• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሐሰተኛ መታወቂያ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ለመውጣት እስከ 150 ሺህ ብር ይከፈላል

August 19, 2022 04:25 pm by Editor Leave a Comment

የትግራይ ክልል ነዋሪዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች መሀል ከተሞች በማምጣት ሥራ የተደራጁ ሰው አዘዋዋሪዎች በአንድ ሰው ከ80 እስከ 150 ሺሕ ብር እያስከፈሉ መሆኑን አዲስ ማለዳ አዘዋዋሪዎቹን በማነጋገር አረጋግጣለች።

መረጃውን ማግኘት የተቻለው በሥራው የተሰማሩ ሰዎች ጉዳዩን ለማስፈጸም ያመቻቸው ዘንድ በከፈቱት የቴሌግራም ቻናል አማካኝነት ነው።

አዘዋዋሪዎቹ እንደገለጹት ከሆነ፤ የትግራይ ክልል ነዋሪዎችን ወደ መሀል ከተማ የሚያመጡት ፎርጂድ መታወቂያ በማሠራት እና የቀይ መስቀል የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) አልብሰው ሠራተኛ በማስመሰል መሆኑን በግልጽ አስረድተዋል።

ከተደራጆቹ መካከል ሥሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የአዲስ ማለዳ ምንጭ፣ ‹‹ቀይመስቀል Transmitter ነኝ። አንድ ሎንግቤዝ እይዛለሁ። ስሄድ የቀይመስቀል ልብስ፤ ፎርጅድ መታወቂያ እና ባጅ በሚሰጠኝ ፎቶ አሠርቼ እወስዳለሁ። የወሰድኩትን ዩኒፎርም ለብሰው በሎንግቤዝ ይዣቸው ነው የምመጣው። እንዲህ ሲደረግ የቀይመስቀል ሠራተኛ ሆኑ ማለት ነው። እስካሁን እንደዛ ነው የማመጣቸው›› በማለት አብራርቷል።

ድርጊቱን የሚያከናውኑት ተደራጅተው ተራ በተራ በመመላለስ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ ነዋሪዎቹን ወደ አዲስ አበባ ለማምጣት የሚያስከፍሉት ብርም ለወንድ እና ለሴት የተለያየ ነው ብለዋል። አንዲትን ሴት ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ ለማምጣት ክፍያው 80 ሺሕ ብር  ሲሆን፤ ለወንድ ደግሞ 150 ሺሕ ብር መሆኑን በሥራው የተሰማሩ አካላት ገልጸዋል።

ለማለፍ ምንም ዓይነት ምክንያት ስለማይኖር እድሜው ከ20 ዓመት በታች የሆነን ሰው ማምጣት እንደማይቻል ተመላክቷል። ከክልሉ ወደ መሀል ከተማ የሚመጡት ሰዎች ግን ምንም ነገር ይዘው መምጣት አይችሉም ነው የተባለው። በተያያዘም ‹‹ብሩን ደግሞ ሳልሄድ ነው የሚከፍለኝ ምክንያቱም ከሄድኩ ኔትወርክ እዛ የለም›› ነው ብለዋል።

ለወንድ ክፍያው ከፍ ያለበትን ምክንያትም፣ ከትግራይ ክልል ይዞ መውጣት አስቸጋሪ ስለሆነ እንዲሁም ለመታወቂያ እና ለአንዳንድ ነገር የማወጣው ብር ከፍተኛ በመሆኑ ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል፣ አዘዋዋሪዎቹ ከትግራይ ክልል ውጪ የሆኑና ወደ ክልሉ ለቤተሰቦቻቸው ብር መላክ የሚፈልጉ ሰዎችን በማነጋገር ከሚላከው 30 በመቶ የሚሆነውን ለራሳቸው በማድረግ የማስተላለፍ ሥራቸውን እንዳላቋረጡ ማወቅ ተችሏል።

ከአዘዋዋሪዎቹ መካከል አንዱ ሰሞኑን ወደ ትግራይ ክልል ተጉዞ ሰዎችን ለማምጣት ተረኛ መሆኑን ጠቁሞ፤ ወደ ክልሉ 500 ሺሕ ብር ይዞ እንደሚሄድም ለአዲስ ማለዳ ሙሉ መረጃውን ዘርዝሯል።

ጥሬ ብር የማስተላለፍ ድርጊቱ ከተጀመረ ሰንበትበት በማለቱ በተለይም በድንበር አካባቢ የሚገኙ ኬላዎች የሚገኙ ፈታሾች ጥብቅ ቁጥጥር እያደረጉ መሆኑ እየተነገረ ቢሆንም፤ አስተላላፊዎቹ ግን በተለያዩ ዘዴዎች እየሸወዷቸው ስለመሆኑ በዝውውር ሂደቱ ከተሰማሩ ሰዎች መረጃው ተገኝቷል።

ፈታሾችን የሚያልፉበት ዋነኛው ዘዴ እንዲተላለፍ የተፈለገውን ብር ለብዙ ሰዎች አከፋፍሎ በማስያዝ ነው። እንዲሁ ሲያደርጉ ተነቅቶባቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች እስከመከዳዳትም መድረሳቸው ተሰምቷል።

100 ሺሕ ብር ለሦስት ተከፋፍለው ከቆቦ ወደ አላማጣ ሲጓዙ የተደረሰባቸው ሰዎች ብሩን በመከዳዳታቸው እናትና ልጅ፤ እህትማማቾች ብሎም ጓደኛሞች በመካከላቸው ትልቅ ጥላቻ መፈጠሩን ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ ሰዎች ተናግረዋል።

አዲስ ማለዳ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገረቻቸው የቀይ መስቀል ማኅበር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሰለሞን አሊ፣ የቀይ መስቀልን ዩኒፎርም በማልበስ ሰዎችን ከቦታ ቦታ የሚያዘዋውሩ ሰዎች እስካሁን እንዳላገጠማቸው ገልጸዋል። ሰለሞን ጉዳዩን ከዚህ በኋላ በጥልቀት እንደሚከታተሉ አንስተው፤ ብር በማስተላለፍ ግን ከዚህ በፊትም በአፋር ክልል በኩል በቁጥጥር ሥራ የዋሉ ሰዎች እንደነበሩ አስታውሰዋል። (አዲስ ማለዳ: ቅጽ 4 ቁጥር 197 ነሐሴ 7 2014) (ፎቶ፤ ፋይል)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, Left Column, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule