ጌታቸው ረዳ “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል” ሲል ሚስጢር ያለውን ይፋ አድርጓል። በመረጃው ለምን አቶ ጌታቸው ብቻ ተለይተው በዚህ ጉዳይ ግንባር ሊሆኑ እንደቻሉ ወይም እንደተፈልገ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም። በተደጋጋሚ እንደሚባለው ከራያ ወገን መሆናቸው ለያዙት ስልጣን ችግር … [Read more...] about “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
ፌዘኛው ትሕነግ አንድም ታጣቂ የለኝም አለ
በሱዳን የተለያዩ የሰደተኛ ካምፖች፣ እንዲሁም በከተሞችና በተለዩ ሥፍራዎች የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትሕነግ) ያደራጃቸውና "ሳምሪ" የሚባሉ ታጣቂዎች መስፈራቸው በተደጋጋሚ ተገልጿል። በማስረጃና በመረጃ ወደ ሱዳን ማቅናታቸው ሲገለጽ ጎን ለጎን እነዚሁ ታጣቂዎች በማይካድራ ጭፍጨፋ፣ ከግብጽና ሱዳን ሰፊ ድጋፍ አግኝተው ራሳቸውን ለጦርነት እያዘጋጁ መሆኑ በተለያዩ አውዶች ሲገለጽ ነበር። ትሕነግ "የትግራይን ሕዝብ ነጻ አወጣለሁ" ብሎ ሲነሳ ጀምሮ ከሱዳን ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው እንደሆነ አባላቱና አመራሩ በኩራትና በውለታ ቆጣሪነት መስክረዋል። "ከአማራ ይልቅ የሱዳን ህዝብ ይሻለናል" በሚል በግልጽ ንግግርም ተደርጎ እንደነበር ይህ ትውልድ ያስታውሳል። ግንቦት ሃያ መቀሌ ሲከበር የቀድሞው የሱዳን መሪ አልበሽር የትሕነግን መለያ ለብሰው በበዓሉ ላይ እንደ ቤተሰብ ይጋበዙ … [Read more...] about ፌዘኛው ትሕነግ አንድም ታጣቂ የለኝም አለ
ማንን እንመን ትህነግን? ወይስ ያየነውን፣ የሰማነውንን በዓይናችን የመሰከርነውን?
ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am by Editor 2 Comments (Edit) በማይካድራ ሳምሪ በተሰኙ የተደራጁ ወጣቶች የተፈጸመው የጅምላ ጭፍጨፋ ቦኮሀራም ናይጄሪያ ላይ በተመሳሳይ ወር ከፈፀመው ወንጀል የበለጠ እንደሆነ ኢንተርፖል አስታወቀ። ዓለም አቀፉ የፖሊስ ትብብር ተቋም ኢንተርፖል በፈረንጆቹ የዘመን አቆጣጠር በወርሃ ህዳር 2020 ዓ.ም በመላው ዓለም የተፈፀሙ 10 አስከፊ የሽብር ጥቃት አስመልክቶ ሪፖርቱን አውጥቷል። እንደዚህ ሪፖርት ከሆነ በህወሃት ቡድን አደራጅነት ማይካድራ ላይ የተፈፀመው የጅምላ ግድያ ቦኮሃራምና ሌሎች የሽብር ቡድኖች በተለዩ ሀገራት ከፈፀሟቸው አሰቃቂ ጭፍጨፋዎች በመብለጥ በርካታ ንፁሃን ሰዎች ህይወታቸውን ያጡበት ኢሰብዓዊ ድርጊት … [Read more...] about ማንን እንመን ትህነግን? ወይስ ያየነውን፣ የሰማነውንን በዓይናችን የመሰከርነውን?
Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF
Sudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of fighting in Sudan in support of the Sudanese Armed Forces (SAF). Civil war broke out in Sudan in April last year involving Rapid Support Forces (RSF) led by Hamdan Dagalo and Sudanese Armed Forces (SAF) led by military chief Abdul Fattah al Burhan. Several regional and international players are involved in Sudanese civil war. Around a month ago, Sudanese military lodged a formal … [Read more...] about Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF
የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ማረጋገጫ ሰጠ
* በ“ጋዜጠኛነት” ስም የሚፈጸመው የሚዲያ ሸፍጥ በትግራይ ክልል "ከ200 በላይ ኢንዱስትሪዎች ሥራ ጀምረዋል" በሚል ፓርላማ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበው ሪፖርት "ከእውነት የራቀ ነው" ሲሉ የከሰሱት የትግራይ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ 212 ኢንዱስትሪዎች ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ሥራ እንዲጀመሩ ክስ ባቀረቡበት ዜና ጎን ለጎን አስታወቁ። ዜናው የክስ ሳይሆን አሃዱና ቲክቫህ በቅብብሎሽ አንዱ ሌላውን ዋቢ አድርገው ባሰራጩት ዜና መግቢያና ርዕስ ቀዳሚ ያደረጉት "ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፓርላማ ያቀረቡት ሪፖርት ከዕውነት የራቀ ነው" በሚል ነው። ዜናው በመሪ ርዕሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የቀረበውን ክስ አላብራራም፣ እርሳቸው ካሉት ጋርም አላነጻጸረም። የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ መሐሪ ገብረሚካኤል "በአሁኑ ወቅት በክልሉ ሥራ የጀመሩት ለትላልቅ … [Read more...] about የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ማረጋገጫ ሰጠ
37 ቢሊዮን ብር የት ገባ? “ትግራይ ውስጥ አዲስ አጀንዳ ተተከለ”
ትግራይን ማቃናት ያቃተው ካድሬ - አቅቶሃል ተባለ “ሰላሳ ሰባት ሚሊዮን ብር ለትግራይ አስተዳደር መሰጠቱን ስንሰማ ደንገጠናል። ዜናውን የሰሙ ሁሉ ብሩ የት ገባ? የሚል ጉምጉምታ እያሰሙ ነው። አካል ጉዳተኞች ጸጉራቸውን እየነጩ ነው። ጉዳዩን ትግራይ ያሉ ፖለቲከኞችም እየመከሩበት ነው። ሕዝብ ተናድዷል” ስትል ተቀማጭነቷ አዲስ አበባ የሆነ የትግራይ ተወላጅ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ተባባሪ ነግራዋለች። ወጣቷ በጦርነቱ አንድ ወንድሟን አጥታለች። ኮምቦልቻ እስከሚደርስ በሕይወት ስለመኖሩ መረጃ እንደነበራት፣ ከዚያ በኋላ ደብዛው ጠፍቶባት መጨረሻ ላይ እናቷ መርዶ እንደተነገራቸው የምትናገረዋ ወጣት፣ ስለ ትሕነግ (የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር) ስትናገር ያንዘዘርታል። ኃላፊዎቹን ስታያቸው ያማታል። ኃፍረትና ጸጸት የሚባል ነገር ያልፈጠረባቸው መሆናቸውን ስታስብ... “ትግራይን … [Read more...] about 37 ቢሊዮን ብር የት ገባ? “ትግራይ ውስጥ አዲስ አጀንዳ ተተከለ”
ትህነግ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያካሂደውን ሽብር እንደሚቀጥል አስታወቀ
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትሕነግ) በማለት ራሱን የሚጠራው ቡድን በዓለምአቀፉ የአሸባሪ ቋት ተመዝግቦ የሚገኘው የወንበዴዎች ስብስብ ነው። ከስድሳ ቀናት በላይ ስብሰባ ተቀምጦ የነበረው ትህነግ የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደሚገባው አልተተገበረም በሚል በመንግሥት ላይ የተቃውሞ መግለጫ አውጥቶ ነበር። በቀጣይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በጥር 23 ቀን 2016 ዓም ለትሕነግ መግለጫ አጸፋ ምላሽ የሰጠ ሲሆን በዋነኝነት ስምምነቱን ለመተግበር መንግሥት እንዴት ከሚገባው በላይ ርቀት እንደሄደ የጠቆመ ነበር። እንደ ማሳያም ከስምምነቱ ወዲህ መንግሥት ለትግራይ ክልል ከ37 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን ገልጾዋል። ለዚህ የመንግሥት ምላሽ ትሕነግ የአጸፋ ምላሽ ሰኞ የሰጠ ሲሆን ለክልሉ የተደረገውን 37 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ምንም ዓይነት ዕውቅና ሳይሰጥ የፕሪቶሪያው … [Read more...] about ትህነግ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያካሂደውን ሽብር እንደሚቀጥል አስታወቀ
ከትሕነግ ጋር ለማበር ወልቃይትን መስዋዕት የሚያደርጉ የ”አማራ ነጻ አውጪዎች”
ከትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትሕነግ) ጋር አብሮ "የጠብ መንጃ ትግሉን ማጧጧፍ" በሚል ከውሳኔ የደረሱ ክፋይ የ"አማራ ነጻ አውጪ" ኃይሎች መኖራቸው ተሰማ። ለስምምነቱ ትሕነግ ምዕራብ ትግራይ የሚለውንና አሁን "ነጻ ወጥቷል" የሚባለውን ወልቃይት ተላልፎ እንዲሰጥ ፈቃደኝነት ያለበት እንደሆነ ተመልክቷል። ራሳቸውን በተለያዩ አካባቢያዊና አደረጃጀት ከሰየሙት መካከል አሁን አንድ ለመሆን እየሠሩ እንደሆነ የሚነገርላቸው በዝናቡ የሚመራው የጎጃም ዕዝና የዘመነ ካሴ ኃይል ነው ይህን ስምምነት ለማድረግ እየሠራ እንደሆነ የተሰማው። “ጊዜው አሁን ነው፤ ይህንን ጊዜ ልንጠቀምበት ይገባል” በሚል በገሃድ ወልቃይትን ዳግም በኃይል ለመያዝ ደብረጽዮን በቅርቡ መናገሩ ይታወሳል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ከሕዝብ ጋር በተለያዩ ከተሞች ውይይት ያደረገው ጌታቸው ረዳም “እኛ ሥራችንን መሥራት … [Read more...] about ከትሕነግ ጋር ለማበር ወልቃይትን መስዋዕት የሚያደርጉ የ”አማራ ነጻ አውጪዎች”
መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው
አየር ኃይል የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን አስተማማኝና ዘመናዊ አየር ኃይል የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በተለይም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ አየር ኃይሉ በሁሉም ረገድ በመዘመንና ስኬታማ በመሆን ሀገር የምትኮራበት ታላቅ ተቋም መሆኑንም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አሁን ላይ በውጊያ መሠረተ-ልማት፣ በሰው ኃይል ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራና አጠቃቀም በአጭር ጊዜ ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቡን በተቋሙ የተለያዩ ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስተማማኝ የሀገር መከታ በመሆን ለየትኛውም ግዳጅ አፈጻጸም ብቁና ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ዘመናዊ ተቋም የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በአየር ኃይል … [Read more...] about መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው










