ጌታቸው ረዳ መሳሪያ ጭኖላቸው ሲገባ ስለተመታው አውሮፕላን በቁጭት ሲናገር “አውሮፕላኑ ሳይመታ መቀሌ ቢገባ ደስታውን አልችለውም ነበር፤ ግን መተውታል፣ ዛሬም ነገም ወደፊትም ሊመቱ ይችላሉ” ብሏል። ከሙሉው ንግግሩ ተቀንጭቦ የተወሰደውን ቪዲዮ ይመልከቱ። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about “አውሮፕላኑ ሳይመታ መቀሌ ቢገባ ደስታውን አልችለውም ነበር”
tplf terrorist
ለአሸባሪው ህወሓት ሊተላለፍ የነበረ ከ1 ሚሊየን ብር በላይ ተያዘ
ከበየዳ ወደ ስሃላ ወረዳ በቅብብሎሽ ለሽብርተኛው ህወሓት ሊደርስ የነበረ 1 ሚሊየን 253 ሺህ ብር መያዙን በአማራ ክልል ልዩ ኃይል የተከዜ ክፍለ ጦር 3ኛ ሻለቃ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ጀጃው ፈረደ ገልጸዋል። አሸባሪው ቡድን ሰርጎ ገቦችን በማዘጋጀት ገንዘብና ቁሳቁስ እንዲሻገርለት ቢፈልግም በአማራ ክልል ልዩ ኃይልና በህብረተሰቡ ጥብቅ ክትትል ዕቅዱ ከሽፏል ብለዋል። ቡድኑ ሊጠቀምበት የነበረ 600 ሊትር አረቂ፣ 10 ጣቃ አቡጀዲ፣ 15 ሺህ 9 የሶላር መብራትና ከአምስት ኩንታል በላይ ጨው እና መሰል ቁሳቁስ ከእነተጠርጣሪዎቹ መያዙን የበየዳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመላክቷል። (Fana) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ለአሸባሪው ህወሓት ሊተላለፍ የነበረ ከ1 ሚሊየን ብር በላይ ተያዘ
የትህነግ ፍቅር ያከነፈው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከኢትዮጵያ ጀርባ ከአሸባሪው ትህነግ ጋር በመደራደር የራሱን ህግ ጥሷል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከኢትዮጵያ ጀርባ ከአሸባሪው ትህነግ አመራር ጋር በቀጥታ በመደራደር የራሱን ሕግ መጣሱ ታውቋል። የድርጅቱ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ባለፈው ሳምንት ከአሸባሪው የህወሓት ቡድን ሊቀመንበር ከሆነው ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ዋና ጸሀፊው ይህንን ከአሸባሪው ድርጅት መሪ ጋር የመነጋገራቸው መረጃ የታወቀውም፤ የድርጅቱ ቃል አቀባይ ስታፌን ዱጃሪች ለተመድ ጉዳይ ዘጋቢ ጋዜጠኞች ጽፈውት ሾልኮ ከወጣው ኢሜይል ነው። የዋና ጸሀፊው ድርጊትን ተከትሎ በርካቶች ጉዳዩን በማንሳት ተገቢነት የጎደለው መሆኑን እየገለጹ ነው። ትህነግ በዓለም አቀፍ የሽብር መረጃ ቋት (Global Terrorism … [Read more...] about የትህነግ ፍቅር ያከነፈው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት
በምትኩ ካሳና ግብረአበሮቹ ላይ የሌብነት ክስ ተመሠረተ
የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ምትኩ ካሳ እና ቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ግብራበሮቹ ላይ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ በዛሬው እለት ክስ መስርቷል፡፡ ተከሳሾች 1ኛ አቶ ምትኩ ካሳ ጉትሌ (የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩ) ፣2ኛአቶ አራጋው ለማ (የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የፋይናንስ ዳይሬክተር)፣ 3ኛ አቶ የማነ ወ/ማሪያም (የኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንደ ዴቭሎፕመንት አሶሴሸን ዋና ዳይሬክተር የነበሩ)፣ 4ኛ ዶ/ር ዮናስ ወ/ትንሳይ (የኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንደ ዴቭሎፕመንት አሶሴሸን የኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ ናቸው፡፡ በተጨማሪም 5ኛ አቶ ደመውዝ ኃይሉ (ኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንደ ዴቭሎፕመንት አሶሴሸን የፋይናንስ ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ) ፣6ኛ ወ/ሮ ሶፊያ ጀማል ሰላሙ (የ1ኛ ተከሳሽ የትዳር አጋር) … [Read more...] about በምትኩ ካሳና ግብረአበሮቹ ላይ የሌብነት ክስ ተመሠረተ
የአዲስ አበባ “ሰላማዊ” ነዋሪዎች – አፍቃሪ ትህነጎች ማንነት በማስረጃ
ትግራይ ነጻ አውጪ የተሰኘውን የወንበዴዎች ድርጅት በትግራይ ሕዝብ ስም በሕይወት እንዲቆይ እያደረጉት ያሉት በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች ውስጥ በተለይ በአዲስ አበባ “ሰላማዊ” ሆነው የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች መሆናቸው በማስረጃ ተረጋገጠ። የማኅበራዊ ሚዲያ መረጃ ላይ ጠቃሚ መረጃዎችን በማስተላለፍ የሚታወቀው እስሌማን አባይ እንዳለው “በመዲናዋ ስውር አፍቃሪ ትህነጎች ያሰራጩት የ 88 በመቶ የትዊተር የሀሰት መረጃ ዘመቻ በሳምንቱ #TPLFisTheCause የሚለው ሀሽታግ በህወሃቱ Tigray Under Attack ሐሽታግ ከ30,000 በላይ ትዊት ብልጫ ተወስዶበት ይታያል” ብሏል። ትህነግ ጦርነቱን (ነሐሴ 17 ንጋት) ላይ ከመክፈቱ በፊት ጀምሮ ነበር tigray under attack በሚለው ሀሽታግ በመቶ ሺዎች የሀሰት መረጃ ትዊተር ማሰራጨት የጀመረው። በሳምንቱ ሰባት … [Read more...] about የአዲስ አበባ “ሰላማዊ” ነዋሪዎች – አፍቃሪ ትህነጎች ማንነት በማስረጃ
ባህር ኃይል ለማዘመን ስልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
"የኢትዮጵያን ባህር ኃይል ለማዘመን ከሀገር ውጭ እና በሀገር ውስጥ የሚሠጡ ስልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ" ሲሉ ተናገሩ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ። የኢትዮጵያ ባህር ኃይል በአዲስ መልክ ከተመሠረተ ጀምሮ የተለያዩ አቅም ፈጣሪ ስልጠናዎችን ከሀገር ውጭ እና በሀገር ውስጥ አባላቱን በማሠልጠን ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ዋና አዛዥ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ በብላቴ የኮማንዶ እና የአየር ወለድ ኃይል ማሠልጠኛ ማዕከል ተገኝተው የማሪን ኮማንዶ የሚሠለጥኑ የባህር ኃይል አባላትን ጎብኝተዋል። ዋና አዛዡ የስልጠና ሂደቱን ተዘዋውረው ከተመለከቱ በኋላ እንደተናገሩት የማሪን ኮማንዶ ሠልጣኞች በማሠልጠኛ ማዕከሉ የሚሠጡ ስልጠናዎችን በድሲፒሊን፣ በሞራል እና በብቃት መወጣት አለባቸው። እየተሠጠ ያለው ስልጠና ከሌሎች የሠራት ክፍሎች ጋር በመሆኑ የተሞክሮ እና … [Read more...] about ባህር ኃይል ለማዘመን ስልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
የኢትዮጵያን አየር ክልል ጥሶ ሊገባ የነበረ አውሮፕላን በአየር ኃይል ተመታ
የኢትዮጵያን መዳከም የሚፈልጉና ለዚሁም ለዘመናት የሚንቀሳቀሱ ህወሃትን በመደገፍ ላይ የሚገኙ ታሪካዊ ጠላቶች ንብረት እንደሆነ የሚታመን አውሮፕላን ለሽብር ቡድኑ የጦር መሳሪያ ጭኖ በሱዳን አልፎ የአየር ክልላችንን ጥሶ ሲገባ በጀግናው አየር ሃይል ተመትቶ ወድቋል። ሠራዊቱ የሀገሩን ሉዓላዊነት ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ በላቀ ሁኔታ ዝግጁ መሆኑም ተገልጿል። በሀገር መከላከያ ሠራዊት የመከላከያ ህብረት ዘመቻ ዋና መምሪያ የመከላከያ ኃይል ስምሪት ኃላፊ ሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ላለፉት በርካታ ወራት ከፍተኛ ወታደራዊ ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው አሸባሪው ህወሃት ካለፉት ሁለት ሳምንታት ጀምሮ ኃይሉን ለውጊያ ሲያስጠጋ ነበር። በየጊዜውም ተኩስ እየከፈተ የሀገር መከላከያን ሲተነኩስ መቆየቱንም ነው ያነሱት። ቡድኑ መንግስት የዘረጋውን የሰላም አማራጭ … [Read more...] about የኢትዮጵያን አየር ክልል ጥሶ ሊገባ የነበረ አውሮፕላን በአየር ኃይል ተመታ
በሐሰተኛ መታወቂያ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ለመውጣት እስከ 150 ሺህ ብር ይከፈላል
የትግራይ ክልል ነዋሪዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች መሀል ከተሞች በማምጣት ሥራ የተደራጁ ሰው አዘዋዋሪዎች በአንድ ሰው ከ80 እስከ 150 ሺሕ ብር እያስከፈሉ መሆኑን አዲስ ማለዳ አዘዋዋሪዎቹን በማነጋገር አረጋግጣለች። መረጃውን ማግኘት የተቻለው በሥራው የተሰማሩ ሰዎች ጉዳዩን ለማስፈጸም ያመቻቸው ዘንድ በከፈቱት የቴሌግራም ቻናል አማካኝነት ነው። አዘዋዋሪዎቹ እንደገለጹት ከሆነ፤ የትግራይ ክልል ነዋሪዎችን ወደ መሀል ከተማ የሚያመጡት ፎርጂድ መታወቂያ በማሠራት እና የቀይ መስቀል የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) አልብሰው ሠራተኛ በማስመሰል መሆኑን በግልጽ አስረድተዋል። ከተደራጆቹ መካከል ሥሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የአዲስ ማለዳ ምንጭ፣ ‹‹ቀይመስቀል Transmitter ነኝ። አንድ ሎንግቤዝ እይዛለሁ። ስሄድ የቀይመስቀል ልብስ፤ ፎርጅድ መታወቂያ እና ባጅ በሚሰጠኝ ፎቶ … [Read more...] about በሐሰተኛ መታወቂያ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ለመውጣት እስከ 150 ሺህ ብር ይከፈላል
በኢትዮጵያ ግብርና ላይ ግብጽ ለዓመታት የፈጸመችው ሤራ
የዛሬ ዘጠኝ ዓመት ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ "ኢህአዴግ ጣና በለስን ለምን አፈራረሰው?" በሚል ርዕስ አንድ ዘገባ አቅርበን ነበር። ያንን ተከትሎ ከሦስት ዓመት በኋላ አምባ – የአማራ ባለሙያዎች ህብረት የጣና በለስ ታሪካዊ የልማት ፕሮጀክት፤ ከመፈራረስና ውድመት እስከ መሸጥ በሚል ርዕስ ሌላ ዘለግ ያለ ዘገባ ለንባብ አብቅቷል። በአገራችን ያለው እና በዘመነ ት ህነግ ተስፋፍቶ መንግሥታዊ ቅርጽ የያዘው የዘር ፖለቲካና ምክን ያቱ አገራችን በነጻነት ራሷል እና ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ ለጥቁር ሕዝብ ኩራት ሆና የኖረችውን ያህል በኢኮኖሚውም መስክ ተመሳሳይ ፈር ቀዳጅ ድል እንዳትቀዳጅ ለማኮላሸት ነው። ከራሳችን በላይ ማንነታችንን እና እሴታችንን የሚያውቁት ጠላቶቻችን በቆፈሩልን ጉድጓድ ስንነጉድ ዓመታት አሳልፈናል። እስሌማን የዓባይ ልጅ በተለይ ከግብርና ጋር በተያያዘ ለዓመታት ሲፈጸምብን … [Read more...] about በኢትዮጵያ ግብርና ላይ ግብጽ ለዓመታት የፈጸመችው ሤራ
ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው
በተለይ ምዕራብ ወለጋን ምሽጉ አድርጎ ከትህነግ ጋር በመሆን ንጹሐንን እየጨፈጨፈ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሞክረው ሸኔ ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ መሆኑ ተነገረ። ሸኔን የማጽዳት ዘመቻው ወደ ፖለቲካውና መንግሥታዊ መዋቅሩም ውስጥ በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ተጠየቀ። ጎልጉል ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በአሁኑ ጊዜ በተጠናከረ ሁኔታ በሸኔ ላይ እየተካሄደ ባለው ዘመቻ ኦነግ ሸኔ ጠንካራ የሚላቸውን ይዞታዎቹን ሳይወድ በግዱ እንዲለቅ እየተደረገ ነው። በተለይ በቅርቡ በምዕራብ ወለጋ በንጹሐን ወገኖቻችን ላይ አሰቃቂና ለኅሊና የሚሰቀጥጥ ግድያ በፈጸመው ሸኔ ላይ አሁን ዝርዝሩን መናገር የማያስፈልግ ዘመቻ እየተካሄደበት ይገኛል። በቀጣይ ባሉት ቀናት መንግሥት በይፋ ዝርዝሩን የሚያሳውቅ ቢሆንም ዘመቻው በዋንኛነት ትኩረት ያደረገው የሸኔን ጠንካራ ምሽጎችን … [Read more...] about ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው










