• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደሴ በወገን እጅ – መከላከያ እየገፋ ነው!

October 31, 2021 05:18 am by Editor 1 Comment

ደሴን ለመውረር አሰፍስፎ የነበረ አሸባሪው የህወሃት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል

በወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብቶ የነበረ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂም ባለበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው ተሸኝቷል

የደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለሙ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት አልተረዱም

ልዩ መረጃ፤ ከጥቂት ደቂዎች በፊት ጎልጉል እንዳረጋገጠው ደሴን ያረጋጋው መከላከያ ሠራዊት፣ ልዩ ኃይል፣ ሕዝባዊ ሚሊሻና ፋኖ

በርካታ አካባቢዎችን እየተቆጣጠረና በወገን እጅ ሥር እያደረጋቸው ይገኛል። በዚህም ጠላት በከፍተኛ ሁኔታ እየተደመሰሰና እየሸሸ እንደሆነ ለማረጋገጥ ችለናል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ላለቁት ልጆቹ ትህነግን ለመጠየቅ እንዲዘጋጅ አሳስቧል።


በጢጣ በኩል ሰብሮ በመግባት የደሴ ከተማን ለመቆጣጠር የሞከረው አሸባሪው የህወሃት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል።

የመጣውን ኃይልም ደሴ ከተማ ከመግባቱ በፊት ሙሉ በሙሉ ባለበት ማስቀረት መቻሉን በወሎ ግንባር ወራሪውን ኃይል እያጸዱ የሚገኙ የመከላከያና ደህንነት ምንጮች ለኢዜአ ጠቁመዋል።

የደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለመ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት ካለመረዳት የመነጨ እንደሆነ አስታውቀዋል።

በግንባሩ የተሰለፉ የሰራዊት አመራርና አባላትም ወራሪውን ኃይል ለአንዴና መጨረሻ ለማጥፋት አኩሪ ተጋድሎ እየፈጸሙ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

በኩታበር በኩል አሰፍስፎ ደሴን ለመውረር የመጣው ወራሪ ኃይልም ምንም ማድረግ እንዳይችል ተደርጎ መደቆሱን ገልጸዋል።

በወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብተው የነበሩ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂዎችም ባሉበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው መሸኘታቸውን ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።

ደሴና አካባቢዋን ለመውረር ከየአቅጣጫው ተሰባስቦ አሰፍስፎ የነበረውን ኃይልም አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የደሴን ከተማ በወገን እጅ እንዳለች ማስቀጠል መቻሉን ገልጸዋል።

የደሴ ከተማ እና አካባቢው የሽብር ቡድኑን የአፈሳ ወሬ ባለመስማት አካባቢውን ጸንቶ እንዲጠብቅና ለግንባሩ ሰራዊት ሲያደርጉት የነበረውን ደጀንነት እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል።

በግንባሩ ያሉ የሰራዊት አባላት የጥፋት ቡድኑን ማጽዳት ይቀጥላሉ ያሉት ምንጮቻችን በቅርብ ጊዜም ይህኑ የኢትዮጵያ ጠላት የሆነ ወራሪ ኃይልም እስከወዲያኛው የሚሸኙበት ቀን ሩቅ እንዳልሆነ አረጋግጠዋል። (ኢዜአ)

ማሳሰቢያ፤ እስካሁን በታሪካችን አስከሬን አትመን አናውቅም ነበር፤ ሆኖም ትህነግ በሕዝባችን ላይ እያደረሰው ካለው አንጻር ይህንን ፎቶ ማውጣታችን እንዲታወቅ እንፈልጋለን

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 31, 2021 09:31 am at 9:31 am

    በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ታሪክ ውስጥ እንደ ወያኔ ያለ ጸላዬ ሰናይ የተጠናወተው ከናዚ ጀርመኖችና ከጣሊያን ወራሪ ሃይል የከፋ ራስ በቀል አረመኔ ገጥሟት አያውቅም። አብረው ቁጭ ብለው በልተው ምግብህና መጠጥህ ውስጥ መርዝ ጨምረው ገለው ሃዘን ላይ ቁጭ ብለው የሃዘን ንፍሮ የሚበሉ ዘግናኝ ፍጡሮች ናቸው። አሁን በደሴና ዙሪያዋ አስቀድመው አሰልጥነውና አስታጥቀው ባሰለፏቸው ሃገር ከሃዲ ሰዎች እየተጠቆሙ ነው ሆቴሎችን አልፎ ተርፎም የታወቁ ሰዎች ቤቶችን ለመደምሰስ የሞከሩት። እነዚህ ሰዎች ከራሳቸው ዘር ውጭ ሌላው ሰው መስሎ አይታያቸውም። ርህራሄ የሚባል ነገር አልተፈጠረባቸውም። ግን አንድ አንድ ሃበሻ አብሮ ከእነርሱ ጋር ሰክሯል። የእነርሱን የፕሮፓጋንዳ ወሬ ተቀብሎ ያናፍሳል። አብሮም ይነፍሳል። የጠ/ሚሩን መንግስት ቅርንጫፍ አልባ እንደ ቀረ ግንድ ይመለምላል። ይህ ሁሉ ግን ለወያኔና ለኦነግ ሸኔ ፈንጠዚያ ነው። የጠ/ሚሩ መንግስት ሴረኞችን አቅፏል፤ ለወያኔ ከውስጥ ሆነው ወሬ የሚያቀብሉትን ዝም ይላል ገለ መሌ መባሉን ከጊዜ ጋር በመረጃ የምንሟገተው ሲሆን አሁን ባለንበት የሞትና የሽረት ሰአት ግን ጠ/ሚሩንና አመራራቸውን የምንነቅፍበት ጊዜ አይመስለኝም። አሁን ሁሉም ነገር ወደ ወያኔ ቢያተኩርና የዚህ እልቂት መቋጫን መፈለጉ ለሃገሪቱና ለህዝቦቿ ደህንነት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። አሁን እንሆ እልፍ ገደልን እልፍ ማረክን እያሉ የሚያወሩና የሚያስወሩ ሙታን ቆጠራቸን በመተው ቆሞ ህዝባችን የሚገድለውንና የሚዘርፈውን መግደል አለባቸው። በዚህ ዙሪያ ላይ በየስፍራው ወደቀ የተባለው አስከሬን ተሰብስቦ ካልተቃጠለ ወይም ካልተቀበረ ሊያስከትል የሚችለው የበሽታ አይነት በጥይት የማንመክተው ይሆናል። አውቃለሁ ሙትን ማቃጠል በሃገራችን የተለመደ አይደለም። ለምሳሌ በጃፓን ከ 90 % በላይ ሙታናቸውን ያቃጥላሉ። ህንድና ከህንድ ተቆርሰው ሃገር የሆኑት እንደ ፓኪስታን ያሉ ሃገሮች ደግሞ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን አስከሬን ያጋያሉ። ሰልጥኛለሁ ከእኔ በላይ ላሳር ነው የሚሉት ምዕራባዊያን ሃገሮችም አሁን አሁን cremation የተለመደ ተግባር ሆኗል። ባጭሩ ሙታን መቀበር ወይም መቃጠል አለባቸው። ያለበለዚያ ቋሚን ወደ ላይኛው ዓለም የሚያሸጋግር በሽታ ያመጣሉ።
    አሁን በደሴ (ወሎ) እየሆነ ያለውን ነገር በእርግጠኝነት የሚያውቅ የለም። የዜናው አውታር ሰበር ብሎ ከለጠፈው ሃሳብ ይልቅ ሌላ ሲያወራን፤ ካሳየን ተንቀሳቃሽም ሆነ የፎቶ ምስል ጋር ጭራሽ የማይገናኝ ሲቀባጥር መስማት የተለመደ ሆኗል። ይህ ሁሉ ግን ያው ሳንቲም ፍለጋ ለመሆኑ ልብ ማለት ያስፈልጋል። ጭንቅላት አለኝ የሚል ሰው የወያኔውን አፈ ቀላጤ ጌታቸው ረዳንም ሆነ የወያኔውን ቁንጮ ደብረጽዪንን ወሬ ተቀብሎ ማናፈስ አልነበረበትም። ወያኔ በእድሜው እውነት ተናግሮ አያውቅም። ገና ከጅምሩ የራሳቸውን የትግል ጓደኞች ለድርድር ጠርተው አብልተው አጠጥተው በተኙበት ነው ጭፍጭፈው የገደሏቸው። ሰው በተኛበት መግደል ልምድ ስላላቸው ነው የሰሜን እዝንም በተኙበት የጨፈጨፏቸው። ይህ አረመኔ ቡድን ከምድረገጽ መጥፋት አለበት።
    በመጨረሻም ከወያኔ መድፍና የጥይት አረር በመሸሸት ማምለጥ አይቻልም። አንድም ሁለትም ይዞ በመሞት እንጂ። ተሩጦ የት ነው የሚደረሰው? ደግሞስ ወያኔ ምህረት ያረግልኛ ብሎ ማመን እንዴት ይታሰባል? ኢትዮጵያን እናፈርሳታለን የሚለው ወያኔ እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ልብ ገዝቶ ለሰላምስ ድርድር ቁጭ የሚለው? አሜሪካ ወታደራዊው ግጭት ፍሬ አያመጣም የምትለው በጎን እሳት እያቀበለች ነው። ግን የኢትዮጵያ ልጆች አይለው ወያኔን ቢደመስሱት ከአሸናፊው ወገን ጋር ተገልብጣ መቆሟ አይቀሬ ነው። የውጭውንም የውስጡንም ግፊትና መከራ በመቋቋም መሆን ያለበትም ወያኔ ለአንድ ጊዜና ለመጨረሻ ጊዜ መቅበር ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule