• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ምዕራባውያን መንግሥታት ዐቢይን በእነርሱ ቁጥጥር ሥር ማዋል ባለመቻላቸው ቀጠናውን ለማተራመስ እየሰሩ ነው” – ሎውረንስ ፍሪማን

November 29, 2021 10:50 am by Editor Leave a Comment

ምዕራባውያንና አሜሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን በእነርሱ ይሁንታና ቁጥጥር ስር ማዋል ባለመቻላቸው፣ ኢትዮጵያንም ሆነ ቀጠናውን ማተራመስን መምረጣቸውን የአፍሪካ ፖለቲካ እና ምጣኔ ሀብት ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ሎረንስ ፍሪማን ተናገሩ።

አሜሪካ ዜጎችን ውጡ እያለች በምትወተውትበት ሰዓት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ሎረንስ ፍሪማን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት የአሜሪካና የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን በኢትዮጵያ ላይ በውሸት ላይ የተመሰረተ የስነ-ልቦና ጦርነት ከፍተዋል፡፡

ይህንን የሚያደርጉት በሚስ-ኢንፎርሜሽን ሳይሆን ሆን ብለው፣ አቅደው ተከታዮቻቸውን ዲስ-ኢንፎርም ለማድረግ  በማሰብ ነው፡፡

ምዕራባውያንና አሜሪካ የሐሰት መረጃ የሚያሰራጩት ኢትዮጵያውያን በመሪያቸው አማካይነት የተደፈረውን ሉዓላዊነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ እየሰሩት ያለውን ስራ የፖለቲካ ጦርነት በማካሄድ ለማዳከም ነው ብለዋል።

በባይደን አስተዳደር ውስጥ ለረጅም ግዜ ከህወሓት ጋር ግንኙነት የነበራቸውና አገሪቱን በእነሱ ቁጥጥር ስር አድርገው የነበሩ ሰዎች መኖራቸውን የገለጹት ፍሪማን በኢትዮጵያ ላይ የዘመቱትም ይህን የበላይነታቸውን ስላጡና ወደነበረበት ለመመለስ ስለሚፈልጉ ነው ብለዋል።

የአሜሪካ መንግስትም፣ ኮንግረሱም፣ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱም በኢትዮጵያ ያለውን ተጨባጭ ማመን አይፈልጉም፣ ዕውነታውን መጋፈጥም አይፈልግም ነው ያሉት፡፡ (ኢዜአ)

ምሁሩ በትዊተር ገጻቸው ደግሞ ይህንን ብለዋል፤

ከ30 ዓመታት በላይ የአፍሪካን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ በመተንተን የማታወቁት አሜሪካዊው የአፍሪካ ፖሊሲ ተመራማሪ ሎውረንስ ፍሪማን አዲስ አበባ ገብተዋል።

ሎውረንስ ፍሪማን አዲስ አበባ መግባታቸውን ተከትሎ በአዲስ አበባ ስላለው ሁኔታ በትዊተር ገፃቸው ባሰራጩት መልዕክት፥ “መዋሸታችሁን አቁሙ፤ እዚህ ሁሉም ነገር ሰላም ነው፤ አፍጋኒስታን እዚህ የለችም” ብለዋል።

የኢኮኖሚ ተንታኝ እና ተመራማሪው የአሜሪካ መንግስት እና ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ላይ ከከፈቱት የስነልቦና ጦርነት በቀር ሁሉም ነገር አዲስ አበባ ውስጥ የተረጋጋ ነው ብለዋል።

“ባርና ሬስቶራንቶች በምሽትም ጭምር ክፍት ናቸው፤ ሆቴሎችም ስራ ላይ ናቸው” ያሉት ፍሪማን “ከአሜሪካ ወደ አዲስ አበባ የመጣሁበት አውሮፕላን መቀመጫዎች በመንገደኞች ለመሙላት የተቃረቡ እንደሆነ ታዝቢያለሁ” ሲሉ ፅፈዋል።

ፍሪማን ቦሌ ኤርፖርት ሲደርሱ ሁሉም ነገር እንደሁል ጊዜው ሰላማዊ እና የተረጋጋ እንደነበር የተናገሩ ሲሆን “መዋሸታችሁን አቁሙ በተሳሳተ መረጃ ማደናገራችሁን አቁሙ፤ የስርዓተ መንግስት ለውጥም እዚህ አያስፈልግም ” ብለዋል። (ሸገር ኤፍ ኤም 102.1)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist, usa

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule