አሸባሪው ትህነግ የአሜሪካ ተራድኦ ደርጅት መጋዘኖችን እንደዘረፈ በኢትዮጵያ የድርጅቱ ሚሽን ዳይሬክተር ሾን ጆንስ ተናገሩ። የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) የኢትዮጵያ ሚሽን ዳይሬክተር ሾን ጆንስ ከኢቲቪው ሰለሞን ዳኜ ጋር በነበራቸው ቆይታ ትህነግ ሁኔታውን ያለአግባብ እየተጠቀመበት እንደሆነ እናምናለን ብለዋል። ከተረጂዎች ላይ እርዳታን በሃይል እየነጠቀ እንደሆነ ይሰማናል ያሉት ዳይሬከተሩ እርግጠኛ ሆነን መናገር የምንችለው ግን የአሸባሪው ትህነግ ቡድን አባላት ሰርገው በገቡባቸው አካባቢዎች ሁሉ ያሉትን የእርዳታ መጋዘኖቻችንን ዘርፈዋል፤ ይህ የምናውቀው ሀቅ ነው ሲሉ ገልጸዋል። አሁን በግልጽ የምናውቀው ነገር የትህነግ ወታደሮች በገቡባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች ሁሉ የእርዳታ መጋዘኖችን ዘርፈዋል፣ መኪኖችን ሰርቀዋል በየመንደሮቹ ብዙ ውድመትን … [Read more...] about የአሜሪካ ተራድኦ ደርጅት (USAID) መጋዘኖች በአሸባሪው ትህነግ መዘረፋቸው ተገለጸ
tplf terrorist
በትህነግ ሽብር ምክንያት ግማሸ ሚሊዮን ተፈናቅለዋል
4 ሚሊዮን ዜጎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ናቸው የህወሓት የሽብር ቡድን በሀይል በወረራቸው አካባቢዎች ግማሸ ሚሊየን ዜጎች ሲፋናቀሉ 4 ሚሊየን የሚደርሱት ደግሞ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ገለጹ። ኢብኮ እንደዘገበው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር ከተባበሩት መንግስታት የህፃናት መርጃ ማዕከል የኢትዮጵያ ሃላፊ አዴል ከድር ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ውይይት አድርገዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ የህውሓት የሽብር ቡድን ወረራ በፈፀመባቸው በሰሜንና ደቡብ ጎንደር ዞኖች እንዲሁም ዋግኸምራና ሰሜን ወሎ ዞኖች ግማሽ ሚሊዮን ዜጎች ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን 4 ሚሊዮን ደግሞ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ብለዋል። የሽብር ቡድኑ ሰርጎ በገባባቸው አካባቢዎች ማህበራዊ ተቋማት በተለይም ትምህርት ቤቶች እና ጤና ተቋማትን … [Read more...] about በትህነግ ሽብር ምክንያት ግማሸ ሚሊዮን ተፈናቅለዋል
ኬኒያ፤ ትህነግ አሸባሪ መባሉ በፓርላማው ሊነሳለት ይገባል አለች
ሐሙስ ዕለት የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በመከረበት ወቅት የኬኒያው ተወካይ ትህነግ አሸባሪ መባሉ ሊነሳለት ይገባል አሉ። ኢስቶኒያ፣ ፈረንሳይ፣ አየርላንድ፣ ኖርዌይ፣ ዩናይትድ ኪንግደምና አሜሪካ በጠሩት በዚህ ስብሰባ ላይ የመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ጸኃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ንግግር አድርገው ነበር። ዋና ጸሃፊውም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ያለው ግጭት ሊቆም እንደሚገባው በመጠቆም ንፁሀን እየተጎዱ ስለሆነ ሰብዓዊ ዕርዳታ ሊያገኙ የሚገባቸው ምቹ ሁኔታ ባለመፈጠሩ እንዳላገኙ አስረድተዋል። ከዋና ጸሃፊው ንግግር ቀጥሎ የስብሰባው ጠሪዎች በተከታታይ ተናግረዋል። እንቆምለታለን የሚሉትን ዴሞክራሲ በገሃድ መቀመቅ በመክተት ከኢስቶኒያ እስከ ሜክሲኮ ያሉት አገራት በአሜሪካና አውሮጳ የታዘዙትን እንደ በቀቀን በመድገም ሎሌነታቸውን በዓለምአቀፍ መድረክ … [Read more...] about ኬኒያ፤ ትህነግ አሸባሪ መባሉ በፓርላማው ሊነሳለት ይገባል አለች
በመከላከያ ውስጥ ለትህነግ ሲሰልሉ የነበሩ ጽኑ እስራት ቅጣት ተላለፈባቸው
ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባላቸው የሰራዊት አባላት ላይ ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት የሚደርስ የፅኑ እስራት ውሳኔ ተላለፈ። የደቡብ ዕዝ ቀዳማዊ ወታደራዊ ፍርድ ቤት በተለያዩ ወንጀሎች ተሳትፎ በነበራችውና ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባላቸው የሰራዊት አባላት ላይ ከ8 ዓመት እስከ 18 ዓመት በሚደርስ የፅኑ እስራት ውሳኔ ማስተላለፉ ተገለፀ። ነሐሴ 20 ቀን 2013 ዓ.ም በዕዙ ጠቅላይ መምሪያ በዋለው ችሎት የተሰየመው የዳኞች ምድብ 8 የክስ መዝገቦችን መርምሮ ነው ውሳኔ የሰጠው። በዚህ መሰረት፣ በ1ኛ መዝገብ እነ ኮሎኔል ካህሱ ሀብቱ ፀልይ፣ ኮሎኔል ሀጎስ አሰፋ ወልደንጉሴ እና ሌተናል ኮሎኔል ሀይላይ ገብሩ ገብረተክላይ በ2ኛ መዝገብ ሻምበል ባሻ ክፍሌ ፍስሃ በ3ኛ መዝገብ ኮሎኔል ክፍሌ ፍስሃ በ4ኛ መዝገብ ሃምሳ አለቃ … [Read more...] about በመከላከያ ውስጥ ለትህነግ ሲሰልሉ የነበሩ ጽኑ እስራት ቅጣት ተላለፈባቸው
ከትህነግ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ 1,642 ሰዎች ተያዙ
በ1,616 የንግድ ድርጅቶች ላይ ዕርምጃ መወሰዱን ፖሊስ አስታውቋል ከአሸባሪው ትህነግ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 1,642 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ጄነራል ዘላለም መንግሥቴ እንደገለጹት፣ ከትህነግ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ ሰዎችን በማደን በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ እየተደረጉ ናቸው። እስካሁን ድረስ በተካሄደው የተቀናጀ ምርመራ ከትህነግ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 1,642 ሰዎች፣ በተለያዩ አካባቢዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነ አስታውቀዋል። ከተጠረጠሩት ሰዎች በተጨማሪ ለትህነግ ቡድን ሕገወጥ ተልዕኮ መጠቀሚያ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ የንግድ ድርጅቶች ተዘግተው ምርምራ በመካሄድ ላይ እንደሆነ … [Read more...] about ከትህነግ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ 1,642 ሰዎች ተያዙ
“የጸጥታው ም/ቤት በተደጋገሚ ቀጠሮ የሚይዘው ቻርተሩን በመጣስ ነው”
የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክርቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በተደጋጋሚ ለመምከር ቀጠሮ የሚይዘውና ስብሰባ የሚቀመጠው የመተዳደሪያ ቻርተሩን በሚፃረር መልኩ የምዕራባውያንን ፍላጎት ለማስፈፀም እንደሆነ የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የህግ መምህር አቶ ፀጋዬ ደመቀ አስታወቁ፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክርቤት የትግራይን ጉዳይ ለማየት የጠራውን ስብሰባ አስመልክተው መምህር ፀጋዬ ደመቀ በተለይም ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ ስሙ እንደሚያመላካተው የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክርቤት ስብሰባ ሊጠራ እና ሊመክር የሚችለው የዓለምን ጸጥታና ደህንነት ችግር ላይ የሚጥል ጉዳዮች ላይ ነው፡፡ ምክር ቤቱ በአገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት እንደማያችል በቻርተሩ ላይ በግልጽ ተቀምጣል፡፡ ለዓለም አቀፍ የፀጥታ ስጋት ተብሎ ሊወሰድ የሚችለው ደግሞ በዋነኝነት በሁለት አገራት መካከል … [Read more...] about “የጸጥታው ም/ቤት በተደጋገሚ ቀጠሮ የሚይዘው ቻርተሩን በመጣስ ነው”
ከትህነግ ጋር በመሆን በአባይ ግድብ ላይ ጥቃት ሊያደርሱ የነበሩ ተደመሰሱ
በህዳሴ ግድብ አካባቢ ሰርገው በመግባት ሽብር ለመፍጠር ያሰቡ ቡድኖች ላይ የተወሰደው ወታደራዊ እርምጃ የማያዳግምና ለቀጣይ ትምህርት የሰጠ እንደነበር ሌተና ጀነራል አስራት ዴኔሮ ገለፁ። መንግስት ያቀረበላቸውን የሰላም ጥሪ ያልተቀበሉ የጉምዝ ታጣቂዎችን ሽብርተኛው ህወሓት በሱዳን አሰልጥኖና አስታጥቆ በአልመሃል አቅጣጫ ጥቃት ለማድረስና የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ሙከራ አድርጎ እንደነበር የመተከል ዞን የተቀናጀ ግብረ ሀይል ኮማንድ ፖስት ዋና ሰብሳቢ ሌተናል ጄኔራል አስራት ዴኔሮ ገልፀዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊትና በቀጣናው የተሰማሩ የክልል ልዩ ሀይሎች ለተከታታይ ሶስት ቀናት በአሸባሪው ተላላኪዎች ላይ በወሰዱት እርምጃ ሀገር እና ህዝብን የሚያኮራ ጀብዱ መፈፀማቸውን ተናግረዋል። በሽፍቶቹ ላይ በተወሰደው የማያዳግም እርምጃ የሰራዊቱ ጀግንነትና ፅናት ጎልቶ … [Read more...] about ከትህነግ ጋር በመሆን በአባይ ግድብ ላይ ጥቃት ሊያደርሱ የነበሩ ተደመሰሱ
ወደ ኮምቦልቻ ሊገባ የነበረ 49 ሺህ 300 የአሜሪካ ዶላር ተያዘ
በኮምቦልቻ ከተማ በወሎ ዩኒቨርሲቲ ኬላ ኮድ3 የሰሌዳ ቁጥር 89654 የሆነ መኪና መነሻውን አዲስ አበባ አድርጎ ወደ ኮምቦልቻ ሊገባ ሲል በብሔራዊ ደኅንነት፣ በፓሊስ እና ኬላ በሚጠብቁ ወጣቶች ትብብር በቁጥጥር ሥር መዋሉን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ገልጿል። የጽ/ቤቱ የታክቲክና ወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ኮማንደር አሊ ለአሚኮ እንደገለፁት ተጠርጣሪው ከምሽቱ 2:40 ሰዓት ላይ አሽከርካሪ በኬላው ላይ በነበረ ፍተሻ ከነዶላሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ወጣቶች በኬላ ፍተሻ እያደረጉት ያለው አስተዋጽኦ የሚበረታታ መሆኑን የገለጹት ኮማንደር አሊ ወጣቶች እየሠሩ ያሉትን አካባቢን በንቃት የመከታተል ተግባር አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። በኬላ ጥበቃ ላይ አሚኮ ያነጋገረው በጎ ፈቃደኛ ወጣት ሐሰን እንድሪስ አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ቡድን ለመቅበር በግንባር … [Read more...] about ወደ ኮምቦልቻ ሊገባ የነበረ 49 ሺህ 300 የአሜሪካ ዶላር ተያዘ
በአሸባሪው ቁንጮ ፃድቃን ገ/ትንሣይ የሚመራው የጠላት ኃይል ድባቅ ተመታ
በአሸባሪው ቁንጮ ፃድቃን ገ/ትንሣይ የሚመራው የጠላት ኃይል በሰሜን ወሎ ግንባር በተሰማራው የመከላከያ ሠራዊት መመታቱ ተገለጸ፡፡ ዓርሚ ሁለት የሚባልና በከሀዲው ሜ/ጄ/ል ዮሀንስ፣ በምክትሉ ከሀዲው ማዕሾ በየነ እና ከሀዲው ከበደ ፍቃዱ እንዲሁም በሜካናይዝድ አዛዡ ከሀዲው ኮ/ል ገ/ስላሴ የተመራው ከፍተኛ ቁጥር ያለው የጠላት ሀይል ድባቅ መመታቱ ተገልጿል፡፡ በግንባሩ የተሰማሩ ሁለት ክ/ጦር አዛዦ እንደተናገሩት፣ መንግስት የተናጠል የተኩሥ አቁም እርምጃውን ካነሳ በኋላ ከበላይ በተሠጣቸው ትዕዛዝ መሠረት ጋሸናን ዋና ማዕከል በማድረግ ከዋድላ እስከ ላልይበላ መስመር ላይ የነበረውን የአሸባሪውን ሀይል መደምሠሳቸውን አረጋግጠዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ጠላት በጀግኖቹ የሠራዊት አባላት፣ ልዩ ሀይል እንዲሁም የሚሊሻ አባላትና የአካባቢው አርሶ አደር ከበባ ውስጥ ሆኖ ይገኛል ነው … [Read more...] about በአሸባሪው ቁንጮ ፃድቃን ገ/ትንሣይ የሚመራው የጠላት ኃይል ድባቅ ተመታ
መርካቶ አካባቢ ለሽብር ተግባር ሊውል የነበረ ከ10 ሺህ በላይ ገጀራ ተያዘ
ለሽብር ተግባር ሊውል የነበረ ከ10ሺ በላይ ገጀራ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ እንደሆነ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የመርካቶ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታወቀ፡፡ በትላንትናው እለት ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ ከማህበረሰቡ የተሰጠውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ መርካቶ ውስጥ ጣና የገበያ ማዕከል ጎን በሚገኝ አድማስ ህንፃ ውስጥ፤ አዲሱን የጦር መሳሪያ ቁጥጥር አዋጅ በሚፃረር መልኩ ተከማችቶ የተገኘው ከ10ሺ በላይ ገጀራ በቁጥጥር ስር በማዋል ጠቅላላ ምርመራ እያካሄደበት እንደሆነ የመርካቶ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ሃላፊ ምክትል ኢኒስፔክተር ብርሃኑ አለሙ ተናግረዋል፡፡ የጦር መሳሪያውን ክምችት በመጠቆም ረገድ የህብረተሰቡ ትብብር ከፍተኛ ነበር ያሉት ምክትል ኢኒስፔክተር ብርሃኑ የብሄራዊ ደህንነት ባለሙያዎችና የፖሊስ አባሎቻችንም ድርሻም የጎላ እንደነበር … [Read more...] about መርካቶ አካባቢ ለሽብር ተግባር ሊውል የነበረ ከ10 ሺህ በላይ ገጀራ ተያዘ