• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ምዕራባውያን መንግሥታት ዐቢይን በእነርሱ ቁጥጥር ሥር ማዋል ባለመቻላቸው ቀጠናውን ለማተራመስ እየሰሩ ነው” – ሎውረንስ ፍሪማን

November 29, 2021 10:50 am by Editor Leave a Comment

ምዕራባውያንና አሜሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን በእነርሱ ይሁንታና ቁጥጥር ስር ማዋል ባለመቻላቸው፣ ኢትዮጵያንም ሆነ ቀጠናውን ማተራመስን መምረጣቸውን የአፍሪካ ፖለቲካ እና ምጣኔ ሀብት ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ሎረንስ ፍሪማን ተናገሩ።

አሜሪካ ዜጎችን ውጡ እያለች በምትወተውትበት ሰዓት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ሎረንስ ፍሪማን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት የአሜሪካና የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን በኢትዮጵያ ላይ በውሸት ላይ የተመሰረተ የስነ-ልቦና ጦርነት ከፍተዋል፡፡

ይህንን የሚያደርጉት በሚስ-ኢንፎርሜሽን ሳይሆን ሆን ብለው፣ አቅደው ተከታዮቻቸውን ዲስ-ኢንፎርም ለማድረግ  በማሰብ ነው፡፡

ምዕራባውያንና አሜሪካ የሐሰት መረጃ የሚያሰራጩት ኢትዮጵያውያን በመሪያቸው አማካይነት የተደፈረውን ሉዓላዊነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ እየሰሩት ያለውን ስራ የፖለቲካ ጦርነት በማካሄድ ለማዳከም ነው ብለዋል።

በባይደን አስተዳደር ውስጥ ለረጅም ግዜ ከህወሓት ጋር ግንኙነት የነበራቸውና አገሪቱን በእነሱ ቁጥጥር ስር አድርገው የነበሩ ሰዎች መኖራቸውን የገለጹት ፍሪማን በኢትዮጵያ ላይ የዘመቱትም ይህን የበላይነታቸውን ስላጡና ወደነበረበት ለመመለስ ስለሚፈልጉ ነው ብለዋል።

የአሜሪካ መንግስትም፣ ኮንግረሱም፣ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱም በኢትዮጵያ ያለውን ተጨባጭ ማመን አይፈልጉም፣ ዕውነታውን መጋፈጥም አይፈልግም ነው ያሉት፡፡ (ኢዜአ)

ምሁሩ በትዊተር ገጻቸው ደግሞ ይህንን ብለዋል፤

ከ30 ዓመታት በላይ የአፍሪካን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ በመተንተን የማታወቁት አሜሪካዊው የአፍሪካ ፖሊሲ ተመራማሪ ሎውረንስ ፍሪማን አዲስ አበባ ገብተዋል።

ሎውረንስ ፍሪማን አዲስ አበባ መግባታቸውን ተከትሎ በአዲስ አበባ ስላለው ሁኔታ በትዊተር ገፃቸው ባሰራጩት መልዕክት፥ “መዋሸታችሁን አቁሙ፤ እዚህ ሁሉም ነገር ሰላም ነው፤ አፍጋኒስታን እዚህ የለችም” ብለዋል።

የኢኮኖሚ ተንታኝ እና ተመራማሪው የአሜሪካ መንግስት እና ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ላይ ከከፈቱት የስነልቦና ጦርነት በቀር ሁሉም ነገር አዲስ አበባ ውስጥ የተረጋጋ ነው ብለዋል።

“ባርና ሬስቶራንቶች በምሽትም ጭምር ክፍት ናቸው፤ ሆቴሎችም ስራ ላይ ናቸው” ያሉት ፍሪማን “ከአሜሪካ ወደ አዲስ አበባ የመጣሁበት አውሮፕላን መቀመጫዎች በመንገደኞች ለመሙላት የተቃረቡ እንደሆነ ታዝቢያለሁ” ሲሉ ፅፈዋል።

ፍሪማን ቦሌ ኤርፖርት ሲደርሱ ሁሉም ነገር እንደሁል ጊዜው ሰላማዊ እና የተረጋጋ እንደነበር የተናገሩ ሲሆን “መዋሸታችሁን አቁሙ በተሳሳተ መረጃ ማደናገራችሁን አቁሙ፤ የስርዓተ መንግስት ለውጥም እዚህ አያስፈልግም ” ብለዋል። (ሸገር ኤፍ ኤም 102.1)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist, usa

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule