የክስ ማንሳት የፍሬ ነገር ይዘትና ስነ ሥርዓት በወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 122 ስር በአምስት ንዑስ አንቀጾች ተጠቃሎ ይገኛል፡፡ በይዘቱም፡- • ከከባድ የሰው ግድያ እና ከከባድ ውንብድና ወንጀሎች ውጭ ዐ/ሕግ ከፍርድ በፊት ክስ ማንሳት ይችላል፡፡ • ክስ የሚነሳው በዐ/ህጉ ጥያቄ ወይም በሌላ የመንግስት አካል ትዕዛዝ ሊሆን ይችላል፡፡ • ክሱ የሚነሳው በፍ/ቤት ፈቃድ ሲሆን ፍ/ቤቱ ለመከልከልም ሆነ በመፍቀድ ምክንያቱን ማስቀመጥ አለበት፡፡ • በወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 113 መሰረት አዲስ ክስ ካልቀረበ ተከሳሹ ለግዜው ይለቀቃል፡፡ • የክሱ መነሳት ዐ/ሕግ ክስን ከማንቀሳቀስ አያግደውም፡፡ የሚል ሀሳብ ያለው ነው፡፡ የፍትሕና የሕግ ሥርዓት ምርምር ኢንስቲቲዩት ባዘጋጀው ረቂቅ የወንጀል ስነ-ሥርዓት ሕግ አንቀጽ 119 ስር ዐ/ሕግ ከፍርድ ቤት በማንኛውም ጊዜ ክስ … [Read more...] about የወንጀል ክስ ማንሳት እና ማስቀጠል የሚቻለዉ መቼ ነዉ?
tplf terrorist
አሸባሪው የትግሬ ቡድን ያደረሰው ውድመት በሳይንሳዊ መልኩ እየተጠና ነው
የአማራ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ እየተካሄደ የሚገኘውን ጥናት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የአማራ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኀላፊ አንሙት በለጠ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በአማራ ክልል መጠነ ሠፊ የሰብዓዊ ጥሰት፣ የንብረት ዘረፋና ውድመት ፈጽሟል ብለዋል። በሽብር ቡድኑ ምክንያት የደረሰውን አጠቃላይ ውድመት ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ እየተጠና እንደሆነ አቶ አንሙት አስረድተዋል። በጥናቱ መሠረት ትክክለኛ ውድመቱ እንደሚገለጽ ነው የተናገሩት። ጥናቱ በጎደለው ልክ ለመሙላት አጋዥ እንደሚሆንም ጠቁመዋል። ከጥናቱ በኋላ የወደሙ መሰረተ ልማቶች ተመልሰው በሚገነቡበት ሁኔታ ላይም ስትራቴጂክ እቅድ እየተዘጋጀ እንደሆነ አመላክተዋል። አቶ አንሙት እንደተናገሩት የጥናቱ ዓላማ ቡድኑ ያደረሰውን ውድመት ትክክለኛ መረጃን መስጠትና በሰነድ ማስቀመጥ፣ የሽብር ቡድኑ ተጠያቂ … [Read more...] about አሸባሪው የትግሬ ቡድን ያደረሰው ውድመት በሳይንሳዊ መልኩ እየተጠና ነው
ሸዋሮቢት ከተማ በአሸባሪው ትህነግ ታጣቂዎች በቡድን የተደፈሩት እናት ራሳቸውን አጠፉ!
"መግደልም መድፈርም መብታችን ነው" – “ተገድደነው የዘመትነው” የሚሉት የትህነግ ታጣቂዎች ዕድሜያቸው 50ዎቹን ያለፈው የሸዋሮቢት ከተማ ነዋሪዋ አዛውንት በአሸባሪው የህወሓት ታጣቂዎች በቡድን ከተደፈሩ በኋላ ራሳቸውን አጥፍተዋል። ፖሊስና የአካባቢው የዓይን እማኞች በሥፍራው ለሚገኙት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎች እንደገለጹት፤ ዕድሜያቸው 50ዎቹን የተሻገረውና የሸዋሮቢት ከተማ ቀበሌ 02 ነዋሪ የነበሩት ወይዘሮ ሞሚና አህመድ (ስማቸው የተቀየረ) በአሸባሪው የህወሓት ታጣቂዎች በመደፈራቸው የልጄን ዓይን ከማይ ብለው ራሳቸውን አጥፍተዋል። ወ/ሮ ሞሚና የማገዶ እንጨት በመሸጥና እንጀራ በመጋገር የሚተዳደሩ ሲሆን፤ የ15 ዓመት ታዳጊ ልጅ እንዳላቸው የሸዋሮቢት ከተማ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ክፍል ሀላፊ ኮማንደር አህመድ መሐመድ ለኢፕድ ገልጸዋል። ዛሬ ትህነግን … [Read more...] about ሸዋሮቢት ከተማ በአሸባሪው ትህነግ ታጣቂዎች በቡድን የተደፈሩት እናት ራሳቸውን አጠፉ!
ቀጣይዋ ትግራይ = “ትግ-ሶቶ”
መውጫው እንደመግቢያው ቀላል አልሆነም። በትግሬ ልሂቃን እብደት፣ ማኅበራዊ መሠረታቸው ላይ የእሳት ቀለበት ሰርተዋል። በእያንዳንዱ የትግሬ ጎጆ የመከራ ዜና፣ የመርዶ መልዕክት ገብቷል። በጦርነቱ እና ከጦርነቱ ጋር ተያያዥ በሆኑ ምክንያቶች አራት መቶ ስድሳ ሺህ ትግሬዎች ረግፈዋል። ይህን እኔ ሳልሆን ያልኩት የሳልሳዊ ወያኔ (ሳወት) መሪ ተስፋ ኪሮስ ሳህለ ነው። ያለምንም ጥርጥር ጦርነቱ በሕዝባቸው ላይ የትውልድ ክፍተት ፈጥሯል። ምናልባትም አንድ ወንድ አምስት ሴቶችን እንዲያገባ በልዩ ሁኔታ የቤተሰብ ሕጉ ካልተሻሻለላቸው በስተቀር የትውልድ ክፍተቱን በቀላሉ አይሞሉትም። ወያኔ ራሱ በለኮሰው እሳት “እወክለዋለሁ” የሚለውን ሕዝብ የእሳት ቀለበት ውስጥ አስገብቶታል። ከዚህ ጦርነት የሚተርፍ ቢኖር እንኳ በርካታ የትግራይ ከተሞችና መንደሮች የአዛውንት እና የሕጻናት ስብስብ … [Read more...] about ቀጣይዋ ትግራይ = “ትግ-ሶቶ”
የምስራቁና የምዕራቡ ድል በመሃል አገር ይደገማል
በምሥራቅና በምዕራብ የተገኘው ድል በመሐል ሀገር እንደሚደገም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሄንን የተናገሩት በሦስተኛው ቁልፍ ግንባር ተገኝተው ከሠራዊቱ ጋር በመከሩበት ጊዜ ነው። ከሰሞኑ በሚሠሩ ኦፕሬሽኖች በወራሪው አሸባሪ የተያዙ ተጨማሪ ከተሞች ነጻ እንደሚወጡ የገለጡ ሲሆን ለወረራ የገባው አሸባሪ ምንም ነገር ይዞ እንዳይወጣ ሕዝቡ ተደራጅቶ ማስቀረት እንዳለበት ጥሪ አድርገዋል። ጠላት ፈርሷል፤ ተበትኗል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ አሁን ጠላት ያለው አማራጭ የሰረቀውን አስረክቦ እጁን መስጠት ነው ብለዋል። የሰረቀውን አስረክቦ እጁን ከሰጠ ምርኮኞችን ተከባክቦ መያዝ የጀግና ባህላችን ነው ብለዋል። ከአሸባሪው ሕወሓት ነጻ በወጡ አካባቢዎች በአስቸኳይ መስተዳድሩን በቶሎ መልሶ ማቋቋም … [Read more...] about የምስራቁና የምዕራቡ ድል በመሃል አገር ይደገማል
“ምዕራባውያን መንግሥታት ዐቢይን በእነርሱ ቁጥጥር ሥር ማዋል ባለመቻላቸው ቀጠናውን ለማተራመስ እየሰሩ ነው” – ሎውረንስ ፍሪማን
ምዕራባውያንና አሜሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን በእነርሱ ይሁንታና ቁጥጥር ስር ማዋል ባለመቻላቸው፣ ኢትዮጵያንም ሆነ ቀጠናውን ማተራመስን መምረጣቸውን የአፍሪካ ፖለቲካ እና ምጣኔ ሀብት ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ሎረንስ ፍሪማን ተናገሩ። አሜሪካ ዜጎችን ውጡ እያለች በምትወተውትበት ሰዓት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ሎረንስ ፍሪማን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት የአሜሪካና የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን በኢትዮጵያ ላይ በውሸት ላይ የተመሰረተ የስነ-ልቦና ጦርነት ከፍተዋል፡፡ ይህንን የሚያደርጉት በሚስ-ኢንፎርሜሽን ሳይሆን ሆን ብለው፣ አቅደው ተከታዮቻቸውን ዲስ-ኢንፎርም ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡ ምዕራባውያንና አሜሪካ የሐሰት መረጃ የሚያሰራጩት ኢትዮጵያውያን በመሪያቸው አማካይነት የተደፈረውን ሉዓላዊነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ እየሰሩት ያለውን ስራ የፖለቲካ … [Read more...] about “ምዕራባውያን መንግሥታት ዐቢይን በእነርሱ ቁጥጥር ሥር ማዋል ባለመቻላቸው ቀጠናውን ለማተራመስ እየሰሩ ነው” – ሎውረንስ ፍሪማን
በ2 ቀናት በተካሄደ ኦፕሬሽን 12 የትህነግ ከፍተኛ የጦር አመራሮች ተደምስሰዋል
የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ዛሬ ምሽት በሰጠው መግለጫ ተደመሰሱ ካላቸው ውስጥ በፌዴራል መንግሥት በሀገር ክህደት ወንጀል ሲፈለጉ የነበሩ ጄነራሎችና ኮሎኔሎች ይገኙበታል። በመግለጫው ላይ ተደመሰሱ የተባሉት ጄነራሎችና ኮሎኔሎች ስም አልተገለፀም። የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ በሰጡት መግለጫ ይህን ነው ያሉት፦ "ባለፉት 2 ቀናት በባቲ ግንባር በተደረገ ልዩ ኦፕሬሽን 6 የአርሚና እና የኮር ከፍተኛ አመራሮቹ ተደምስሰዋል። እነዚህ አመራሮች በፌዴራል መንግሥት በሀገር ክህደት ወንጀል ሲፈጉ የነበሩ ከሃዲ ጄነራሎች እና ኮሎኔሎች ናቸው። በተጨማሪ በከሚሴ ግንባር በተለያዩ ቦታዎች በተደረጉ ልዩ ኦፕሬሽኖች የጠላትን ግንባር ጦር ሲመሩ የነበሩ 6 ከሃዲ ከፍተኛ የጦር አመራሮች ከነጠባቂዎቻቸው ተደምስሰዋል። በዛሬው ዕለት በባቲ ግንባር በተደረገው … [Read more...] about በ2 ቀናት በተካሄደ ኦፕሬሽን 12 የትህነግ ከፍተኛ የጦር አመራሮች ተደምስሰዋል
ትህነግ ኤርትራውያንን ለመጨፍጨፍ ማቀዱን ትሮንቮል አረጋገጠ
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር - ትህነግ ስም ሳይጠራ “ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ትሠራላችሁ" በሚል የጠቀሳቸው ክፍሎች ኤርትራዊያንን እንደሆነ ጥርጥር እንደሌለው ተመለከተ። ዛቻው በኢትዮጵያ ያሉ የኤርትራ ተወላጆች ላይ እንደሆነም ተጠቁሟል። ትህነግ በመግለጫው በመከላከያ፣ በደኅንነትና ጸጥታ ተቋማት “ተሰግስጋችሁ” ሲል የፈረጃቸው ማስጠንቀቂያው እንዲደርሳቸው ደጋግሞ አመልክቷል። በዚሁ ስምና አገር ይፋ ባልተደረገበት የማስጠንቀቂያ መግለጫ የተጠቀሱት ተቋማት ውስጥ አሉ ያላቸው የውጭ ዜጎች “የአስካሁኑ በቃን” ብለው አገር ለቀው እንዲወጡ፣ አገራቸውም የተጠቀሱትን ወገኖች ከኢትዮጵያ እንዲያስወጡ ያሳሰባል። ይህ ካልሆነ “የትግራይ መንግሥትና ሰራዊት በትግራይ ህዝብ ጆኖሳይድ በፈፀሙ ወንጅሎኞች ላይ በሚወሰደዉ ማንኛዉም አፀፋዊ እርምጃ ተጠያቂ እንደማይሆን የዓለም አቀፍ … [Read more...] about ትህነግ ኤርትራውያንን ለመጨፍጨፍ ማቀዱን ትሮንቮል አረጋገጠ
የዛሬ ዓመት በማይካድራ በተፈጸመው የዘር ጭፍጨፋ
• አንድ ሺ 564 ሰዎች በጭካኔ ተገድለዋል። • 81 ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። • ድርጊቱን የፈጸመው አሸባሪው ሕወሓት ያደራጀው ሳምሪ የሚባል ገዳይ ቡድን ነው። የዛሬ ዓመት በማይካድራ በተፈጸመው የዘር ጭፍጨፋ አንድ ሺ 564 ሰዎች በጭካኔ መገደላቸውን፤ 81 ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑን ድርጊቱን የፈጸመው አሸባሪው ሕወሓት ያደራጀው ሳምሪ የሚባል ገዳይ ቡድን መሆኑን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህርና ወልቃይት፣ ጠገዴና ጠለምት የጥናት ቡድን መሪ ገለጹ። የጥናት ቡድኑ መሪ አቶ ጌታ አስራደ አለማየሁ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የዛሬ አመት በማይካድራ ጭፍጨፋውን ያካሄዱት ሳምሪ የተባለ አሸባሪው ሕወሓት ያደራጃቸው ገዳይ ቡድን ነው። ይህ ቡድን አንድ ሺ 564 ሰዎችን መጥረቢያ፣ ቆንጨራና፣ ቢለዋ፣ ማጭድና መሰል … [Read more...] about የዛሬ ዓመት በማይካድራ በተፈጸመው የዘር ጭፍጨፋ
“ከምርጫ 97 በኋላ የወያኔን ሴራ የሚያስፈፅሙ የክልሉ ተወላጆች 100ሺ ጠመንጃ እንዳከፋፈለ እናውቃለን”
የኢትዮጵያ ህዝብ በጉያው ተሸሽገው የአሸባሪውን ሀገር የማፈረስ ሴራ እያስፈፀሙ ያሉ የወያኔ ተላላኪዎችን መንጥሮ ማውጣት እንደሚገባው የዲሞክራሲ ተሟጋቹ አቶ ነዓምን ዘለቀ አስታወቁ። የአርበኞች ግንቦት ሰባት መስራችና የዲሞክራሲ ተመጓቹ አቶ ነዓምን ዘለቀ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ አሸባሪው የህወሓት ቡድን መለዮ አልብሶ ካሰማራቸው አራዊት መንጋዎች በተጨማሪ በህዝቡ ጉያ ተሸሽገው የሽብር ሥራውን የሚያስፈፅሙ ተላላኪዎችን በስፋት በማንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።በተለይም በከተሞች አካባቢ በህቡዕ ያደራጃቸው እነዚሁ ፀረ ሰላም ኃይሎች የሃሰት ወሬ በማሰራጨት የህዝቡን ስነልቦና የሚሰርቁ አሉባልታዎችን በማራገብ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም ህዝቡ የአሸባሪውን ተላላኪዎች እንቅስቃሴ በንቃት መከታተልና መንጥሮ በማውጣት በህግ ተጠያቂ ሊያደርጋቸው ይገባል። እንደአቶ ነዓምን ገለፃ፤ ኢትዮጵያን … [Read more...] about “ከምርጫ 97 በኋላ የወያኔን ሴራ የሚያስፈፅሙ የክልሉ ተወላጆች 100ሺ ጠመንጃ እንዳከፋፈለ እናውቃለን”