• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል

November 27, 2024 12:09 pm by Editor Leave a Comment

* በሶስት ወራት ብቻ ከ6,600 በላይ ወጣቶች በህገ-ወጥ መንገድ ተሰድዋል” – የትግራይ የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ

በትግራይ ክልል ከተሞች በሚገኙ አውራ መንገዶች “ልጄ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ስደት ሲሄድ በአጋቾች ተይዞ ይህንን ብር ክፈል፣ ካልከፈልክ ትገደላለህ ብለውኛል እርዱኝ” የሚሉ በትልቅ ባነር በተቀመጠ የወጣቶች ፎቶ አስደግፈው እርዳታ የሚለሙኑ ወላጆች ተበራክተዋል።

ከነዚሁ ወላጆች የአክሱም ከተማ ነዋሪዋ ወ/ሮ ኣስካለ ውብኣንተ አንድዋ ሲሆኑ፤ ይጦረኛል ብለው ኮስኩሰው አስተምረው ያሳደጉት ወንድ ልጃቸው ህገ-ወጥ ስደት የነጠቃቸው እናት ናቸው።

“ልጄ በጦርነቱ ማግስት በአከባቢው የስራ እድል በማጣቱ በህገ-ወጥ መንገድ የተለያዩ ሃገራት ደንበር አቋርጦ ሊብያ ሲደርስ ለሰው ህይወት ቁብ በሌላቸው ሽፍቶ እጅ ወድቆ ቁም ስቅሉን እያሳዩት ነው” ብለዋል።

“አካል ጉዳተኛ ነኝ፤ ልጄ እኔ እናቱን ለመጦር ዳቦ መጋገሪያ ቤት ከፍቶ የነበረ ቢሆንም ንብረቱ መዘረፉ አናድዶት ነው በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ስደት የሄደው” ወ/ሲሉ እኚሁ እናት እንባ እተናነቃቸው ተናግረዋል።

“ልጄ በአጋቾች ቁጥጥር ስር ውሎ ጥዋት እና ማታ በሚደርስበት ገርፋት እየተሰቃየ ሲያናገርኝ የምይዘው የምጨብጠው ይጠፋብኛል ፤ ‘የጠየቁኝ ብር ካልተከፈለ ኩላሊቴ ያወጡታል ምን ማድረግ ነው ያለብኝ?’ ካለኝ ቀንና ሰዓት ጀምሮ አእምሮየ ልክ አይደለም” ብለዋል።

“ልጄ በመጀመሪያው አከባቢ በሙሉ  ጤንነት እያለ 1.5 ሚሊዮን ብር እንድከፍል ጠየቁኝ  ደጋግመው ደብድበው አካል ጉዳተኛ እና በሽተኛ ካደረጉት በኋላ ግን 300 ሺህ ቀንሰው 1.2 ሚሊዮን ብር ጠይቀውኛል። ይህንን ገቢ ካላደረግኩ ድግሞ እንገድለዋለን ብለውኛል እባካችሁ አርዱኝ” ሲሉ ተማፅነዋል።

ወ/ሮ አስካለ ልጆቻቸው የህገ-ወጥ ስደት ገፋት ቀማሽ ሆኖውባቸው ሌት ተቀን ከሚያለቅሱ በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ እናቶች አንድዋ ናቸው።

እሳቸው ለሚድያ ቃላቸው በሰጡባት ቀን ሰዓትና ደቂቃ ሳይቀር በተለያዩ አቅጣጫዎች በርካታ ወጣቶች በአከባቢያቸው ተስፋ ሰጪ ሁኔታ በማጣት እግራቸው ወደ መራቸው ይሰደዳሉ። 

የትግራይ የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ሓይሽ ስባጋድስ፣ የህገ-ወጥ ስደቱ ዋና መነሻ የሰራ እና መልካም አስተዳደር እጦት መሆኑ ገልጸዋል።

ወጣቶች በነዚህና ሌሎች ችግሮች ተማረው አደገኛ የሆነውን ስደት በመምረጥ ለተለያዩ አደገኛ ነገሮች እየተጋለጡ እንደሆነ አስረድተዋል።

በቢሮቸው የተካሄደው ዳሰሳ እንደሚያመለክተው ከሓምለ 2016 አስከ መስከረም 2017 ዓ.ም ባሉት ሦስት ወራት ብቻ በክልሉ ማእከላዊ ፣ ምስራቅ እና ሰሜናዊ ምዕራብ ከሚገኙ 11 ወረዳዎች ከ6,600 በላይ ወጣቶች በህገ-ወጥ መንገድ ተሰደዋል ሲሉ ገልጸዋል።

“የትግራይ የፓለቲካ አመራሮች ከገቡበት የስልጣን መቆራቆስ በመውጣት በህገ-ወጥ ስደት ለከፍተኛ አደጋ እና እልቀቂት የተጋለጠውን የወጣቱን ክፍል ለመታደግ ቅድሚያ መስጠት አለባቸው” ብለዋል።

የመረጃው ምንጭ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ እና ትግራይ ቴሌቪዥን የህዳር 17/2017 ዓ/ም የዜና ዘገባ ናቸው።@tikvahethiopia

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf, Tigray Mothers, tplf children soldiers, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule