ይህ ኃይል አስተሳሰቡም ተግባሩም ሠይጣናዊ ነው፤ የሠይጣን ቁራጭ ነውወያኔ ይዋሻል፤ የውሸት አባት ደግሞ ሠይጣን ነውየኢትዮጵያ ሕዝብ እንኳን ድጋሚ ወያኔን የበላይነት ቢቀበል እግዚአብሔር አይቀበለውምኢትዮጵያዊ ውስጥ ወያኔን የሚወጋው ሰው እንኳን ባይኖር ንፋስ ይጥለዋልወያኔ ውሸት ላይ ስለቆመ ከእንግዲህ ኃይል ሆኖ አይቆምም ሕዝቡ በየአካባቢው በውስጡ ተሰግስገው ያሉት የአሸባሪው ሕወሓት ተላላኪዎችንና የሸኔ ጉዳይ አስፈፃሚዎችን መታገልና ከውስጡ መንጥሮ ማውጣት እንዳለበት የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ አሳሰቡ። አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ አሸባሪው ትሕነግ ለኢትዮጵያ ጠላት ሆኖ የተፈጠረ ኃይል ነው። ይህ የአገር ጠላት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስወገድ የኢትዮጵያ ሕዝብ … [Read more...] about “ወያኔ የመርገም ውጤት ነው” አቶ ሽመልስ
tplf terrorist
በደሴ የወንበዴው ክፍለ ጦር አዛዥ ጉዕሽ ገብሩ በቁጥጥር ሥር ውሏል
አሸባሪው የትህነግ ቡድን አገር የማፍረስ እቅዱን ለማሳካት በርካታ እኩይ ተግባራትን እየፈፀመ እንደሚገኝ በደሴ ግንባር የተማረከው የሽብር ቡድኑ ሜይዴይ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ጉዕሽ ገብረ ተናገረ። የሽብር ቡድኑ በርካታ ህፃናትና ሽማግሌዎችን ያለ ትጥቅ በማሰለፍም ለአላስፈላጊ መስዋዕትነት እየዳረጋቸው እንደሚገኝም ምርኮኛው ተናግሯል። አሸባሪው ትህነግ አገር የማፍረስ እቅድ ነድፎ መንቀሳቀስ ከጀመረ ድፍን አንድ አመት ተቆጥሯል። ቡድኑ በጥቅምት ወር 2013 ዓ.ም በሰሜን እዝ ላይ ያሰበው እቅድ እንዳሰበው አልሆን ሲለው የትግራይን ህዝብ በሀሰት ፕሮፓጋንዳ በማሰባሰብ ለዳግም የክህደት ተግባር በተለያዩ ግንባሮች ጦርነት ከፍቶ ይገኛል። የሽብር ቡድኑ ሰሞኑን እጅግ በርካታ ቁጥር ያለው የሰው ሃይል በማሰለፍ በደሴ ግንባር ውግያ ቢከፍትም በርካታ ሰብዓዊና ቁሳዊ … [Read more...] about በደሴ የወንበዴው ክፍለ ጦር አዛዥ ጉዕሽ ገብሩ በቁጥጥር ሥር ውሏል
“በሀገር ጉዳይ ቀልድ የለም፤ በነጭ ፕሮፖጋንዳ ሀገርን በማፍረስ ተግባር የተጠመዱ” ላይ መንግሥት የማያዳግም ርምጃ ይወስዳል
በነጭ ፕሮፖጋንዳ ሀገርን በማፍረስ ተግባር የተጠመዱ ወገኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ መንግስት አሳሰበ፡፡ በነጭ ፕሮፖጋንዳ ሀገርን በማፍረስ ተግባር የተጠመዱ ወገኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አሳሰበ፡፡ በሀገር ጉዳይ ቀልድ የለም ያለው አገልግሎቱ ከዚህ ድርጊታቸው በማይቆጠቡት ላይ መንግስት የማያዳግም ርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል፡፡ መላው ህዝብ ኢትዮጵያን የማዳን የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ የሚገኝ መሆኑን ተገንዝቦ የጀመረውን ሀገር የማዳን ንቅናቄ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስቧል፡፡ "ዋስትናችን ህልውናችንን በአንድነት ማረጋገጥ መሆኑን በመረዳት" በአፍራሽ ኃይሎችና ግብረ አበሮቻቸው በኩል የሚነዙ መርዛማ ወሬዎች የሚመጡበትን መንገድ መዝጋት እንደሚገባም ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያውያንና የወዳጅ ሀገራት ሚዲያዎች ለህብረተሰቡ ትክክለኛውን … [Read more...] about “በሀገር ጉዳይ ቀልድ የለም፤ በነጭ ፕሮፖጋንዳ ሀገርን በማፍረስ ተግባር የተጠመዱ” ላይ መንግሥት የማያዳግም ርምጃ ይወስዳል
“የመከላከያ ጥምር ኃይልና ህዝቡ አሸባሪውን ቡድን እንደ እግር እሳት እየፈጁት ነው”
የመከላከያ ጥምር ሀይልና ህዝቡ አሸባሪው ቡድን ሰርጎ በገባባቸው አካባቢዎች እንደ እግር እሳት እየፈጀው እንደሚገኝ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። የፌዴራል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ የሽብር ቡድኑ ለከፈተው አገርን የማፍረስ ጦርነት ለመመከት ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በርካታ ቁጥር ያለው ህዝብ በከፍተኛ ቁጭትና ወኔ ወደ ግምባር እየዘመቱ ይገኛሉ ብለዋል። የመከላከያ ጥምር ሀይልና ህዝቡ አሸባሪው ቡድን ሰርጎ በገባባቸው አካባቢዎች እንደ እግር እሳት እየፈጀው እንደሚገኝም ገልጸዋል። አሸባሪው ቡድን ሰርጎ ቢገባም አይወጣም ያሉ የደሴ ወጣቶች "እንደገና" ብለው በመደራጀት አሸባሪውን እየቀጡትና አካባቢያቸውንም በንቃት እየጠበቁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። (ኢፕድ) ከዚሁ ጋር … [Read more...] about “የመከላከያ ጥምር ኃይልና ህዝቡ አሸባሪውን ቡድን እንደ እግር እሳት እየፈጁት ነው”
በቤኒሻንጉል ከትህነግና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከአሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አብዱልአዚም መሐመድ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመውጣቱ አስቀድሞ የክልሉ ፖሊስ የተጠናከር የክትትል ስራ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ኮሚሽነሩ እንዳሉት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 23 ቀን 2014 ዓ.ም ወጥቶ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የጸደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የክልሉን ሠላም ለማስጠበቅ ለፀጥታ አስከባሪ ኃይሉ ተጨማሪ አቅም ሆኖታል። ግለሰቦቹ በሕግ ቁጥጥር ስር የዋሉት ከአሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደነበራቸው ፖሊስ በደረሰው መረጃ መሰረት ከጥቅምት 21 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ባደረገው ኦፕሬሽን ነው ብለዋል፡፡ አሸባሪው … [Read more...] about በቤኒሻንጉል ከትህነግና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
“የዛሬዋ ኢትዮጵያ አይደለም የትላንትናውን ትህነግ የዘመነውን ትህነግ ለመቀበል አትችልም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
* "በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ተሳትፈዋል" * የ፷፪ ዓመት ሽማግሌ ከትግራይ ለትህነግ ዘምቷል በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ከአሸባሪው ቡድን ጋር መሳተፋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በጦርነቱ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ እና የኢትዮጵያውያ ዝርያ የሌላቸው ነጮች እና ጥቁሮች ከአሸባሪው ቡድን ጋር ተሳትፈው መስዋትነት መክፈላቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያረጋገጡት። “በወሎ ግምባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ተሳትፈውበታል። የኢትዮጵያ ዝርያ የሌላቸው ሰዎች ተሳትፈው መስዋዕትነት ከፍለዋል። ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ሰው ኢትዮጵያ መጥቶ በደሴ … [Read more...] about “የዛሬዋ ኢትዮጵያ አይደለም የትላንትናውን ትህነግ የዘመነውን ትህነግ ለመቀበል አትችልም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ደሴ በወገን እጅ – መከላከያ እየገፋ ነው!
ደሴን ለመውረር አሰፍስፎ የነበረ አሸባሪው የህወሃት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷልበወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብቶ የነበረ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂም ባለበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው ተሸኝቷልየደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለሙ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት አልተረዱም ልዩ መረጃ፤ ከጥቂት ደቂዎች በፊት ጎልጉል እንዳረጋገጠው ደሴን ያረጋጋው መከላከያ ሠራዊት፣ ልዩ ኃይል፣ ሕዝባዊ ሚሊሻና ፋኖ በርካታ አካባቢዎችን እየተቆጣጠረና በወገን እጅ ሥር እያደረጋቸው ይገኛል። በዚህም ጠላት በከፍተኛ ሁኔታ እየተደመሰሰና እየሸሸ እንደሆነ ለማረጋገጥ ችለናል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ላለቁት ልጆቹ ትህነግን ለመጠየቅ እንዲዘጋጅ … [Read more...] about ደሴ በወገን እጅ – መከላከያ እየገፋ ነው!
ስድስተኛው የአየር ጥቃት ተደርጓል፤ አየር ኃይሉ ብቃቱን አስመስክሯል
ዛሬ መቀሌ ኵሃ አካባቢ የሚገኘው የልዩ ኃይል ፖሊስ ማሠልጠኛ ተቋም በአየር ኃይል ተመቷል። ይህ ተቋም በአሁኑ ወቅት በርካታ የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች እየሰለጠኑበት ያለ ተቋም መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል። በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ የተጠኑና ወራሪው ሽብርተኛው ህወሓት ወያኔ መሳሪያ በማከማቸት የጦር ስልጠና የሚሰጥበት ቦታ ላይ የኢትዮጵያ አየር ሀይል ለ6 ተኛ ዙር ዛሬ የአየር ጥቃት አድርሷል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባደረጋቸው የአየር ጥቃቶች ኢላማውን አግኝቶ መምታቱና የጠላትን ወታደራዊ ይዞታዎችን ለይቶ ከጥቅም ውጪ ማድረጉ ስኬታማነቱንና በቂ ሥልጠና እንዳለው እንደሚያሳይ የቀድሞ ሠራዊት አባል ብርጋዴር ጀነራል መስፍን ኃይሌ ገለጹ። ብርጋዴር ጀነራል መስፍን በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አየር … [Read more...] about ስድስተኛው የአየር ጥቃት ተደርጓል፤ አየር ኃይሉ ብቃቱን አስመስክሯል
ለሸኔ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ ተያዙ
የሽብር ተግባር ለመፈጸምና የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ የሸኔ ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ለኢቢሲ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፣ ሽብርተኛው ሸኔ በንፁሃን ዜጎች እና በፀጥታ አካላት ላይ ግድያ እንዲፈፅሙ መልምሎ እና ስልጠና ሰጥቶ ለጥፋት ተልዕኮ ካሰማራቸው ግለሰቦች መካከል በስሩ 5 የገዳይ ቡድን አባላትን በማደራጀት በህቡዕ ሲንቀሳቀሰ የነበረው ጃፋር መሐመድ ሳኒ የተባለው ተጠርጣሪ በተደረገበት ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ይህ የሸኔ ታጣቂ በቁጥጥር ስር የዋለው በስሩ ካደራጃቸው 5 ግብረ አበሮቹ ጋር በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ኦዳ ቡልቱም ወረዳ ሚደግዱ ቀበሌ እና ቦረማ ጫካ እንዲሁም ዳሮ ለቡ ወረዳ ሚጨታ እና በዴሳ ከተማ ውስጥ በንፁሃን ዜጎች እና በመንግሥት ፀጥታ … [Read more...] about ለሸኔ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ ተያዙ
የመቀሌ አየር ድብደባዎች ዒላማቸውን የመቱ ናቸው
የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸው የአየር ድብደባዎች ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎች ላይ ብቻ እንደሆነና ኢላማቸውን የመቱ መሆናቸው ተገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ ገጽ ባወጣው መግለጫ፤ የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸውን የአየር ድብደባዎች በተመለከተ የተዛባ ግንዛቤ ቢኖርም፣ በተቃራኒው ጥቃቶቹ ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎችን ብቻ ነው ብሏል። የመከላከያ ሠራዊት የሚያከውናቸው እነዚህ ሥራዎች የሽብር ድርጅቱ ከባድ የጦር መሣሪያዎችን እና ሌሎች ሕገወጥ የጦር መሣሪያዎችን ለመሸሸግ የሚጠቀምባቸውን እና ወደ ወታደራዊ መገልገያነት የቀየራቸውን የተወሰኑ ቦታዎች ከጥቅም ውጭ ለማድረግ ያለመ ነው ሲልም አስታውቋል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about የመቀሌ አየር ድብደባዎች ዒላማቸውን የመቱ ናቸው