• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ትሕነግ ሕጋዊ ዕውቅና ተሰጥቶት ብልጽግናን ሊቀላቀል ይችላል ተባለ

May 31, 2024 10:16 am by Editor Leave a Comment

ትሕነግ ሌላ ሕንፍሽፍሽ ይጠብቀዋል

በጌታቸው አሰፋ የሚመራው ጽንፈኛ የክልል ፓርቲ ሆኖ ሊቀጥል ይችላል

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ህወሓት መልሶ ሕጋዊ እውቅና እንዲያገኝ የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ ወደ ፓርላማ መራ። ውሳኔው ትሕነግን ሕጋዊ ዕውቅና ሰጥቶ ወደ ብልጽግና ለመቀላቀል የታሰበ ነው የሚል ግምት ሲሰጠው በትሕነግ ውስጥ አንጃ ፈጥረው ፓርቲውን ቀውስ ውስጥ የከተቱት እነ ጌታቸው አሰፋና ሞንጆሪኖ በክልል የተወሰነ ጽንፈኛ ፓርቲ ይዘው ሊቀሩ ይችላሉ እየተባለ ነው።  

የሚኒስትሮች ምክር ቤት “ከሕጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማዕቀፍ ውጪ” ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የፖለቲካ ቡድኖች መልሰው እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ለመመዝገብ የሚያስችላቸውን ድንጋጌ የያዘ የአዋጅ ማሻሻያን ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መራ። የሕጉ ዋና ዓላማ ትሕነግን ወደ ሕይወት ለማምጣት ነው ተብሏል።

በሥራ ላይ ባለው “የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ” ላይ የተደረገው ይህ ማሻሻያ፤ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትሕነግ) የተሰረዘበትን የፓርቲነት ሕጋዊ እውቅና መልሶ እንዳያገኝ ያደረገውን የሕግ ጥያቄ የሚመልስ ነው።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአዋጅ ማሻሻያውን ተቀብሎ ወደ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመራው ዛሬ አርብ ግንቦት 23/2016 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ ያወጣው መረጃ እንደሚያስረዳው ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት በአራት ረቂቅ አዋጆች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ከእነዚህ ረቂቆች መካከል በሕገ ወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አድርጎ ስለማቅረብ እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የቀረበው አዋጅ ይገኝበታል።

በተጨማሪም የንብረት ማስመለስ አዋጅ እና የነዳጅ ውጤቶች የግብይት ሥርዓትን ለመደንገግ የቀረበው አዋጅም ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ ውሳኔ የተሰጠባቸው ሕጎች ናቸው።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፤ በዛሬው ስብሰባ ውሳኔ እንደተላለፈበት በቀዳሚነት የጠቀሰው የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ አዋጅ ነው። ማሻሻያ የቀረበበት በ2012 ዓ.ም. የወጣው የምርጫ ሕግ፤ እውቅና የተነፈጉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን መልሶ ከመመዝገብ ጋር በተያያዘ ክፍተት ያለበት እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ጠቅሷል።

“ከሕጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማዕቀፍ ውጪ የቆዩ የፖለቲካ ቡድኖች በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ፍላጎት በሚያሳዩበት ጊዜ እነዚህን አካላት ሕጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ አድርጎ ለመመዝገብ የሚያስችል ሥርዓት በነባሩ አዋጅ ላይ አልተካተተም” ሲል በሥራ ላይ ያለው አዋጅ ላይ የታየውን ክፍተት ይገልጻል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ የመራው ማሻሻያ ላይ የፖለቲካ ቡድኖች “በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ እና ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ፍላጎት በሚያሳዩበት ጊዜ” መልሰው ለመመዝገብ የሚችሉበትን ሥርዓት የሚዘረጋ እንደሆነም ተጠቅሷል።

ዛሬው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔ ላይ የተጠቀሰው የፖለቲካ ቡድኖች መልሶ የመመዝገብ ጉዳይ ከህወሓት ዳግም ሕጋዊ እውቅና የማግኘት ጉዳይ ጋር በተያያዘ ውዝግብ ፈጥሮ ነበረ ጉዳይ መሆኑ ይታወሳል። (Esat)

ትሕነግ እንደገና ሕይወት እንዲኖረው የሚያደርገው ረቂቅ በብልጽግና ፓርቲ አብላጫ ባለው ፓርላማ እንደሚጸድቅ የሚታመን ነው። ጉዳዩ ከሰሞኑ የአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋ ለታጣቂዎች ካቀረቡት ጥሪ እና የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ ሐመር በአዲስ አበባ ከመክረማቸው ጋር ውሳኔው ይያያዛል የሚሉ ወገኖች መንግሥት ከፍተኛ ጥንቃቄ ካላደረገ የትሕነግ መመለስ ትልቅ የራስ ምታት ሊሆን ይችላል ሲሉ ፍርሃታቸውን ይገልጻሉ። የትሕነግ መመለስ አሜሪካ ጊዜውን ጠብቆ የሚፈነዳ ቦምብ እየቀበረች እንዳይሆን ሲሉም ሥጋታቸውን ያጋራሉ።

ይህንን የሚቃወሙ ግን ትሕነግን ወደ ብልጽግና ለማስገባት የግድ ሕጋዊ ኅልውና ሊሰጠው ይገባል፤ በሕግ የሌለ ፓርቲ በአባልነት ለማስመዝገብ አይቻልም። ስለዚህ ትሕነግን በብልጽግና ውስጥ አስገብቶ ለማሟሟት የግድ ሕጋዊ ሰውነት መስጠት ያስፈልጋል ይላሉ።

ትሕነግ ወደ ብልጽግና ለመግባት እየተደራደረ ነው የሚለው መረጃ ከወጣ ወዲህ ምንም እንኳን የትሕነግ ሰዎች ምንም ዓይነት ድርድር የለም ቢሉም በመሬት ላይ የሚታየው ግን የሚጠቁመው ሌላ ነው። በቅርቡ የብልጽግና ሁለተኛ ሰው አደም ፋራህ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ያካተተ ቡድን ይዘው ወደ መቀሌ በመጓዝ ከትሕነግ ሰዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።

መቀሌ ላይ በአማርኛ በተደረገው ስብሰባ ከብልጽግና የመከላከያ ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ፣ የአማራ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ፣ የአማራ ክልል የቀድሞ የሰላምና የሕዝብ ደኅንነት ቢሮ ኃላፊ የነበሩት ሰማ ጥሩነህ የተገኙ ሲሆን ከትሕነግ በኩል ደግሞ የፓርቲው ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል፣ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበርና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳዳሪ ጌታቸው ረዳ፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሜቴ አባል ፈትለወርቅ ገብረ እግዚአብሔር (በበረኻ ስሟ ሞንጆሪኖ)፣ አብርሃም ተከስተ እና አዲስ ዓለም ባሌማ ናቸው፡፡

ከጥቂት ቀናት በፊት በትሕነግን ውስጥ ስላለው ውጥረት ጥያቄ የተደረገለት ደብረጽዮን ሲመልስ ጌታቸው ረዳ ከሚመራው የሽግግር መስተዳደር ጋር ምንም ችግር የለብንም፤ ዋናው ክፍፍል ያለው በትሕነግ ውስጥ ነው ማለቱ ይታወሳል። ደብረጽዮን እንደሚለው ይህንን መሰል ክፍፍል በትሕነግ ውስጥ ካለ ፓርቲው ለዳግመኛ ሕንፍሽፍሽ የተጋለጠ ይሆናል።

መለስ የሌለበት ሕንፍሽፍሽ ትሕነግን ትንሳኤ ለሌለው ሞት እንደሚዳርገው ይጠበቃል። ሌላው ሞቱን የሚያፋጥነው በብልጽግና ውስጥ መሟሟቱ ሳይሆን ዞሮ ወደ ብልጽግና ለመግባት ያንን ሁሉ ድራማ በመፍጠር ከአንድ ሚሊዮን በላይ የትግራይ ተወላጅ ማስጨፍጭፉ የሚያስነሳውና ምላሽ የሌለው ጥያቄ ይሆናል።

በዚህ ውስጥ ለዘብተኛ የሆነው ዓይኑን በጨው አጥቦ ተገንጥሎ በመውጣት ከብልጽግና ጋር ሊዋኻድ ይችላል። በነ ጌታቸው አሰፋ እና ፈትለወርቅ (ሞንጆሪኖ) የሚመራው ቡድን በማዕከላዊ መንግሥት ላይ አንዳች ሥልጣን የሌለው ጽንፈኛ የክልል ፓርቲ ሆኖ ዕድሜውን ይጨርሳል የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም።

ይህንን የሚኒስትሮች ምክርቤት ውሳኔ ጌታቸው ረዳ በትዊተር ገጹ ከለጠፈ በኋላ ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ አንድ እርምጃ የተራመደ ውሳኔ በማለት አሞግሶታል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule