• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደሴ በወገን እጅ – መከላከያ እየገፋ ነው!

October 31, 2021 05:18 am by Editor 1 Comment

ደሴን ለመውረር አሰፍስፎ የነበረ አሸባሪው የህወሃት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል

በወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብቶ የነበረ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂም ባለበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው ተሸኝቷል

የደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለሙ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት አልተረዱም

ልዩ መረጃ፤ ከጥቂት ደቂዎች በፊት ጎልጉል እንዳረጋገጠው ደሴን ያረጋጋው መከላከያ ሠራዊት፣ ልዩ ኃይል፣ ሕዝባዊ ሚሊሻና ፋኖ

በርካታ አካባቢዎችን እየተቆጣጠረና በወገን እጅ ሥር እያደረጋቸው ይገኛል። በዚህም ጠላት በከፍተኛ ሁኔታ እየተደመሰሰና እየሸሸ እንደሆነ ለማረጋገጥ ችለናል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ላለቁት ልጆቹ ትህነግን ለመጠየቅ እንዲዘጋጅ አሳስቧል።


በጢጣ በኩል ሰብሮ በመግባት የደሴ ከተማን ለመቆጣጠር የሞከረው አሸባሪው የህወሃት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል።

የመጣውን ኃይልም ደሴ ከተማ ከመግባቱ በፊት ሙሉ በሙሉ ባለበት ማስቀረት መቻሉን በወሎ ግንባር ወራሪውን ኃይል እያጸዱ የሚገኙ የመከላከያና ደህንነት ምንጮች ለኢዜአ ጠቁመዋል።

የደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለመ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት ካለመረዳት የመነጨ እንደሆነ አስታውቀዋል።

በግንባሩ የተሰለፉ የሰራዊት አመራርና አባላትም ወራሪውን ኃይል ለአንዴና መጨረሻ ለማጥፋት አኩሪ ተጋድሎ እየፈጸሙ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

በኩታበር በኩል አሰፍስፎ ደሴን ለመውረር የመጣው ወራሪ ኃይልም ምንም ማድረግ እንዳይችል ተደርጎ መደቆሱን ገልጸዋል።

በወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብተው የነበሩ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂዎችም ባሉበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው መሸኘታቸውን ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።

ደሴና አካባቢዋን ለመውረር ከየአቅጣጫው ተሰባስቦ አሰፍስፎ የነበረውን ኃይልም አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የደሴን ከተማ በወገን እጅ እንዳለች ማስቀጠል መቻሉን ገልጸዋል።

የደሴ ከተማ እና አካባቢው የሽብር ቡድኑን የአፈሳ ወሬ ባለመስማት አካባቢውን ጸንቶ እንዲጠብቅና ለግንባሩ ሰራዊት ሲያደርጉት የነበረውን ደጀንነት እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል።

በግንባሩ ያሉ የሰራዊት አባላት የጥፋት ቡድኑን ማጽዳት ይቀጥላሉ ያሉት ምንጮቻችን በቅርብ ጊዜም ይህኑ የኢትዮጵያ ጠላት የሆነ ወራሪ ኃይልም እስከወዲያኛው የሚሸኙበት ቀን ሩቅ እንዳልሆነ አረጋግጠዋል። (ኢዜአ)

ማሳሰቢያ፤ እስካሁን በታሪካችን አስከሬን አትመን አናውቅም ነበር፤ ሆኖም ትህነግ በሕዝባችን ላይ እያደረሰው ካለው አንጻር ይህንን ፎቶ ማውጣታችን እንዲታወቅ እንፈልጋለን

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 31, 2021 09:31 am at 9:31 am

    በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ታሪክ ውስጥ እንደ ወያኔ ያለ ጸላዬ ሰናይ የተጠናወተው ከናዚ ጀርመኖችና ከጣሊያን ወራሪ ሃይል የከፋ ራስ በቀል አረመኔ ገጥሟት አያውቅም። አብረው ቁጭ ብለው በልተው ምግብህና መጠጥህ ውስጥ መርዝ ጨምረው ገለው ሃዘን ላይ ቁጭ ብለው የሃዘን ንፍሮ የሚበሉ ዘግናኝ ፍጡሮች ናቸው። አሁን በደሴና ዙሪያዋ አስቀድመው አሰልጥነውና አስታጥቀው ባሰለፏቸው ሃገር ከሃዲ ሰዎች እየተጠቆሙ ነው ሆቴሎችን አልፎ ተርፎም የታወቁ ሰዎች ቤቶችን ለመደምሰስ የሞከሩት። እነዚህ ሰዎች ከራሳቸው ዘር ውጭ ሌላው ሰው መስሎ አይታያቸውም። ርህራሄ የሚባል ነገር አልተፈጠረባቸውም። ግን አንድ አንድ ሃበሻ አብሮ ከእነርሱ ጋር ሰክሯል። የእነርሱን የፕሮፓጋንዳ ወሬ ተቀብሎ ያናፍሳል። አብሮም ይነፍሳል። የጠ/ሚሩን መንግስት ቅርንጫፍ አልባ እንደ ቀረ ግንድ ይመለምላል። ይህ ሁሉ ግን ለወያኔና ለኦነግ ሸኔ ፈንጠዚያ ነው። የጠ/ሚሩ መንግስት ሴረኞችን አቅፏል፤ ለወያኔ ከውስጥ ሆነው ወሬ የሚያቀብሉትን ዝም ይላል ገለ መሌ መባሉን ከጊዜ ጋር በመረጃ የምንሟገተው ሲሆን አሁን ባለንበት የሞትና የሽረት ሰአት ግን ጠ/ሚሩንና አመራራቸውን የምንነቅፍበት ጊዜ አይመስለኝም። አሁን ሁሉም ነገር ወደ ወያኔ ቢያተኩርና የዚህ እልቂት መቋጫን መፈለጉ ለሃገሪቱና ለህዝቦቿ ደህንነት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። አሁን እንሆ እልፍ ገደልን እልፍ ማረክን እያሉ የሚያወሩና የሚያስወሩ ሙታን ቆጠራቸን በመተው ቆሞ ህዝባችን የሚገድለውንና የሚዘርፈውን መግደል አለባቸው። በዚህ ዙሪያ ላይ በየስፍራው ወደቀ የተባለው አስከሬን ተሰብስቦ ካልተቃጠለ ወይም ካልተቀበረ ሊያስከትል የሚችለው የበሽታ አይነት በጥይት የማንመክተው ይሆናል። አውቃለሁ ሙትን ማቃጠል በሃገራችን የተለመደ አይደለም። ለምሳሌ በጃፓን ከ 90 % በላይ ሙታናቸውን ያቃጥላሉ። ህንድና ከህንድ ተቆርሰው ሃገር የሆኑት እንደ ፓኪስታን ያሉ ሃገሮች ደግሞ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን አስከሬን ያጋያሉ። ሰልጥኛለሁ ከእኔ በላይ ላሳር ነው የሚሉት ምዕራባዊያን ሃገሮችም አሁን አሁን cremation የተለመደ ተግባር ሆኗል። ባጭሩ ሙታን መቀበር ወይም መቃጠል አለባቸው። ያለበለዚያ ቋሚን ወደ ላይኛው ዓለም የሚያሸጋግር በሽታ ያመጣሉ።
    አሁን በደሴ (ወሎ) እየሆነ ያለውን ነገር በእርግጠኝነት የሚያውቅ የለም። የዜናው አውታር ሰበር ብሎ ከለጠፈው ሃሳብ ይልቅ ሌላ ሲያወራን፤ ካሳየን ተንቀሳቃሽም ሆነ የፎቶ ምስል ጋር ጭራሽ የማይገናኝ ሲቀባጥር መስማት የተለመደ ሆኗል። ይህ ሁሉ ግን ያው ሳንቲም ፍለጋ ለመሆኑ ልብ ማለት ያስፈልጋል። ጭንቅላት አለኝ የሚል ሰው የወያኔውን አፈ ቀላጤ ጌታቸው ረዳንም ሆነ የወያኔውን ቁንጮ ደብረጽዪንን ወሬ ተቀብሎ ማናፈስ አልነበረበትም። ወያኔ በእድሜው እውነት ተናግሮ አያውቅም። ገና ከጅምሩ የራሳቸውን የትግል ጓደኞች ለድርድር ጠርተው አብልተው አጠጥተው በተኙበት ነው ጭፍጭፈው የገደሏቸው። ሰው በተኛበት መግደል ልምድ ስላላቸው ነው የሰሜን እዝንም በተኙበት የጨፈጨፏቸው። ይህ አረመኔ ቡድን ከምድረገጽ መጥፋት አለበት።
    በመጨረሻም ከወያኔ መድፍና የጥይት አረር በመሸሸት ማምለጥ አይቻልም። አንድም ሁለትም ይዞ በመሞት እንጂ። ተሩጦ የት ነው የሚደረሰው? ደግሞስ ወያኔ ምህረት ያረግልኛ ብሎ ማመን እንዴት ይታሰባል? ኢትዮጵያን እናፈርሳታለን የሚለው ወያኔ እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ልብ ገዝቶ ለሰላምስ ድርድር ቁጭ የሚለው? አሜሪካ ወታደራዊው ግጭት ፍሬ አያመጣም የምትለው በጎን እሳት እያቀበለች ነው። ግን የኢትዮጵያ ልጆች አይለው ወያኔን ቢደመስሱት ከአሸናፊው ወገን ጋር ተገልብጣ መቆሟ አይቀሬ ነው። የውጭውንም የውስጡንም ግፊትና መከራ በመቋቋም መሆን ያለበትም ወያኔ ለአንድ ጊዜና ለመጨረሻ ጊዜ መቅበር ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule