• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ምዕራባውያን መንግሥታት ዐቢይን በእነርሱ ቁጥጥር ሥር ማዋል ባለመቻላቸው ቀጠናውን ለማተራመስ እየሰሩ ነው” – ሎውረንስ ፍሪማን

November 29, 2021 10:50 am by Editor Leave a Comment

ምዕራባውያንና አሜሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን በእነርሱ ይሁንታና ቁጥጥር ስር ማዋል ባለመቻላቸው፣ ኢትዮጵያንም ሆነ ቀጠናውን ማተራመስን መምረጣቸውን የአፍሪካ ፖለቲካ እና ምጣኔ ሀብት ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ሎረንስ ፍሪማን ተናገሩ።

አሜሪካ ዜጎችን ውጡ እያለች በምትወተውትበት ሰዓት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ሎረንስ ፍሪማን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት የአሜሪካና የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን በኢትዮጵያ ላይ በውሸት ላይ የተመሰረተ የስነ-ልቦና ጦርነት ከፍተዋል፡፡

ይህንን የሚያደርጉት በሚስ-ኢንፎርሜሽን ሳይሆን ሆን ብለው፣ አቅደው ተከታዮቻቸውን ዲስ-ኢንፎርም ለማድረግ  በማሰብ ነው፡፡

ምዕራባውያንና አሜሪካ የሐሰት መረጃ የሚያሰራጩት ኢትዮጵያውያን በመሪያቸው አማካይነት የተደፈረውን ሉዓላዊነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ እየሰሩት ያለውን ስራ የፖለቲካ ጦርነት በማካሄድ ለማዳከም ነው ብለዋል።

በባይደን አስተዳደር ውስጥ ለረጅም ግዜ ከህወሓት ጋር ግንኙነት የነበራቸውና አገሪቱን በእነሱ ቁጥጥር ስር አድርገው የነበሩ ሰዎች መኖራቸውን የገለጹት ፍሪማን በኢትዮጵያ ላይ የዘመቱትም ይህን የበላይነታቸውን ስላጡና ወደነበረበት ለመመለስ ስለሚፈልጉ ነው ብለዋል።

የአሜሪካ መንግስትም፣ ኮንግረሱም፣ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱም በኢትዮጵያ ያለውን ተጨባጭ ማመን አይፈልጉም፣ ዕውነታውን መጋፈጥም አይፈልግም ነው ያሉት፡፡ (ኢዜአ)

ምሁሩ በትዊተር ገጻቸው ደግሞ ይህንን ብለዋል፤

ከ30 ዓመታት በላይ የአፍሪካን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ በመተንተን የማታወቁት አሜሪካዊው የአፍሪካ ፖሊሲ ተመራማሪ ሎውረንስ ፍሪማን አዲስ አበባ ገብተዋል።

ሎውረንስ ፍሪማን አዲስ አበባ መግባታቸውን ተከትሎ በአዲስ አበባ ስላለው ሁኔታ በትዊተር ገፃቸው ባሰራጩት መልዕክት፥ “መዋሸታችሁን አቁሙ፤ እዚህ ሁሉም ነገር ሰላም ነው፤ አፍጋኒስታን እዚህ የለችም” ብለዋል።

የኢኮኖሚ ተንታኝ እና ተመራማሪው የአሜሪካ መንግስት እና ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ላይ ከከፈቱት የስነልቦና ጦርነት በቀር ሁሉም ነገር አዲስ አበባ ውስጥ የተረጋጋ ነው ብለዋል።

“ባርና ሬስቶራንቶች በምሽትም ጭምር ክፍት ናቸው፤ ሆቴሎችም ስራ ላይ ናቸው” ያሉት ፍሪማን “ከአሜሪካ ወደ አዲስ አበባ የመጣሁበት አውሮፕላን መቀመጫዎች በመንገደኞች ለመሙላት የተቃረቡ እንደሆነ ታዝቢያለሁ” ሲሉ ፅፈዋል።

ፍሪማን ቦሌ ኤርፖርት ሲደርሱ ሁሉም ነገር እንደሁል ጊዜው ሰላማዊ እና የተረጋጋ እንደነበር የተናገሩ ሲሆን “መዋሸታችሁን አቁሙ በተሳሳተ መረጃ ማደናገራችሁን አቁሙ፤ የስርዓተ መንግስት ለውጥም እዚህ አያስፈልግም ” ብለዋል። (ሸገር ኤፍ ኤም 102.1)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist, usa

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule