• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደሴ በወገን እጅ – መከላከያ እየገፋ ነው!

October 31, 2021 05:18 am by Editor 1 Comment

ደሴን ለመውረር አሰፍስፎ የነበረ አሸባሪው የህወሃት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል

በወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብቶ የነበረ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂም ባለበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው ተሸኝቷል

የደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለሙ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት አልተረዱም

ልዩ መረጃ፤ ከጥቂት ደቂዎች በፊት ጎልጉል እንዳረጋገጠው ደሴን ያረጋጋው መከላከያ ሠራዊት፣ ልዩ ኃይል፣ ሕዝባዊ ሚሊሻና ፋኖ

በርካታ አካባቢዎችን እየተቆጣጠረና በወገን እጅ ሥር እያደረጋቸው ይገኛል። በዚህም ጠላት በከፍተኛ ሁኔታ እየተደመሰሰና እየሸሸ እንደሆነ ለማረጋገጥ ችለናል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ላለቁት ልጆቹ ትህነግን ለመጠየቅ እንዲዘጋጅ አሳስቧል።


በጢጣ በኩል ሰብሮ በመግባት የደሴ ከተማን ለመቆጣጠር የሞከረው አሸባሪው የህወሃት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል።

የመጣውን ኃይልም ደሴ ከተማ ከመግባቱ በፊት ሙሉ በሙሉ ባለበት ማስቀረት መቻሉን በወሎ ግንባር ወራሪውን ኃይል እያጸዱ የሚገኙ የመከላከያና ደህንነት ምንጮች ለኢዜአ ጠቁመዋል።

የደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለመ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት ካለመረዳት የመነጨ እንደሆነ አስታውቀዋል።

በግንባሩ የተሰለፉ የሰራዊት አመራርና አባላትም ወራሪውን ኃይል ለአንዴና መጨረሻ ለማጥፋት አኩሪ ተጋድሎ እየፈጸሙ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

በኩታበር በኩል አሰፍስፎ ደሴን ለመውረር የመጣው ወራሪ ኃይልም ምንም ማድረግ እንዳይችል ተደርጎ መደቆሱን ገልጸዋል።

በወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብተው የነበሩ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂዎችም ባሉበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው መሸኘታቸውን ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።

ደሴና አካባቢዋን ለመውረር ከየአቅጣጫው ተሰባስቦ አሰፍስፎ የነበረውን ኃይልም አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የደሴን ከተማ በወገን እጅ እንዳለች ማስቀጠል መቻሉን ገልጸዋል።

የደሴ ከተማ እና አካባቢው የሽብር ቡድኑን የአፈሳ ወሬ ባለመስማት አካባቢውን ጸንቶ እንዲጠብቅና ለግንባሩ ሰራዊት ሲያደርጉት የነበረውን ደጀንነት እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል።

በግንባሩ ያሉ የሰራዊት አባላት የጥፋት ቡድኑን ማጽዳት ይቀጥላሉ ያሉት ምንጮቻችን በቅርብ ጊዜም ይህኑ የኢትዮጵያ ጠላት የሆነ ወራሪ ኃይልም እስከወዲያኛው የሚሸኙበት ቀን ሩቅ እንዳልሆነ አረጋግጠዋል። (ኢዜአ)

ማሳሰቢያ፤ እስካሁን በታሪካችን አስከሬን አትመን አናውቅም ነበር፤ ሆኖም ትህነግ በሕዝባችን ላይ እያደረሰው ካለው አንጻር ይህንን ፎቶ ማውጣታችን እንዲታወቅ እንፈልጋለን

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Slider Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 31, 2021 09:31 am at 9:31 am

    በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ታሪክ ውስጥ እንደ ወያኔ ያለ ጸላዬ ሰናይ የተጠናወተው ከናዚ ጀርመኖችና ከጣሊያን ወራሪ ሃይል የከፋ ራስ በቀል አረመኔ ገጥሟት አያውቅም። አብረው ቁጭ ብለው በልተው ምግብህና መጠጥህ ውስጥ መርዝ ጨምረው ገለው ሃዘን ላይ ቁጭ ብለው የሃዘን ንፍሮ የሚበሉ ዘግናኝ ፍጡሮች ናቸው። አሁን በደሴና ዙሪያዋ አስቀድመው አሰልጥነውና አስታጥቀው ባሰለፏቸው ሃገር ከሃዲ ሰዎች እየተጠቆሙ ነው ሆቴሎችን አልፎ ተርፎም የታወቁ ሰዎች ቤቶችን ለመደምሰስ የሞከሩት። እነዚህ ሰዎች ከራሳቸው ዘር ውጭ ሌላው ሰው መስሎ አይታያቸውም። ርህራሄ የሚባል ነገር አልተፈጠረባቸውም። ግን አንድ አንድ ሃበሻ አብሮ ከእነርሱ ጋር ሰክሯል። የእነርሱን የፕሮፓጋንዳ ወሬ ተቀብሎ ያናፍሳል። አብሮም ይነፍሳል። የጠ/ሚሩን መንግስት ቅርንጫፍ አልባ እንደ ቀረ ግንድ ይመለምላል። ይህ ሁሉ ግን ለወያኔና ለኦነግ ሸኔ ፈንጠዚያ ነው። የጠ/ሚሩ መንግስት ሴረኞችን አቅፏል፤ ለወያኔ ከውስጥ ሆነው ወሬ የሚያቀብሉትን ዝም ይላል ገለ መሌ መባሉን ከጊዜ ጋር በመረጃ የምንሟገተው ሲሆን አሁን ባለንበት የሞትና የሽረት ሰአት ግን ጠ/ሚሩንና አመራራቸውን የምንነቅፍበት ጊዜ አይመስለኝም። አሁን ሁሉም ነገር ወደ ወያኔ ቢያተኩርና የዚህ እልቂት መቋጫን መፈለጉ ለሃገሪቱና ለህዝቦቿ ደህንነት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። አሁን እንሆ እልፍ ገደልን እልፍ ማረክን እያሉ የሚያወሩና የሚያስወሩ ሙታን ቆጠራቸን በመተው ቆሞ ህዝባችን የሚገድለውንና የሚዘርፈውን መግደል አለባቸው። በዚህ ዙሪያ ላይ በየስፍራው ወደቀ የተባለው አስከሬን ተሰብስቦ ካልተቃጠለ ወይም ካልተቀበረ ሊያስከትል የሚችለው የበሽታ አይነት በጥይት የማንመክተው ይሆናል። አውቃለሁ ሙትን ማቃጠል በሃገራችን የተለመደ አይደለም። ለምሳሌ በጃፓን ከ 90 % በላይ ሙታናቸውን ያቃጥላሉ። ህንድና ከህንድ ተቆርሰው ሃገር የሆኑት እንደ ፓኪስታን ያሉ ሃገሮች ደግሞ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን አስከሬን ያጋያሉ። ሰልጥኛለሁ ከእኔ በላይ ላሳር ነው የሚሉት ምዕራባዊያን ሃገሮችም አሁን አሁን cremation የተለመደ ተግባር ሆኗል። ባጭሩ ሙታን መቀበር ወይም መቃጠል አለባቸው። ያለበለዚያ ቋሚን ወደ ላይኛው ዓለም የሚያሸጋግር በሽታ ያመጣሉ።
    አሁን በደሴ (ወሎ) እየሆነ ያለውን ነገር በእርግጠኝነት የሚያውቅ የለም። የዜናው አውታር ሰበር ብሎ ከለጠፈው ሃሳብ ይልቅ ሌላ ሲያወራን፤ ካሳየን ተንቀሳቃሽም ሆነ የፎቶ ምስል ጋር ጭራሽ የማይገናኝ ሲቀባጥር መስማት የተለመደ ሆኗል። ይህ ሁሉ ግን ያው ሳንቲም ፍለጋ ለመሆኑ ልብ ማለት ያስፈልጋል። ጭንቅላት አለኝ የሚል ሰው የወያኔውን አፈ ቀላጤ ጌታቸው ረዳንም ሆነ የወያኔውን ቁንጮ ደብረጽዪንን ወሬ ተቀብሎ ማናፈስ አልነበረበትም። ወያኔ በእድሜው እውነት ተናግሮ አያውቅም። ገና ከጅምሩ የራሳቸውን የትግል ጓደኞች ለድርድር ጠርተው አብልተው አጠጥተው በተኙበት ነው ጭፍጭፈው የገደሏቸው። ሰው በተኛበት መግደል ልምድ ስላላቸው ነው የሰሜን እዝንም በተኙበት የጨፈጨፏቸው። ይህ አረመኔ ቡድን ከምድረገጽ መጥፋት አለበት።
    በመጨረሻም ከወያኔ መድፍና የጥይት አረር በመሸሸት ማምለጥ አይቻልም። አንድም ሁለትም ይዞ በመሞት እንጂ። ተሩጦ የት ነው የሚደረሰው? ደግሞስ ወያኔ ምህረት ያረግልኛ ብሎ ማመን እንዴት ይታሰባል? ኢትዮጵያን እናፈርሳታለን የሚለው ወያኔ እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ልብ ገዝቶ ለሰላምስ ድርድር ቁጭ የሚለው? አሜሪካ ወታደራዊው ግጭት ፍሬ አያመጣም የምትለው በጎን እሳት እያቀበለች ነው። ግን የኢትዮጵያ ልጆች አይለው ወያኔን ቢደመስሱት ከአሸናፊው ወገን ጋር ተገልብጣ መቆሟ አይቀሬ ነው። የውጭውንም የውስጡንም ግፊትና መከራ በመቋቋም መሆን ያለበትም ወያኔ ለአንድ ጊዜና ለመጨረሻ ጊዜ መቅበር ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule