አሸባሪው ህወሓት በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የዛሪማ መስጊድን በከባድ መሳሪያ ደብድቦ ማውደሙን የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት አረጋ ገጠ። አሸባሪ ቡድኑ የፈጸመው ድርጊትም የሰዎችን እምነት የሚጋፋ መሆኑን ምክር ቤቱ ገልጿል። የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ ሀጂ ሙሀመድ ሀሰን፣ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፣ በሰሜን ጎንደር ውስጥ በሚገኘውና በቅርብ በተገነባው የዛሪማ መስጊድ ላይ በከባድ መሳሪያ ተኩሶ መስጊዱን በከፊል አውድሟል። በአካባቢው አሸባሪው ቡድን ሸሽቶ ጫካ በመግባቱና ደብቆ ባከማቸው የከባድ መሳሪያ ከርቀት በማስወንጨፍ በዛሪማ መስጊድና በአካባቢው በሚገኙ ቤተ-እምነቶችና ንፁሀን ላይ ጉዳት እያደረሰ እንዳለ ገልጸዋል። አሸባሪ ቡድኑ የፈጸመው ተግባርም ለእምነት ክብር እንደማይሰጥ አንዱ ማሳያ መሆኑንም … [Read more...] about ትህነግ የዛሪማን መስጊድ አወደመ
tplf terrorist
በወለጋ የሰፈሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ትህነጎችና የሸኔ ግፍ
በምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ሀሮ ከተማ ፅንፈኛው የአሸባሪ ቡድን ሸኔ ጥቅምት 1 እና 2 በንፁሃን ላይ በከፈተው ጥቃት በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል። ቡድኑ ከህውሃት የሽብረ ቡድን ጋር ህብረቱን ካረጋገጠ በኋላ በብሄር ብሄረሰቦች ላይ ትንኮሳ በማድረግ ግጭቶችም የብሄር መልክ እንዲይዙ እየሰራ ይገኛል ብለዋል የቢሮው ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ። ኃላፊው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት ሸኔ በአካባቢው ከሚንቀሳቀስ ሌላ የሽፍታ ቡድን ጋር በመተባበር በሀሮ ከተማ በከፈተው ጥቃት የ15 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ የንብረት ውድመት እንዳደረሰ እንዲሁም 967 አባወራዎች ከቤት ንብረታቸው እንደተፈናቀሉ ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት ተጨማሪ የፀጥታ ሀይል ወደ ስፍራው በማሰማራት ወረዳውን እና ከተማውን … [Read more...] about በወለጋ የሰፈሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ትህነጎችና የሸኔ ግፍ
እያፈገፈገ ያለውን ሽፍታ የሚመራው ፃድቃን ጦርነቱ “በቀናት፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ይጠናቀቃል” አለ
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር / ትህነግ አማጺ ሃይል መሪ የሆነው ጻድቃን ገብረትንሳይ ጦርነቱ እንደማይራዘም አመለከተ። አዲስ ተጀመረ የተባለውን ጦርነት “የቀናት ጉዳይ ነው፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ውስጥ ይጠናቀቃል” ሲል የተናገረው ለኒውዮርክ ታይምስ ነው። የትግራይ ሕዝብ የዕድሜ ልክ ጠላት ሲሉ የጠራቸው ኢሳያስ መወገድ እንዳለባቸው ለዓለም ማህበረሰብ አስታውቋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እስካሁን ማጥቃት አለመጀመሩን፣ ነገር ግን ዝግጅቱን አጠናቆ መመሪያ እየጠበቀ መሆኑንና ማጥቃት ከጀመረ “ድረሱልኝ” የሚል ጊዜ የሚሰጥ እንዳልሆነ ከዚህ በፊት ሲነገር ነበር። ትህነግ ያወጣውን የድረሱልኝ ጥሪ ተከትሎ መከላከያ ይህንን ቢልም የተለያዩ ሃላፊዎችና ዓለም ዓቀፍ ሚዲያዎች ደጋግመው ጥቃት መጀመሩን እያስታወቁ ነው። የአየር ሃይል አዛዥም በባንዲራ ቀን አየር ኃይል “ጠላትን … [Read more...] about እያፈገፈገ ያለውን ሽፍታ የሚመራው ፃድቃን ጦርነቱ “በቀናት፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ይጠናቀቃል” አለ
የተመድ የሥልጣን ሽኩቻና የኃላፊዎች መጠራት
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከትግራይ ጦርነት ጋር በተያያዘ ያልተገባ አስተያየት ሰጥተዋል ያላቸውን ሁለተኛዋን የተመድ የኢትዮጵያ ኃላፊን ጠርቷል። ተመድ የጠራቸው የድርጅቱ ሥነ ሕዝብ ጽ/ቤት (ዩኤንኤፍፒኤ) የኢትዮጵያ ኃላፊ ዴኒያ ጌይል መሆናቸውን ኤኤፍፒን ጠቅሶ ቢቢሲ ዘግቧል። ቀደም ሲል የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) የኢትዮጵያ ኃላፊ ማውሪን አቻንግ "የድርጅቱን እሴቶች የማያንጸባርቅ" አስተያየት በመስጠታቸው ምክንያት አስተዳደራዊ እረፍት እንዲወስዱ መደረጉን ተቋሙ ገልጾ ነበር። መንግሥታቱ ድርጅት የሥነ ሕዝብ እና የስደተኞች ጉዳይ ኃላፊዎች ለትግራይ ኃይሎች ርኅራኄ አላቸው ባሏቸው የተባበሩት መንግሥታት ከፍተኛ አመራሮች ወደ ጎን ገሸሽ ተደርገናል ማለታቸው ተዘግቧል። ሁለቱ በኢትዮጵያ የተመድ ከፍተኛ ኃላፊዎች የፌዴራሉ መንግሥት በትግራይ ላይ … [Read more...] about የተመድ የሥልጣን ሽኩቻና የኃላፊዎች መጠራት
የኢትዮጵያ መንግሥት ምንም አይነት ማብራሪያ እና ማረጋገጫ የማቅረብ ግዴታ የለበትም!
ትላንት ማክሰኞ መስከረም 26 የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ስብሰባ ሲቀመጥ 2 ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ይኸኛው ለ4ኛ ጊዜ (በዝግ እና በክፍት) ነው። ይኸኛው ስብሰባው ለምን ተጠራ? - ኢትዮጵያ 7 የተመድ ሰራተኞችን ከሀገር በማስወጣቷ። - የሰሜን ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ሁኔታ ላይ ለመወያየት። ስብሰባው እንዲካሄድ የጠየቁት፦ አሜሪካ፣ ዩኬ፣ ኖርዌይ፣ ኢስቶኒያ፣ ፈረንሳይ እና አየርላንድ ናቸው። በስብሰባው ላይ የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ንግግር አድርገዋል። የምክር ቤቱ አባል ሀገራት የተለያዩ ሀሳቦችን ሰንዝረዋል። ሙሉ ውይይቱን (ክፍት ውይይት ስለሆነ) በተመድ የዩትዩብ ቻናል መከታተል እንደምትችሉ እየጠቆምን የተነሱ ዋና ሃሳቦችን ግን በአጭሩ … [Read more...] about የኢትዮጵያ መንግሥት ምንም አይነት ማብራሪያ እና ማረጋገጫ የማቅረብ ግዴታ የለበትም!
34 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ
34 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር አዉሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። ተጠርጣሪው ግለሰብ በጥቁር ፌስታል የተጠቀለለ ነገር ይዞ ሲንቀሳቀስ መደበኛ የወንጀል መከላከል ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተነስቷል፡፡ ፖሊሶቹ ባደረባቸው ጥርጣሬ ግለሰቡን ሲፈትሹት 34 ሺህ የአሜርካ ዶላር ይዞ በህገ ወጥ መንገድ ሲያዘዋውር በመገኘቱ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት ነው ተብሏል፡፡ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በአዲስ አበባ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሲሆን የኑሮ ውድነት እንዲባባስ እና መንግስት ማግኘት ያለበትን ገቢ እንዲያጣ እያደረገ ይገኛል፡፡ ወንጀል ፈፃሚዎች እና ህገ-ወጥ ተግባራት ላይ የሚሳተፉ አካላት የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ህግን በጣሰ መልኩ እየተንቀሳቀሱ … [Read more...] about 34 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ
በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ማን እንደሚገባ፣ እንደሚወጣና እንደሚቆይ ለማንም ማሳወቅ አይጠበቅብንም
አንድ ሀገር በግዛቷ ውስጥ ማን እንደሚገባ፣ እንደሚወጣና እንደሚቆይ የመወሰን መብቷ የተጠበቀ ነው፤ የኢትዮጵያ መንግስትም ይህንን ውሳኔውን ለማንም ማሳወቅ አይጠበቅበትም ሲሉ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ። አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮጵያ ከተልዕኳቸው ውጪ ሲንቀሳቀሱ ከአገር እንዲወጡ የተደረጉ የተመድ ሰራተኞችን በተመለከተ ለጸጥታው ምክር ቤት ማብራሪያ ሰጥተዋል። አምባሳደሩ በሰጡት ማብራርያ “የዛሬው ስብሰባ መነሻ ምክንያት የአንድን ሉዓላዊት ሀገር ውሳኔ የሚጋፋ የመወያያ አጀንዳ መፍጠሩ ተገቢ ካለመሆኑ በላይ ራስን በራስ በማስተዳደር በተወሰነ ውሳኔ ላይ እንዲሁም በሉዐላዊት አገር ጉዳይ ጣልቃ መግባት ነው” ብለዋል። በዓለም አቀፍ ህጎች መነሻነት ኢትዮጵያ ውሳኔውን መወሰኗንም አስታውቀዋል። የተለያዩ አገራት በተለያየ … [Read more...] about በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ማን እንደሚገባ፣ እንደሚወጣና እንደሚቆይ ለማንም ማሳወቅ አይጠበቅብንም
በአዲስ አበባ ሕገወጥ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ፍተሻ የተለያዩ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያዎች እና ሰነዶች በቁጥጥር ስር ዋሉ። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው 32 ቀበሌ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውሰጥ ከፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት በተደረገ ፍተሻ የጦር መሳሪያዎች እና ሰነዶች መገኘታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። በግለሰቡ መኖሪያ ቤት ላይ ጥናት በማድረግና የፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት በተደረገ ብርበራ 85 የክላሽን-ኮቭ እና የሽጉጥ ጥይቶች፣ 3 ሽጉጦች ፣ 2 ሳንጃዎች እና 1 የእጅ ቦንብ መያዙን ነው ፖሊስ የገለፀው፡፡ በተጨማሪም 10 ሺህ የኢትዮጵያ ብር እና በርካታ ፓስፖርቶችን ጨምሮ የትምህርት ማስረጃዎች በግለሰቡ መኖሪያ ቤት ውስጥ መገኘታቸውን ከአዲስ ከተማ ክፍለ … [Read more...] about በአዲስ አበባ ሕገወጥ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ
በልዩ ልዩ መንገድ ለትህነግ ሢሠሩ የነበሩ ፯ የተመድ ኃላፊዎች ተባረሩ
የኢትዮጵያ መንግሥት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስር በተለያዩ ኤጀንሲዎች ውስጥ የሚሰሩ 7 የውጭ አገር ዜጎች በ72 ሰዓት ውስጥ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡ ትእዛዝ ማስተላለፉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢቲቪ በላከው መረጃ እንዳስታወቀው የኢትዮጵያን ድንበር ለቀው እንዲወጡ የታዘዙት የመንግሥታቱ ድርጅት ባልደረቦች በአገር ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ህገ ወጥ ሥራ ሲሠሩ የተገኙ መሆናቸውም ነው የተገለፀው።የኢትዮጵያን ድንበር ለቀው እንዲወጡ የታዘዙት የውጭ አገር ዜጎች የዩኒሴፍ የኢትዮጵያ ተወካይ የዩኒሴፍ ሃላፊ አዴል ኮርድ፣ የተራድኦ ምክትል አስተባባሪ ግራንት ሊያቲ፣ የተራድኦ ምክትል አስተባባሪ ተወካይ ጋዳ ኤልታሂር ሙዳዊ፣ የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ምክትል አስተባባሪ ሰኢድ መሀመድ ሀርሲ፣ ሶኒ ኦኔግቡላ የስብዓዊ መብቶች … [Read more...] about በልዩ ልዩ መንገድ ለትህነግ ሢሠሩ የነበሩ ፯ የተመድ ኃላፊዎች ተባረሩ
ኢትዮጵያን ለማፍረስ መስከረም 2013 በትህነግ የተዘጋጀው ሰነድ
“የትግል ልዩ ምዕራፍ እድገቶች እና የምከታችን ቀጣይ ስትራቴጂዎች፣ ስልቶች እና አቅጣጫዎች” በሚል ርዕስ ኢትዮጵያን በረቀቀ ስልት ለማፈራረስ ካልተቻለም የትህነግን ጡንቻ በማሳበጥ የመደራደር ዐቅሙን ለማጎልበት እንዲረዳ የወጣ ባለ 86 ገጽ ሰነድ እዚህ ላይ ይገኛል። “የትግል ልዩ ምዕራፍ እድገቶች እና የምከታችን ቀጣይ ስትራቴጂዎች፣ ስልቶች እና አቅጣጫዎች” Download ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ኢትዮጵያን ለማፍረስ መስከረም 2013 በትህነግ የተዘጋጀው ሰነድ