• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በ2 ቀናት በተካሄደ ኦፕሬሽን 12 የትህነግ ከፍተኛ የጦር አመራሮች ተደምስሰዋል

November 24, 2021 01:42 pm by Editor 1 Comment

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ዛሬ ምሽት በሰጠው መግለጫ ተደመሰሱ ካላቸው ውስጥ በፌዴራል መንግሥት በሀገር ክህደት ወንጀል ሲፈለጉ የነበሩ ጄነራሎችና ኮሎኔሎች ይገኙበታል።

በመግለጫው ላይ ተደመሰሱ የተባሉት ጄነራሎችና ኮሎኔሎች ስም አልተገለፀም።

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ በሰጡት መግለጫ ይህን ነው ያሉት፦

“ባለፉት 2 ቀናት በባቲ ግንባር በተደረገ ልዩ ኦፕሬሽን 6 የአርሚና እና የኮር ከፍተኛ አመራሮቹ ተደምስሰዋል። እነዚህ አመራሮች በፌዴራል መንግሥት በሀገር ክህደት ወንጀል ሲፈጉ የነበሩ ከሃዲ ጄነራሎች እና ኮሎኔሎች ናቸው።

በተጨማሪ በከሚሴ ግንባር በተለያዩ ቦታዎች በተደረጉ ልዩ ኦፕሬሽኖች የጠላትን ግንባር ጦር ሲመሩ የነበሩ 6 ከሃዲ ከፍተኛ የጦር አመራሮች ከነጠባቂዎቻቸው ተደምስሰዋል።

በዛሬው ዕለት በባቲ ግንባር በተደረገው ከፍተኛ የማጥቃት እርምጃ ቀደም ሲል ከነበሩት ጥቃቶች ተርፎ ለዳግም ማጥቃት ተዘጋጅቶ የነበረው የጠላት ኃይል የተደመሰሰ ሲሆን እግሬ አውጪኝ ብሎ ወደ ኋላ እየፈረጠጠ ያለውን ጠላት እግር በእግር የወገን ኃይል እየተከተለ እያፀዳው እየገሰገሰ ይገኛል።

በሌሎች ግንባሮችም የወገን ጦር በሰነዘረው ከፍተኛ ማጥቃት ጠላት በከፍተኛ ደረጃ እየተመታ ይገኛል።

በዚሁ አጋጣሚ የወገንን ክንድ መቋቋም አቅቶት በተናጠል እና በቡድን እየሸሸ የሚገኘውን የጠላት ኃይል ዘረፋ እንዳይፈፅም እና ንብረት እንዳያወድም ህብረተሰቡ ተደራጅቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ መንግሥት ጥብቅ ጥሪ ያቀርባል።

እንዳሁም እየሸሸ ያለው ጠላት እጁን እንዲሠጥ የማይሰጥ ከሆነ ህብረተሰቡ ተደራጅቶ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ መንግሥት ያስገነዝባል። (ቲክቫህ እና ኢፕድ)

ከዚህ ጋር በተያያዘ ከሞቱት መካከል አንዱ ት ህነጎች የሚተማመኑብትና የሚያመልኩት አብርሃ ተስፋየ ወይም ድንኩል የተባለው ይገኝበታል ይባላል።

ሌላው በቅዳሜ ምሽት ለእሁድ አጥቢያ ከሌሊቱ ፯ ሰዓት ላይ በመቀሌ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት ፮ የትህነግ ሰዎች እንደሞቱ እየተነገረ ነው። ኬኒያዊው የደኀንነት መረጃ ባለቤት ካፒቴን ኮሊንስ ዋንዴሪ እንዳስታወቀው ሰዎቹ ምናልባትም ከፍተኛ ባለሥልጣናት ናቸው። ደብረጽዮን ገብረሚካኤልም በአካባቢው ነበር ተብሎ እንደሚታመን ጨምሮ ገልጾዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, terrorism, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    November 24, 2021 05:41 pm at 5:41 pm

    እኮ በል ጉልጉሎች ረጋ በሉ። ወያኔ እኮ የራሱን ሞት ቀድሞ የሚያሰወራ ቡድን ነው። የደብረጽዪን እኮ ራሳቸው አንድ ጋ እጃቸውና ሌላው ሰውነታቸው ሌላ ጋ ተቀበሩ ተብሎ ባለፈው ሲዘባረቅ ሰምተናል። ግን የሆነው ያ አይደለም። የእጃቸውን ግለብ አውልቀው እንደገና ሲያስፈራሩን በትግራይ ቴሌቪዝን አይተናል። ወያኔ እባብ ነው። አንገቱን ስትቆርጠው ሌላው ሰውነቱ ቆሞ ለመራመድ ይሞክራል። እግራቸው ሲቆረጥ ከፍታ ላይ ሆነው ይፋለማሉ። ወሬው የተረጋገጠ ከሆነ እሰየው ፈጣሪ ከምድረ ገጽ ያጥፋቸው እንላለን። ግን አሜሪካና ሌሎች ሃገሮች በሳተላይት ድጋፍ የሚያደርጉለት የወያኔ ጥርቅም እንዲህ በቀላሉ በአንድ ሥፍራ ተሰብስቦ ለሞት ይበቃል ብሎ መገመት ከባድ ነው። የአሜሪካ ሴራ ጥልቅ ነው። እልፍ ጊዜ በሰላምና ዲሞክራሲ ስም ወደ አፍሪቃ ብሎም ወደ ኢትዮጵያ የሚመላለሱት እነዚህ ሙቶች በዋሽንግተን ዲሲ ጊዜአዊ መንግስት ካቋቋሙ በህዋላ ነው በሰውና በሃገር ላይ የሚቀልድት። ኬኒያታን በአብይ ላይ ጫና እንዲያደርግ የወተወቱትና በሙሉ ክብር በዋይት ሃውስ ተቀብለው ያስተናገድት አሜሪካኖች የመከሩት የኢትዮጵያ ጉዳይ አልቋል። አዲስ አበባ ሊገቡ 30 ኪ. ሜትር ቀራቸው፤ እኛና መሰሎቻችን ሰዎቻችን እያወጣን ነው በማለት ሲያዋክቡት ወይ ፍንክች ባለማለቱ መፍትሄ አጥተው አሜሪካኖች ሌላ ዘፈን ይዘው ብቅ ብለዋል።
    አሁን ደግሞ ለይቶላቸው የኢትዮጵያ የአየር ሰማይ ላይ መብረር ዋስትና የለውም እያሉ እያናፈሱ ይባስ ብለው በአዲስ አበባና በከተሞች ጥቃት በአሸባሪዎች ሊደርስ ይችላል በማለት ወሬውን ይነዙታል። አሸባሪዋ አሜሪካ ናት። መረጃው ካላቸው ይህ ከመሆኑ በፊት ለምን ለመንግስት አካላት አካፍለው ጥበቃና የቀድሞ ማክሸፍ ሥራ እንዲሰራ አያደርጉም? እጃቸው እንዳለበት የሚያስታውቀው ለዚያ ነው።
    አሁን በኢትዪጵያ ላይ አሜሪካ የምታደርገውን ሴራ ለመረዳት ታሪክን መለስ ብሎ በኢራን፤ በኢራቅ፤ በችሌ፤ በፓናማ እና በሌሎችም ሃገራት እንዴት አድርገው ለሃገርና ለወገን የሚያስቡ መሪዎችን በማጥፋት በራሳቸው አሻንጉሊቶች እንደተኳቸው ማየት ይቻላል። የቀድሞ የኢኮኖሚ የስለላ ሰው “The Economic Hit man” በተሰኘው መጽሃፉ ላይ የ 30 ዓመት ድርጊቱን ሲናዘዝ እያነበቡ አለማልቀስ አይቻልም። እጅግ ጭራቃዊ ስራ ነውና የሚሰሩት። ይህም በመሆኑ አሜሪካና ሌሎች የአውሮፓ ሃገሮች ወያኔን የሙጥኝ ቢሉ የሚያስገርም ነገር አይሆንም። ደም አፍሳሽና ሃገር አፍራሽ ህብረት ቢፈጥር እንግዳ ነገር አይደለም። ወያኔ ሸረኛና ተንኮለኛ ነው ይህን ሸሩንና ተንኮሉን የሚወድለት አሜሪካኖችም ተላላኪዎቻቸው መልሰው ስልጣን ላይ ለማውጣት ያልሞከሩት ነገር የለም። ስለዚህ የእነርሱ የሰላምና የዲሞክራሲ ጥሪ የማስመሰያ ካባ ነው። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ በህዋላ አሜሪካ ለሰው ልጆች መብት ቁማ አታውቅም። ለራሷ ጥቅም እንጂ!
    ባጭሩ በዲሲ ያቋቋሙት ቡድን የሽግግር መንግስት መሆኑ ነበር። መሪውም ደም አፍሳሹና የሃገር ሃብትን የሟጠጠው ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ነው። ደርሰንበታል። ይህ ሌባና ደም አፍሳሽ እንኳን ሃገር ቤት ገብቶ መሪ ለመሆን መግባትም አይችልም። የአዲስ አበባ ወጣቶች ደብድበው ይገሉታል። ግፈኛ ሰው ነው። አምባሳደር ሆኖ የሰራቸውን ግፎች በቦታው ሁና የተመለከተች አንዲት ሰው ሥራቸው ሁሉ ስርቆትና ሌብነት ነው በማለት በእንባ በቦታው የተሰራውን አጫውታኛለች። እንግዲህ ይህን ሰው ነው አሜሪካ የሽግግር መንግስቱ መሪ ያደረገችው። ሰው ሰምቶና አይቶ ይፍረድ።
    ግራም ነፈሰ ቀኝ የተባለው ቢባል። የተደረገው ሊደረግ ቢሞከር በጦር ሜዳው ላይ ወያኔ ተቀጥቅጦ ከተረታ ዞረው ተመልሰው እንርዳችሁ ማለታቸው አይቀሬ ነው። ስለሆነም የወታደራዊ የበላይነት ወያኔን ድባቅ መምታት ለአጭር ጊዜም ሆነ ለረጅሙ ትግል ወሳኝ ነው። በጦር ሜዳ ላይ ተሸንፎ ድርድር ላይ የፈለገውን ያገኘ አንድም መንግስት የለም። የህዝባችን አንድነት፤ የመንግስት ጥንካሬ የሚያመጣው ያ ሰላም አሜሪካና አውሮፓ ከሚሰጡን የእጅ አዙር ባርነት ይልቃል። እንበርታ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule