• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው

July 19, 2022 01:55 am by Editor Leave a Comment

በተለይ ምዕራብ ወለጋን ምሽጉ አድርጎ ከትህነግ ጋር በመሆን ንጹሐንን እየጨፈጨፈ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሞክረው ሸኔ ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ መሆኑ ተነገረ። ሸኔን የማጽዳት ዘመቻው ወደ ፖለቲካውና መንግሥታዊ መዋቅሩም ውስጥ በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ተጠየቀ።

ጎልጉል ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በአሁኑ ጊዜ በተጠናከረ ሁኔታ በሸኔ ላይ እየተካሄደ ባለው ዘመቻ ኦነግ ሸኔ ጠንካራ የሚላቸውን ይዞታዎቹን ሳይወድ በግዱ እንዲለቅ እየተደረገ ነው። በተለይ በቅርቡ በምዕራብ ወለጋ በንጹሐን ወገኖቻችን ላይ አሰቃቂና ለኅሊና የሚሰቀጥጥ ግድያ በፈጸመው ሸኔ ላይ አሁን ዝርዝሩን መናገር የማያስፈልግ ዘመቻ እየተካሄደበት ይገኛል።

በቀጣይ ባሉት ቀናት መንግሥት በይፋ ዝርዝሩን የሚያሳውቅ ቢሆንም ዘመቻው በዋንኛነት ትኩረት ያደረገው የሸኔን ጠንካራ ምሽጎችን መቆጣጠር ሲሆን ሌላው ደግሞ ዋነኛ አመራሮቹን ማስወገድ ነው። ጎልጉል ያገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው ዘመቻው በሁለቱም መስክ ወሳኝ ድሎችን እያስመዘገበ ነው። አሁን መጥቀስ ባያስፈልግም ዘመቻው በከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ አመራሮች እየተመራ መሆኑ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

ይህ በወታደራዊ መስክ እየተገኘ ያለው ድል በወለጋ ብቻ ሳይሆን ለወለጋ ቅርብ በሆኑና በሌሎች ሸኔ ጠንካራ ምሽጎቼ በሚላቸው አካባቢዎች ጭምርም እንደሆነ ታውቋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ኅብረተሰቡ ሸኔ የኦሮሞ ነጻ አውጪ ሳይሆን ከትህነግ ጋር ለመሥራት የፈረመ፣ ለዕኩይ ዓላማ የተሰለፈ ጸረ ኦሮሞ መሆኑን ተረድቶ ልጆቹን በማዝመትም ሆነ ሸኔን በመደገፍ እንዳይተባበር በማድረግ ረገድ ውጤታማ ሥራዎች መሠራታቸውን ጎልጉል ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ይህ በሸኔ ላይ የተመዘገበው ድል በወታደራዊ ዘመቻ ብቻ ሳይሆን ወደ ፖለቲካዊ አመራሩም እንዲዘልቅ የአገር ወዳድ ዜጎች ፍላጎት መሆኑ ታውቋል። ጥያቄያቸው እንዲሰማላቸው የሚፈልጉ ወገኖች እንደሚሉት የሸኔ ስኬት በሜዳ ላይ ብቻ ሳይሆን በመንግሥታዊና ክልላዊ መዋቅር ውስጥ ባሉ ከሚያገኘው ድጋፍ መሆኑ ታውቆ ተመሳሳይ የማጽዳት ዘመቻ ከታች እስከላይ እንዲደረግ የዜጎች ጥያቄ መሆኑ ለመረዳት ተችሏል።

በቅርቡ በመንግሥት በኩል ዝርዝሩ የሚገለጽ ይሆናል።   

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ  

(ፎቶ፤ ለማሳያ የቀረበ)

Filed Under: News, Slider Tagged With: ethiopian terrorists, olf shanee, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule