• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የዛሬዋ ኢትዮጵያ አይደለም የትላንትናውን ትህነግ የዘመነውን ትህነግ ለመቀበል አትችልም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

November 1, 2021 01:56 pm by Editor 1 Comment

* “በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ተሳትፈዋል”

* የ፷፪ ዓመት ሽማግሌ ከትግራይ ለትህነግ ዘምቷል

በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ከአሸባሪው ቡድን ጋር መሳተፋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ። 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። 

በጦርነቱ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ እና የኢትዮጵያውያ ዝርያ የሌላቸው ነጮች እና ጥቁሮች ከአሸባሪው ቡድን ጋር ተሳትፈው መስዋትነት መክፈላቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያረጋገጡት። 

“በወሎ ግምባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ተሳትፈውበታል። የኢትዮጵያ ዝርያ የሌላቸው ሰዎች ተሳትፈው መስዋዕትነት ከፍለዋል። ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ሰው ኢትዮጵያ መጥቶ በደሴ ግምባር ሲሞት ኢትዮጵያዊ የሆነ አካል ኢትዮጵያን ለማዳን ምን ያህል ዝግጁ ነው? የሚለው ለሁላችን የሚተው ነው” በማለት ዐቢይ ለባለሥልጣናቱ አስረድተዋል።

የሕወሀት የሽብር ቡድን የከፈተውን ጦርነት እና ጦርነቱን እየመራበት ያለው ህዝባዊ አካሄድ አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህዝብ ለመከላከያ ሠራዊቱ ያሳየው ድጋፍ የሚበረታታ እንደነበር አስታውሰዋል። 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በቅስቀሳ የመጣውን የህዝብ ኃይል ለማስተናገድ በመንግስት በኩል በቂ ዝግጅት እንዳልነበር በመግለፅ፤ በአሁኑ ሰአትም ከዛ ሁኔታ እርምት ተወስዶ ስትራቴጂካዊ በሆነ መልኩ እየተሰራበት እንደሆነ ጠቁመዋል።

አጠቃላይ ህዝቡ ለሠራዊቱ ያለው ድጋፍ አሁን ካለው በላይ ሊጠናከር ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የገጠመችው ጦርነት ከአንድ ወገን ጋር ብቻ እንዳልሆነ በመረዳት ህዝቡ ዋጋ በመክፈል ያለውን ፍቅር በተግባር ሊገልጽ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ጠ/ሚ/ሩ ሲናገሩ “ለምሳሌ ባለፉት ሦስት አራት ወር ገደማ ትግራይ ክልል ለቅቀን ከወጣን በኋላ በመቶዎች የሚቆጠሩ ውጊያዎችን አካሂደናል። ጦርነት አይደለም፤ ጦርነት ድምር ውጤቱ ነው፤ ውጊያ የሚቀደድ የሚሰፋ ነገር ነው፤ መቀሌን ስንይዝም ሲቀደድ ሲሰፋ ነበር፤ የሆነ ኃይል ይበተናል፣ የሆነ ኃይል ይማረካል፣ የሆነ ኃይል በጀግንነት ይዋጋል፣ መፍረስ መልሶ መደራጀት፣ አንዳንዴ ትጥቅን ጥሎ መሄድ፣ ትጥቅን ሽጦ መሄድ፣ አንዳንዴ ደግሞ ትጥቅ በሌለበት ሁኔታ እጅ በእጅ መዋጋት ሁሉም ባህርዮች ውጊያ አሉት” በማለት የጦርነቱንና የውጊያውን ሁኔታ አስረድተዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘም ከ፲ ቀን በፊት ትህነግ ፈንጂ ደርድሮ በሌላ መንገድ ነበር ሊያጠቃ ቢመጣም መከላከያው እንዳያልፍ የገደበውን ፈንጂ ፲፱ ራሳቸውን ለመስዋዕትነት ያዘጋጁ ወጣቶች እኛ በፈንጂ ላይ ተረማመደን ለመከላከያው መንገድ መጥረግ አለብን ብለው አድርገውታል፤ ራሱን መስዋዕት አድርጎ አገርን ለመታደግ የወሰነ ሕዝብ አለ በማለት አስረድተዋል።

ጦርነት የፖለቲካ እሳቤ ማስጠበቂያ የመጨረሻ መንገድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚ/ሩ፤ ውጊያ በየትኛውም ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል ገልፀው ጦርነቱን ግን ኢትዮጵያ እንደምታሸንፍ አትጠራጠሩ ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሙሉ ንግግር ከዚህ በታች ይገኛል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Slider Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    November 2, 2021 09:31 am at 9:31 am

    ልብ ያላቸው የድሮ ሰዎች ነገር ሲከብድባቸው “የምችለው ስጠኝ ይሉ ነበር”። ጠንቋዪ፤ ባለ ቃልቻው፤ ነብይና ነብይት ነይ ባዪቹ በሚዘላብድባት በዚህች የመከራ ምድር ላይ የሰው እንባና ሞት መቀለጃ ሆኗል። እኔ ጋ እስካልደረሰ የመከራው ወላፈን የላሰውን ቢልስ ደንታ የማይሰጣቸው በየቀኑ ከየስፍራው ከውጭ ሃገር ሰው ለፍቶ በሚልክላቸው ገንዘብ ጮቤ የሚረግጡ፤ አልፎ ተርፎም ከህዝብ ላይ ለ 27 ዓመት ዘርፈው ባጠራቀሙት የደም ሃብት በውስኪ የሚራጩና ከበሮ የሚመቱ በምድሪቱ እየተስተዋሉ ነው። ጀግና አባሮ ገዳይ፤ የሃገር መከታ የሚባለው ወታደርም ያለ ስልት አፈግፍጎ አሁን እንሆ ወያኔ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል የመከራና የዘረፋ ዶፍ በማዝነብ ላይ ይገኛል። ገናም የመከራው ዝናብ ይቀጥላል። ያ ጎርፍ ማንን ጠርጎ ማንን አልፎ እንደሚሄድ ግን ማንም መገመት አይችልም።
    ከወያኔ የተባረረው አሁን ተመልሶ የጦር መሪ ነኝ የሚለው ጻድቃን የተናገረውን ላዳመጠና የጠ/ሚሩን ዲስኩር ለሰማ የሁለቱ የአነጋገር ፈሊጥም ሆነ ድንፋታ ጭራሽ አይገናኝም። ግን ሁለቱም ለድላቸው መሳካት ያቀረቡትን ሃሳብ ለመዘነ የወያኔው ወታደር ጭብጥ መረጃ ያለው ይመስላል። ያው ሁሉም ወያኔ ከድርጅቱ ወጣ ገባ አንድ መሆናቸውን በዚህ ደም አፍሳሽ ወታደር ታያለህ። ዛሬም ስለ አንድ ብሄር የበላይነት፤ ስለ ሚኒሊክ ጨቋኝነት ሲያወራ ላዳመጠው እነዚህ ሰዎች ጨርቅ ያወለቁ እብዶች መሆናቸውን ታያለህ። ምንም አይነት ድርድር፤ ምንም አይነት የሰላም ጥሪ በእነዚህ ሰዎች ልብና ጭንቅላት አይደርስም። አፍርሶ መፍረስ ነው ምኞታቸው። ታዲያ ይህን ምኞታቸውን ማሳካት የሚቻለው በተጣመረ ጉልበት ሆኖ እያለ ሁሉም በየጎራው ማቅራራቱ ፍሬ የለውም። ወያኔ ወደፊት በገፋ ቁጥር ለእልቂት መጋለጡም አይቀሬ ነው። የኦሮሞ ሸኔዎች ከወያኔ ጋር አብሮ ሃተፍ ተፍ ማለት ደግሞ ወያኔ አኝኮ እስኪተፋቸው ነው። ያኔስ በለንደን በአሜሪካ መሪነት ከኦነግ ጋር አብረው አልነበረ የመከሩት። የተመከረው ሌላ አዲስ አበባ ከተገባ በህዋላ የተከወነው ሌላ። የዘር ፓለቲካ የሙታን ፓለቲካ ነው። እንደ ውሻ አናካሽ!
    ጉዳዪ አሁን የሞትና የሽረት ነው። ዳግመኛ ወያኔን ተቀብሎ የሚያስተናግድ ምድር የተረገመ ይሁን። ጥፍራቸው የተነቀለ፤ ቆለጣቸው የፈረሰ፤ በሴትና በወንድ ብልት ያልሆነ ነገር የገባባቸው፤ የሴት መርማሪዎች የሸኑባቸው ኸረ ስንቱ ይባላል። ያ የመከራ ዘመን ይረሳል? ወያኔ በክህደት የተካነ የተናገረውን የሚረሳ ክፉ መናፍስት ነው። ጻድቃን ሲናገር እኛ የሰሜን ጦርን አላጠቃንም ሲል በፊት የተናገረውን ዘንግቶ ነው። አይ ውስልትና። ግን ከእብድ ጋር ግርግር አይመችም። መተው ነገሬን ከተተው ይላሉ አበው።
    ዶ/ር አብይ አዲስ አበባ ላይ ሆኖ በካሜራ ፊት ከሚደሰኩር ነገሩን በዝግ ማድረግም በቻለ ነበር። ግን የዝግ ስብሰባ የሚያደርገው ምንም ሚስጢራዊ ነገር የለውም። ባይሆን እንኳን የተጨነቁትን ሰዎች ፊት አናይም ነበር። የድሮን አጠቃቀም ሰራዊቱ ታጥቋል፤ እንዲህም እንዲያም እናረጋለን እያሉ ሲለፉ የነበሩት ለምን የወያኔ አመራሮችን ለመግደል አልተቻለም። መንጋውን ለመበተን አመራርን መግደል ነው። ሌላው ሁሉ ከመንገድ ላይ እየተጫነ እቃ ለመዝረፍና ሃብታም ለመሆን የሚመጣ ጀሌና አንድ ተኩሶ የሚፈረጥጥ ነው። ግን ይህን የመሰለ ጥቃት ለማድረስ ደግሞ የስለላና የወታደራዊ ቅንጅት አስፈላጊ ነው። ይመስለኛል በስለላውም በወታደራዊ ቅንጅቱም ወያኔ የበላይነቱን ይዟል። የወያኔ ጄኔራሎች ልብ አብጦ በየምክንያቱ መጣንባችሁ ይህን እንይዛለን እቤታችሁ ታሸጉ ያሉትም ለዚሁ ነው።
    በመጨረሻ ኢትዮጵያ የፈጣሪ ቃል ኪዳን አላት፤ የሰው ጸሎት አሳልፎ ለመከራ አይሰጠንም። የጾምና የጸሎት ጊዜ አውጅ የምትሉ ያለፈውን ታሪክ ከአሁኑ ታሪክ ጋር ብታመሳክሩ ፈጣሪ በእኛ ጉዳይ የገባበት አንድም ዘመንና ጊዜ የለም። የተደበቀው ማስታወሻ በዶ/ር ሀራልድ ናይስትሮም ተጽፎ በዶ/ር ገበየሁ ተፈሪና ደሳለኝ ዓለሙ የተተረጎመው (With St. George on the death ride) የሚነግረን ፈጣሪን ያመለክንና ያስቀደምን መስሎን ሰው ያስጨረስንበትን ታሪክ ነው። አሁንም አትዘላብድ። የእኛ ችግር ራሳችን የፈጠርነው፤ በራሳችን የሚፈታ እንጂ ፈጣሪ እሳት እንደሚያቃጥል አሳውቆን እጃችን እሳት ውስጥ ከተን ለምን ተበላን ወይም ና አውጣን ማለቱ በፈጣሪ ላይ ማሾፍ ነው። ግን የሞራል ድጋፍ ሊሆን ይችላል። የቃል ኪዳን ሃገር ናት እያሉ መመጻደቁ። ሶሪያ፤ ኢራቅ፤ የመን፤ አፍጋኒስታን፤ ዪጎዝላቪያ ወዘተ ፈጣሪ አይወዳቸውም እንዴ? የእኛ ሃገር ከማንም ከምንም አትለይም። በራስ አስቦ ለራስና ለሌሎች ሰዎች መብትና ደህንነት ቆሞ ማለፍ እሱ ነው ከፈጣሪ ጋር የሚያስማማ። ሌላው ሁሉ የመሰንበቻ ወይም የመኖሪያ ብልሃት ፍለጋ ነው። ይህ ፍልሚያ የሚያባራበትንና የት ቦታ ላይ እንደሚቆም አሁን ላይ ሆኖ ማሳየት የሚችል የለም። ድል ቀናን ያሉ ሲደመሰሱ፤ አለቀልን ብለው ዋይታ ሊያሰሙ ቀናት የቀራቸው ተነቃቅተው ጠላትን ሲያበራዪና ድል በድል ሲሆኑ በታሪክ አይተናል። ግን ወያኔ ለሃገራችን የጨለማ ዘመን የተመኘ፤ ሲኦል ድረስ ወርዶ ለማፈራረስ የተዘጋጀ በመሆኑ የወያኔ ሞት ለምድሪቱ ከሞላ ጎደል ሰላምን ሊያሰፍን ይችላል። ጠብቀን እንይ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule