• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሐሰተኛ መታወቂያ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ለመውጣት እስከ 150 ሺህ ብር ይከፈላል

August 19, 2022 04:25 pm by Editor Leave a Comment

የትግራይ ክልል ነዋሪዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች መሀል ከተሞች በማምጣት ሥራ የተደራጁ ሰው አዘዋዋሪዎች በአንድ ሰው ከ80 እስከ 150 ሺሕ ብር እያስከፈሉ መሆኑን አዲስ ማለዳ አዘዋዋሪዎቹን በማነጋገር አረጋግጣለች።

መረጃውን ማግኘት የተቻለው በሥራው የተሰማሩ ሰዎች ጉዳዩን ለማስፈጸም ያመቻቸው ዘንድ በከፈቱት የቴሌግራም ቻናል አማካኝነት ነው።

አዘዋዋሪዎቹ እንደገለጹት ከሆነ፤ የትግራይ ክልል ነዋሪዎችን ወደ መሀል ከተማ የሚያመጡት ፎርጂድ መታወቂያ በማሠራት እና የቀይ መስቀል የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) አልብሰው ሠራተኛ በማስመሰል መሆኑን በግልጽ አስረድተዋል።

ከተደራጆቹ መካከል ሥሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የአዲስ ማለዳ ምንጭ፣ ‹‹ቀይመስቀል Transmitter ነኝ። አንድ ሎንግቤዝ እይዛለሁ። ስሄድ የቀይመስቀል ልብስ፤ ፎርጅድ መታወቂያ እና ባጅ በሚሰጠኝ ፎቶ አሠርቼ እወስዳለሁ። የወሰድኩትን ዩኒፎርም ለብሰው በሎንግቤዝ ይዣቸው ነው የምመጣው። እንዲህ ሲደረግ የቀይመስቀል ሠራተኛ ሆኑ ማለት ነው። እስካሁን እንደዛ ነው የማመጣቸው›› በማለት አብራርቷል።

ድርጊቱን የሚያከናውኑት ተደራጅተው ተራ በተራ በመመላለስ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ ነዋሪዎቹን ወደ አዲስ አበባ ለማምጣት የሚያስከፍሉት ብርም ለወንድ እና ለሴት የተለያየ ነው ብለዋል። አንዲትን ሴት ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ ለማምጣት ክፍያው 80 ሺሕ ብር  ሲሆን፤ ለወንድ ደግሞ 150 ሺሕ ብር መሆኑን በሥራው የተሰማሩ አካላት ገልጸዋል።

ለማለፍ ምንም ዓይነት ምክንያት ስለማይኖር እድሜው ከ20 ዓመት በታች የሆነን ሰው ማምጣት እንደማይቻል ተመላክቷል። ከክልሉ ወደ መሀል ከተማ የሚመጡት ሰዎች ግን ምንም ነገር ይዘው መምጣት አይችሉም ነው የተባለው። በተያያዘም ‹‹ብሩን ደግሞ ሳልሄድ ነው የሚከፍለኝ ምክንያቱም ከሄድኩ ኔትወርክ እዛ የለም›› ነው ብለዋል።

ለወንድ ክፍያው ከፍ ያለበትን ምክንያትም፣ ከትግራይ ክልል ይዞ መውጣት አስቸጋሪ ስለሆነ እንዲሁም ለመታወቂያ እና ለአንዳንድ ነገር የማወጣው ብር ከፍተኛ በመሆኑ ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል፣ አዘዋዋሪዎቹ ከትግራይ ክልል ውጪ የሆኑና ወደ ክልሉ ለቤተሰቦቻቸው ብር መላክ የሚፈልጉ ሰዎችን በማነጋገር ከሚላከው 30 በመቶ የሚሆነውን ለራሳቸው በማድረግ የማስተላለፍ ሥራቸውን እንዳላቋረጡ ማወቅ ተችሏል።

ከአዘዋዋሪዎቹ መካከል አንዱ ሰሞኑን ወደ ትግራይ ክልል ተጉዞ ሰዎችን ለማምጣት ተረኛ መሆኑን ጠቁሞ፤ ወደ ክልሉ 500 ሺሕ ብር ይዞ እንደሚሄድም ለአዲስ ማለዳ ሙሉ መረጃውን ዘርዝሯል።

ጥሬ ብር የማስተላለፍ ድርጊቱ ከተጀመረ ሰንበትበት በማለቱ በተለይም በድንበር አካባቢ የሚገኙ ኬላዎች የሚገኙ ፈታሾች ጥብቅ ቁጥጥር እያደረጉ መሆኑ እየተነገረ ቢሆንም፤ አስተላላፊዎቹ ግን በተለያዩ ዘዴዎች እየሸወዷቸው ስለመሆኑ በዝውውር ሂደቱ ከተሰማሩ ሰዎች መረጃው ተገኝቷል።

ፈታሾችን የሚያልፉበት ዋነኛው ዘዴ እንዲተላለፍ የተፈለገውን ብር ለብዙ ሰዎች አከፋፍሎ በማስያዝ ነው። እንዲሁ ሲያደርጉ ተነቅቶባቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች እስከመከዳዳትም መድረሳቸው ተሰምቷል።

100 ሺሕ ብር ለሦስት ተከፋፍለው ከቆቦ ወደ አላማጣ ሲጓዙ የተደረሰባቸው ሰዎች ብሩን በመከዳዳታቸው እናትና ልጅ፤ እህትማማቾች ብሎም ጓደኛሞች በመካከላቸው ትልቅ ጥላቻ መፈጠሩን ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ ሰዎች ተናግረዋል።

አዲስ ማለዳ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገረቻቸው የቀይ መስቀል ማኅበር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሰለሞን አሊ፣ የቀይ መስቀልን ዩኒፎርም በማልበስ ሰዎችን ከቦታ ቦታ የሚያዘዋውሩ ሰዎች እስካሁን እንዳላገጠማቸው ገልጸዋል። ሰለሞን ጉዳዩን ከዚህ በኋላ በጥልቀት እንደሚከታተሉ አንስተው፤ ብር በማስተላለፍ ግን ከዚህ በፊትም በአፋር ክልል በኩል በቁጥጥር ሥራ የዋሉ ሰዎች እንደነበሩ አስታውሰዋል። (አዲስ ማለዳ: ቅጽ 4 ቁጥር 197 ነሐሴ 7 2014) (ፎቶ፤ ፋይል)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, Left Column, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule