• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሐሰተኛ መታወቂያ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ለመውጣት እስከ 150 ሺህ ብር ይከፈላል

August 19, 2022 04:25 pm by Editor Leave a Comment

የትግራይ ክልል ነዋሪዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች መሀል ከተሞች በማምጣት ሥራ የተደራጁ ሰው አዘዋዋሪዎች በአንድ ሰው ከ80 እስከ 150 ሺሕ ብር እያስከፈሉ መሆኑን አዲስ ማለዳ አዘዋዋሪዎቹን በማነጋገር አረጋግጣለች።

መረጃውን ማግኘት የተቻለው በሥራው የተሰማሩ ሰዎች ጉዳዩን ለማስፈጸም ያመቻቸው ዘንድ በከፈቱት የቴሌግራም ቻናል አማካኝነት ነው።

አዘዋዋሪዎቹ እንደገለጹት ከሆነ፤ የትግራይ ክልል ነዋሪዎችን ወደ መሀል ከተማ የሚያመጡት ፎርጂድ መታወቂያ በማሠራት እና የቀይ መስቀል የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) አልብሰው ሠራተኛ በማስመሰል መሆኑን በግልጽ አስረድተዋል።

ከተደራጆቹ መካከል ሥሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የአዲስ ማለዳ ምንጭ፣ ‹‹ቀይመስቀል Transmitter ነኝ። አንድ ሎንግቤዝ እይዛለሁ። ስሄድ የቀይመስቀል ልብስ፤ ፎርጅድ መታወቂያ እና ባጅ በሚሰጠኝ ፎቶ አሠርቼ እወስዳለሁ። የወሰድኩትን ዩኒፎርም ለብሰው በሎንግቤዝ ይዣቸው ነው የምመጣው። እንዲህ ሲደረግ የቀይመስቀል ሠራተኛ ሆኑ ማለት ነው። እስካሁን እንደዛ ነው የማመጣቸው›› በማለት አብራርቷል።

ድርጊቱን የሚያከናውኑት ተደራጅተው ተራ በተራ በመመላለስ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ ነዋሪዎቹን ወደ አዲስ አበባ ለማምጣት የሚያስከፍሉት ብርም ለወንድ እና ለሴት የተለያየ ነው ብለዋል። አንዲትን ሴት ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ ለማምጣት ክፍያው 80 ሺሕ ብር  ሲሆን፤ ለወንድ ደግሞ 150 ሺሕ ብር መሆኑን በሥራው የተሰማሩ አካላት ገልጸዋል።

ለማለፍ ምንም ዓይነት ምክንያት ስለማይኖር እድሜው ከ20 ዓመት በታች የሆነን ሰው ማምጣት እንደማይቻል ተመላክቷል። ከክልሉ ወደ መሀል ከተማ የሚመጡት ሰዎች ግን ምንም ነገር ይዘው መምጣት አይችሉም ነው የተባለው። በተያያዘም ‹‹ብሩን ደግሞ ሳልሄድ ነው የሚከፍለኝ ምክንያቱም ከሄድኩ ኔትወርክ እዛ የለም›› ነው ብለዋል።

ለወንድ ክፍያው ከፍ ያለበትን ምክንያትም፣ ከትግራይ ክልል ይዞ መውጣት አስቸጋሪ ስለሆነ እንዲሁም ለመታወቂያ እና ለአንዳንድ ነገር የማወጣው ብር ከፍተኛ በመሆኑ ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል፣ አዘዋዋሪዎቹ ከትግራይ ክልል ውጪ የሆኑና ወደ ክልሉ ለቤተሰቦቻቸው ብር መላክ የሚፈልጉ ሰዎችን በማነጋገር ከሚላከው 30 በመቶ የሚሆነውን ለራሳቸው በማድረግ የማስተላለፍ ሥራቸውን እንዳላቋረጡ ማወቅ ተችሏል።

ከአዘዋዋሪዎቹ መካከል አንዱ ሰሞኑን ወደ ትግራይ ክልል ተጉዞ ሰዎችን ለማምጣት ተረኛ መሆኑን ጠቁሞ፤ ወደ ክልሉ 500 ሺሕ ብር ይዞ እንደሚሄድም ለአዲስ ማለዳ ሙሉ መረጃውን ዘርዝሯል።

ጥሬ ብር የማስተላለፍ ድርጊቱ ከተጀመረ ሰንበትበት በማለቱ በተለይም በድንበር አካባቢ የሚገኙ ኬላዎች የሚገኙ ፈታሾች ጥብቅ ቁጥጥር እያደረጉ መሆኑ እየተነገረ ቢሆንም፤ አስተላላፊዎቹ ግን በተለያዩ ዘዴዎች እየሸወዷቸው ስለመሆኑ በዝውውር ሂደቱ ከተሰማሩ ሰዎች መረጃው ተገኝቷል።

ፈታሾችን የሚያልፉበት ዋነኛው ዘዴ እንዲተላለፍ የተፈለገውን ብር ለብዙ ሰዎች አከፋፍሎ በማስያዝ ነው። እንዲሁ ሲያደርጉ ተነቅቶባቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች እስከመከዳዳትም መድረሳቸው ተሰምቷል።

100 ሺሕ ብር ለሦስት ተከፋፍለው ከቆቦ ወደ አላማጣ ሲጓዙ የተደረሰባቸው ሰዎች ብሩን በመከዳዳታቸው እናትና ልጅ፤ እህትማማቾች ብሎም ጓደኛሞች በመካከላቸው ትልቅ ጥላቻ መፈጠሩን ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ ሰዎች ተናግረዋል።

አዲስ ማለዳ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገረቻቸው የቀይ መስቀል ማኅበር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሰለሞን አሊ፣ የቀይ መስቀልን ዩኒፎርም በማልበስ ሰዎችን ከቦታ ቦታ የሚያዘዋውሩ ሰዎች እስካሁን እንዳላገጠማቸው ገልጸዋል። ሰለሞን ጉዳዩን ከዚህ በኋላ በጥልቀት እንደሚከታተሉ አንስተው፤ ብር በማስተላለፍ ግን ከዚህ በፊትም በአፋር ክልል በኩል በቁጥጥር ሥራ የዋሉ ሰዎች እንደነበሩ አስታውሰዋል። (አዲስ ማለዳ: ቅጽ 4 ቁጥር 197 ነሐሴ 7 2014) (ፎቶ፤ ፋይል)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, Left Column, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule