በጋሸና ግንባር የሚገኙ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት በጠላት ላይ የላቀ የበላይነት እያገኙ እንደሆነ አባላቱና መሪዎቹ ተናግረዋል። ሳጅን ካሳዬ ወርቁ በጋይንት ግንባር ያለው የአማራ ልዩ ኃይል ተጋድሎ አኩሪ እንደነበረ ተናግሯል። ልዩ ኃይሉ ከጋሳይ ጀምሮ እስከ ደብረ ዘቢጥ ጀብድ ፈጽሟል ብሏል። የሀገር መከላከያ ሠራዊትና ልዩ ኃይሉ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድንን በተቀናጀ መልኩ እንደደመሰሱት ገልጿል። ጠላት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ለማስረከብ እንደተገደደም አስረድቷል። ኮንስታብል አሳልፍ ተመሰለው ልዩ ኃይሉ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት የአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድንን እንደደመሰሱት ተናግሯል። የአማራ ብሎም የኢትዮጵያ ሕዝቦች ከአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን ነፃ እስኪሆኑ ድረስ ተጋድሏቸውን እንደሚቀጥሉ ነው … [Read more...] about “የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሲተኩስ ከአንገት በላይ መምታት እንዳለበት አምኖ ነው”
tplf terrorist
ልደቱ ትህነግን ለማዳን ጥሪ አቀረበ፤ አማራ የኅልውና ችግር አልገጠመውም
“አማራውም ሆነ አፋሩ ምንም ዓይነት የኅልውና አደጋ አላጋጠመውም፤ ቀሪው የኢትዮጵያ ሕዝብ ምንም በትህነግ የደረሰበት ችግር የለም፤ አማራውም ሆነ አፋሩ በትህነግ በጅምላ አልተጨፈጨፈም፤ ማይካድራ፣ ጭና፣ አጋምሳ፣ ጋሊኮማ፣ ወዘተ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተፈጸመ ጭፍጨፋ ነው እንጂ በዲሲፒሊን የታነጸው ትህነግ እንዲህ ዓይነት ግፍ አይፈጽምም፣ በአጠቃላይ “ሒሳብ እናወራርድብሃለን” የተባለው የአማራው ሕዝብ በትህነግ ምንም ግፍ አልደረሰበትም፤ ወልቃይት የምዕራብ ትግራይ አካል ነው፣ ራያም የትግራይ ነው፤ ወዘተ። ስለዚህ ትህነግ ሳትሞት በሽግግር መንግሥት ምሥረታ የአፍ ለአፍ ትንፋሽ እንስጣትና እንታደጋት”።ልደቱ አያሌው ትህነግ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ሲገባ ለመታደግ ከሚረባረቡት “ቅምጥ” ቡድኖች መካከል በቀዳሚነት የሚሰለፈው ልደቱ አያሌው ነው። ከእርሱ ሌላ የቀድሞ የትህነግ … [Read more...] about ልደቱ ትህነግን ለማዳን ጥሪ አቀረበ፤ አማራ የኅልውና ችግር አልገጠመውም
ልደቱ አያሌውን ስድስት ነገሮች ሆነው ይሆናል በሉት
አቶ ልደቱ አያሌው የፖለቲካ ህይወቱን አሀዱ ብሎ የጀመረው 1983ዓ.ም. ህወሃት/ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ የከተማዋን ወጣቶች የማደራጀት ስራ ላይ ከተሰማሩ ወጣቶች አንዱ ሆኖ ነው። በዚያ ወቅት ወጣቱ ልደቱ ለወያኔ መንግስት የመወገን ጫና በነበረበት የወጣት ማህበር ምስረታ ሂደት ንቁ ተዋናይ ነበረ። በመሆኑም የማህበሩ ሊቀመንበር የመሆን ፍላጎት እንደነበረው በወቅቱ አብረውት የነበሩ የመሰከሩት ነገር ነው። ነገር ግን በ1990 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በይፋ ሲመሰረት ወጣቱን በማደራጀት ምንም ተሳትፎ ያልነበረው የዳዊት ዮሃንስ (አፈጉባዔ የነበረ) ሚስት ወንድም የሆነው ወጣት ታጠቅ ካሳ ሊቀመንበር ሆኖ ተመረጠ። ይሄኔ ነው እንግድህ የልደቱ የመጀመሪያው የፖለቲካ አቋም እጥፋት የተጀመረው። የታጠቅን በሊቀመንበርነት መመረጥ አሚን ብሎ መቀበል አልፈለገም። … [Read more...] about ልደቱ አያሌውን ስድስት ነገሮች ሆነው ይሆናል በሉት
5 ሚሊዮን “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ተጀመረ
ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለዓለም የማስረዳትና የአሸባሪውን ህወሃት የጥፋት ድርጊት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማሳየትን አላማ ያደረገው "የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት" ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል። ዘመቻው ይፋ ሲደረግ ሚኒስትሮች፣ የተለያዩ ታዋቂ ግለሰቦችና በርካታ ወጣቶች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። "የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት" ዘመቻ ከዛሬ ጀምሮ አስከ መስከረም 15 ቀን 2014 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል። “በኢትዮጵያ ላይ በተሳሳተ መልኩ የሚነዛው አሉባልታ ከእውነት የራቀ መሆኑን ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ለማሳየት በዘመቻው ይሰራል” ተብሏል። በዚሁ ንቅናቄ ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እንዲደርስ ይሰራል ተብሏል። በዚህ ዘመቻ ከ5 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል። በሌላ በኩል … [Read more...] about 5 ሚሊዮን “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ተጀመረ
ሃብትና ቀለባቸው በትህነግ ወራሪ ተዘርፎ የዕለት ጉርስ አልባ የሆኑት እማሆይ ሲሳይ ዋጋው
እማሆይ ሲሳይ ዋጋው የደብረ ዘቢጥ ከተማ ነዋሪ ናቸው። የዛሬን አያድረገውና በየዓመቱ የዘመን መለወጫ በዓል ሲመጣ ቤት ያፈራውን በማዘጋጀት በዓሉን በደስታ ያከብሩ ነበር። “የዘመን መለወጫ ለእኔ ልዩ በዓል ነበር” ያሉት እማሆይ ሲሳይ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ከተማቸውን በወረረበት ወቅት ሀብትና ቀለባቸው በመዝረፉ በዓልን አስፈላጊውን ነገር አዘጋጅቶ በደስታ ማሳለፍ ቀርቶ የዕለት ጉርስ ማጣታቸውን ተናግረዋል። እማሆይ ሲሳይ እንዳሉት የእሳቸው ንብረት ብቻ ሳይሆን የቀበሌው ነዋሪዎች ሁሉ በሽብር ቡድኑ በመዘረፉ ችግሩን የበለጠ የከፋ ያደርገዋል። “ይህ ክፉ ጊዜ ይለፍ እንጅ በዓል ሁሌም ይደረሳል። ብቻ ሀገራችንን ሰላም ያድርጋት” ነው ያሉት። አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ከተማቸውን በወረረበት ወቅት አቅም በሌለው ጉልበታቸው ወደ ጫካ ገብተው … [Read more...] about ሃብትና ቀለባቸው በትህነግ ወራሪ ተዘርፎ የዕለት ጉርስ አልባ የሆኑት እማሆይ ሲሳይ ዋጋው
የሽብርተኛው ትህነግ ግፍና በደል በዛሪማ
አሸባሪው የህወሓት ቡድን በዛሪማና አካባቢው ሰርገው በገቡባቸው ቀናት የተለያዩ ግፍና በደሎች መፈፀማቸውን ተጎጂ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ በዛሪማ ከተማ የሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የተከራየውን ንብረትነቱ የኪዳነምህረት ገዳም የሆነ ህንፃ የሚቆጣጠሩት አባ ገብረማርያም ሳሙኤል እንደተናገሩት፣ አሸባሪ ቡድኑ እኔን እንኳ በአባትነት ሳያከብሩኝ ገፍትረው ጥለው የባንኩን ኤቲኤም ማሽን ሰብረው መዝረፋቸውንና ወደውስጥ በመግባትም የፈለጉትን አድርገው መውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ በዛሪማ ከተማ ተወልደው ያደጉት አቶ ባዬ አትክልት እና አቶ ዳግማዊ ገነነውም የሽብር ቡድኑ ዘራፊዎች የሞቀ ቤታቸውን በማዘጋት ሱቃቸውንና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሳቸውን እንደዘረፏቸው ገልጸዋል፡፡ ቋንቋና ዘርን እየለዩ አሰቃይተውናል ያሉት አቶ ባዬ እና አቶ ዳግማዊ መሳሪያ … [Read more...] about የሽብርተኛው ትህነግ ግፍና በደል በዛሪማ
የዛሪማን ድልድይ በውስጥ በኩል ቦርቡሮ ፈንጅ ለመደበቅ ያሤረው ጠላት ተደምስሷል
በማይጠብሪ ግንባር የሚገኘው የወገን ጦር ጠላትን እየደመሰሰ ወደ ፊት እየገሰገሰ ነው። በጭና ቆርጦ ደባርቅና ዳባትን ሊይዝ የነበረው የትግራይ ወራሪ ቡድን በጭና እና በተለያዩ አካባቢዎች ድባቅ ተመትቶ አብዛኛው ተደምስሷል። የቀረው ወደ ኋላ በመመለስ ወደ መጣበት እየፈረጠጠ ነው። በግንባሩ የተሰማራው የወገን ጦርም እየተከታተለ እየደመሰሰው ነው። በግንባሩ የክፍለ ጦር አዛዥ እንደነገሩን ሠራዊቱ በቦዛ፣ በጭና፣ በብና እና በተለያዩ አካባቢዎች ከባድ ጦርነት ማድረጉን ነው የተናገሩት። በተደረገው ጦርነትም የጠላት ቡድን ተደምስሷል። በዛሪማና በድብ ባሕር አድርጎ ወደ ሊማሊሞ ሊወጣ የነበረው አሸባሪ ቡድንም በወገን ጦር ተመትቷል ነው ያሉት። ከድብ ባሕር እስከ ዛሪማ እየተቀጠቀጠ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ መመለሱን ነው የተናገሩት። ጠላት መልሶ እንዳይቋቋም ካደረጉት ምቶች መካከል … [Read more...] about የዛሪማን ድልድይ በውስጥ በኩል ቦርቡሮ ፈንጅ ለመደበቅ ያሤረው ጠላት ተደምስሷል
CNN ትህነግን እንደ ማስረጃ ጠቅሶ የሠራው ዘገባና ያፈተለከው ቅሌት
ሲኤንኤን (CNN) “አሰቃቂው ዕይታ” የሚል ርዕስ የሰጠውን እና በሁመራ ተፈፅሟል ያለውን ግርፋት፣ ጅምላ እስር እና ግድያን በተመለከተ የምርመራ ዘገባ አቅርቧል። እነዚህ ግርፋት፣ ጅምላ እስር እና ግድያ የተፈፀሙት “በኢትዮጵያ ሠራዊት እና አጋሮቹ” ሲል በገለጻቸው ኃይሎች መሆኑንም ምስክሮቹን ጠቅሶ ደምድሟል። የዚህ የምርመራ ዘገባ መነሻ የሆነው በሱዳን ድንበር አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ላይ የሚንሳፈፉ አስከሬኖች ዳግም መገኘታቸው እንደሆነ ሚዲያው ጠቅሷል። ኒማ ኤልባጊር ይሁን እንጂ የዘገባው አዘጋጅ የሆነችው ሱዳናዊቷ ጋዜጠኛ ኒማ ኤልባጊር ለምስክርነት የመረጠቻቸው ሰዎች ገለልተኛ አለመሆን እና የአሸባሪው ህወሓት ቡድን ደጋፊዎች መሆናቸው የዘገባውን ተዓማኒነት አጠያያቂ አድርጎታል። በተለይ ተፈፅመዋል የተባሉትን ግድያዎች በዝርዝር የሚናገረው እና የሞቱ ሰዎች … [Read more...] about CNN ትህነግን እንደ ማስረጃ ጠቅሶ የሠራው ዘገባና ያፈተለከው ቅሌት
ሲራጅ ዲቢል አሊ 5 ገድለው 6 ክላሽ የማረኩ የድሬ ሮቃው ጀግና
ስማቸው ሲራጅ ዲቢል አሊ ይባላሉ። በሀብሩ ወረዳ 024 ድሬ ሮቃ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ከሰሞኑ አሸባሪው የትህነግ ወራሪ ቡድን ወደ ቀበሌያቸው ለመግባት ሲሞክር ቀበሌያቸውን ባለማስደፈር ታላቅ ጀብዱ ሰርተዋል። በሚኖሩበት ድሬ ሮቃ ቀበሌ ግንባር ላይ በመሰለፍ አንድ የአሸባሪው ቡድን አባል በወገን ጦር ላይ ጥቃት ለመፈፀም ሲሞክር በድንጋይ አንገቱን ብለው የያዘውን ክላሽ ማርከውታል። ከዚያም ሌሎች አምስት የአሸባሪው ቡድን አባላት ጓደኛቸውን ለማንሳት ሲመጡ አምስቱንም በመግደል የያዙትን አምስት ክላሽ በመማረክ በአጠቃላይ 6 ክላሽ ከአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን መማረክ ችለዋል። በሃይማኖቴ እና በኢትዮጵያዊነቴ አልደራደርም የሚሉት አቶ ሲራጅ ወጣቱ የሀገሩን ሰላም እንዲጠብቅ ጥሪ … [Read more...] about ሲራጅ ዲቢል አሊ 5 ገድለው 6 ክላሽ የማረኩ የድሬ ሮቃው ጀግና
❝አላህ ይፍረደኝ የልጆቼን አባት አንገላተው ገደሉት፤ ጅብ አስበሉት ብጥስጣሽ ልብሱ ውርማ ተገኘ❞ ወ/ሮ ጦይባ
አሸባሪው የትህነግ ቡድን መግደል ብቻ ሳይሆን የቤተሰቦቻችንን አስክሬን ጅብ አስበልቶ የግፍ ግፍ ፈጽሞብናል ሲሉ የወረባቦ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። አሸባሪው የትህነግ ቡድን በወረባቦ ወረዳ ህጻናትን፣ ሴቶችን፣ አርሶአደሮችን በግፍ ገድሏል፤ ሃብትና ንብረት ዘርፏል ብሎም አውድሟል። በወረባቦ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ካሊድ ሙሐመድ የተመራ ልዑክ አሸባሪው ትህነግ በወረዳው ጥቃት ያደረሰባቸውን፣ ንብረታቸው የተዘረፈባቸውንና የወደመባቸውን ወገኖች ተመልክቷል፡፡ በሰው ደም የሰከረው ሽብርተኛው የትህነግ ቡድን በየደረሰበት ሁሉ የጥፋት ሰይፉን እየመዘዘ ንጹሐንን ገድሏል። ለአማራ ያለውን ስር የሰደደ ጥላቻ በሚፈጽመው እኩይ ድርጊት እያሳየ ይገኛል። በሁሉም ግንባሮች ከፍተኛ ሽንፈት ሲደርስበት ኀይሉን አሰባስቦ ደሴ፣ ሐይቅና ኮምቦልቻን መዳረሻዎቹ ሊያደርግ በደቡበ ወሎ በወረባቦ … [Read more...] about ❝አላህ ይፍረደኝ የልጆቼን አባት አንገላተው ገደሉት፤ ጅብ አስበሉት ብጥስጣሽ ልብሱ ውርማ ተገኘ❞ ወ/ሮ ጦይባ