• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ትሕነግ ሕጋዊ ዕውቅና ተሰጥቶት ብልጽግናን ሊቀላቀል ይችላል ተባለ

May 31, 2024 10:16 am by Editor Leave a Comment

ትሕነግ ሌላ ሕንፍሽፍሽ ይጠብቀዋል

በጌታቸው አሰፋ የሚመራው ጽንፈኛ የክልል ፓርቲ ሆኖ ሊቀጥል ይችላል

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ህወሓት መልሶ ሕጋዊ እውቅና እንዲያገኝ የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ ወደ ፓርላማ መራ። ውሳኔው ትሕነግን ሕጋዊ ዕውቅና ሰጥቶ ወደ ብልጽግና ለመቀላቀል የታሰበ ነው የሚል ግምት ሲሰጠው በትሕነግ ውስጥ አንጃ ፈጥረው ፓርቲውን ቀውስ ውስጥ የከተቱት እነ ጌታቸው አሰፋና ሞንጆሪኖ በክልል የተወሰነ ጽንፈኛ ፓርቲ ይዘው ሊቀሩ ይችላሉ እየተባለ ነው።  

የሚኒስትሮች ምክር ቤት “ከሕጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማዕቀፍ ውጪ” ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የፖለቲካ ቡድኖች መልሰው እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ለመመዝገብ የሚያስችላቸውን ድንጋጌ የያዘ የአዋጅ ማሻሻያን ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መራ። የሕጉ ዋና ዓላማ ትሕነግን ወደ ሕይወት ለማምጣት ነው ተብሏል።

በሥራ ላይ ባለው “የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ” ላይ የተደረገው ይህ ማሻሻያ፤ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትሕነግ) የተሰረዘበትን የፓርቲነት ሕጋዊ እውቅና መልሶ እንዳያገኝ ያደረገውን የሕግ ጥያቄ የሚመልስ ነው።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአዋጅ ማሻሻያውን ተቀብሎ ወደ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመራው ዛሬ አርብ ግንቦት 23/2016 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ ያወጣው መረጃ እንደሚያስረዳው ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት በአራት ረቂቅ አዋጆች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ከእነዚህ ረቂቆች መካከል በሕገ ወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አድርጎ ስለማቅረብ እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የቀረበው አዋጅ ይገኝበታል።

በተጨማሪም የንብረት ማስመለስ አዋጅ እና የነዳጅ ውጤቶች የግብይት ሥርዓትን ለመደንገግ የቀረበው አዋጅም ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ ውሳኔ የተሰጠባቸው ሕጎች ናቸው።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፤ በዛሬው ስብሰባ ውሳኔ እንደተላለፈበት በቀዳሚነት የጠቀሰው የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ አዋጅ ነው። ማሻሻያ የቀረበበት በ2012 ዓ.ም. የወጣው የምርጫ ሕግ፤ እውቅና የተነፈጉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን መልሶ ከመመዝገብ ጋር በተያያዘ ክፍተት ያለበት እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ጠቅሷል።

“ከሕጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማዕቀፍ ውጪ የቆዩ የፖለቲካ ቡድኖች በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ፍላጎት በሚያሳዩበት ጊዜ እነዚህን አካላት ሕጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ አድርጎ ለመመዝገብ የሚያስችል ሥርዓት በነባሩ አዋጅ ላይ አልተካተተም” ሲል በሥራ ላይ ያለው አዋጅ ላይ የታየውን ክፍተት ይገልጻል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ የመራው ማሻሻያ ላይ የፖለቲካ ቡድኖች “በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ እና ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ፍላጎት በሚያሳዩበት ጊዜ” መልሰው ለመመዝገብ የሚችሉበትን ሥርዓት የሚዘረጋ እንደሆነም ተጠቅሷል።

ዛሬው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔ ላይ የተጠቀሰው የፖለቲካ ቡድኖች መልሶ የመመዝገብ ጉዳይ ከህወሓት ዳግም ሕጋዊ እውቅና የማግኘት ጉዳይ ጋር በተያያዘ ውዝግብ ፈጥሮ ነበረ ጉዳይ መሆኑ ይታወሳል። (Esat)

ትሕነግ እንደገና ሕይወት እንዲኖረው የሚያደርገው ረቂቅ በብልጽግና ፓርቲ አብላጫ ባለው ፓርላማ እንደሚጸድቅ የሚታመን ነው። ጉዳዩ ከሰሞኑ የአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋ ለታጣቂዎች ካቀረቡት ጥሪ እና የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ ሐመር በአዲስ አበባ ከመክረማቸው ጋር ውሳኔው ይያያዛል የሚሉ ወገኖች መንግሥት ከፍተኛ ጥንቃቄ ካላደረገ የትሕነግ መመለስ ትልቅ የራስ ምታት ሊሆን ይችላል ሲሉ ፍርሃታቸውን ይገልጻሉ። የትሕነግ መመለስ አሜሪካ ጊዜውን ጠብቆ የሚፈነዳ ቦምብ እየቀበረች እንዳይሆን ሲሉም ሥጋታቸውን ያጋራሉ።

ይህንን የሚቃወሙ ግን ትሕነግን ወደ ብልጽግና ለማስገባት የግድ ሕጋዊ ኅልውና ሊሰጠው ይገባል፤ በሕግ የሌለ ፓርቲ በአባልነት ለማስመዝገብ አይቻልም። ስለዚህ ትሕነግን በብልጽግና ውስጥ አስገብቶ ለማሟሟት የግድ ሕጋዊ ሰውነት መስጠት ያስፈልጋል ይላሉ።

ትሕነግ ወደ ብልጽግና ለመግባት እየተደራደረ ነው የሚለው መረጃ ከወጣ ወዲህ ምንም እንኳን የትሕነግ ሰዎች ምንም ዓይነት ድርድር የለም ቢሉም በመሬት ላይ የሚታየው ግን የሚጠቁመው ሌላ ነው። በቅርቡ የብልጽግና ሁለተኛ ሰው አደም ፋራህ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ያካተተ ቡድን ይዘው ወደ መቀሌ በመጓዝ ከትሕነግ ሰዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።

መቀሌ ላይ በአማርኛ በተደረገው ስብሰባ ከብልጽግና የመከላከያ ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ፣ የአማራ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ፣ የአማራ ክልል የቀድሞ የሰላምና የሕዝብ ደኅንነት ቢሮ ኃላፊ የነበሩት ሰማ ጥሩነህ የተገኙ ሲሆን ከትሕነግ በኩል ደግሞ የፓርቲው ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል፣ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበርና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳዳሪ ጌታቸው ረዳ፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሜቴ አባል ፈትለወርቅ ገብረ እግዚአብሔር (በበረኻ ስሟ ሞንጆሪኖ)፣ አብርሃም ተከስተ እና አዲስ ዓለም ባሌማ ናቸው፡፡

ከጥቂት ቀናት በፊት በትሕነግን ውስጥ ስላለው ውጥረት ጥያቄ የተደረገለት ደብረጽዮን ሲመልስ ጌታቸው ረዳ ከሚመራው የሽግግር መስተዳደር ጋር ምንም ችግር የለብንም፤ ዋናው ክፍፍል ያለው በትሕነግ ውስጥ ነው ማለቱ ይታወሳል። ደብረጽዮን እንደሚለው ይህንን መሰል ክፍፍል በትሕነግ ውስጥ ካለ ፓርቲው ለዳግመኛ ሕንፍሽፍሽ የተጋለጠ ይሆናል።

መለስ የሌለበት ሕንፍሽፍሽ ትሕነግን ትንሳኤ ለሌለው ሞት እንደሚዳርገው ይጠበቃል። ሌላው ሞቱን የሚያፋጥነው በብልጽግና ውስጥ መሟሟቱ ሳይሆን ዞሮ ወደ ብልጽግና ለመግባት ያንን ሁሉ ድራማ በመፍጠር ከአንድ ሚሊዮን በላይ የትግራይ ተወላጅ ማስጨፍጭፉ የሚያስነሳውና ምላሽ የሌለው ጥያቄ ይሆናል።

በዚህ ውስጥ ለዘብተኛ የሆነው ዓይኑን በጨው አጥቦ ተገንጥሎ በመውጣት ከብልጽግና ጋር ሊዋኻድ ይችላል። በነ ጌታቸው አሰፋ እና ፈትለወርቅ (ሞንጆሪኖ) የሚመራው ቡድን በማዕከላዊ መንግሥት ላይ አንዳች ሥልጣን የሌለው ጽንፈኛ የክልል ፓርቲ ሆኖ ዕድሜውን ይጨርሳል የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም።

ይህንን የሚኒስትሮች ምክርቤት ውሳኔ ጌታቸው ረዳ በትዊተር ገጹ ከለጠፈ በኋላ ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ አንድ እርምጃ የተራመደ ውሳኔ በማለት አሞግሶታል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule