• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በ2 ቀናት በተካሄደ ኦፕሬሽን 12 የትህነግ ከፍተኛ የጦር አመራሮች ተደምስሰዋል

November 24, 2021 01:42 pm by Editor 1 Comment

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ዛሬ ምሽት በሰጠው መግለጫ ተደመሰሱ ካላቸው ውስጥ በፌዴራል መንግሥት በሀገር ክህደት ወንጀል ሲፈለጉ የነበሩ ጄነራሎችና ኮሎኔሎች ይገኙበታል።

በመግለጫው ላይ ተደመሰሱ የተባሉት ጄነራሎችና ኮሎኔሎች ስም አልተገለፀም።

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ በሰጡት መግለጫ ይህን ነው ያሉት፦

“ባለፉት 2 ቀናት በባቲ ግንባር በተደረገ ልዩ ኦፕሬሽን 6 የአርሚና እና የኮር ከፍተኛ አመራሮቹ ተደምስሰዋል። እነዚህ አመራሮች በፌዴራል መንግሥት በሀገር ክህደት ወንጀል ሲፈጉ የነበሩ ከሃዲ ጄነራሎች እና ኮሎኔሎች ናቸው።

በተጨማሪ በከሚሴ ግንባር በተለያዩ ቦታዎች በተደረጉ ልዩ ኦፕሬሽኖች የጠላትን ግንባር ጦር ሲመሩ የነበሩ 6 ከሃዲ ከፍተኛ የጦር አመራሮች ከነጠባቂዎቻቸው ተደምስሰዋል።

በዛሬው ዕለት በባቲ ግንባር በተደረገው ከፍተኛ የማጥቃት እርምጃ ቀደም ሲል ከነበሩት ጥቃቶች ተርፎ ለዳግም ማጥቃት ተዘጋጅቶ የነበረው የጠላት ኃይል የተደመሰሰ ሲሆን እግሬ አውጪኝ ብሎ ወደ ኋላ እየፈረጠጠ ያለውን ጠላት እግር በእግር የወገን ኃይል እየተከተለ እያፀዳው እየገሰገሰ ይገኛል።

በሌሎች ግንባሮችም የወገን ጦር በሰነዘረው ከፍተኛ ማጥቃት ጠላት በከፍተኛ ደረጃ እየተመታ ይገኛል።

በዚሁ አጋጣሚ የወገንን ክንድ መቋቋም አቅቶት በተናጠል እና በቡድን እየሸሸ የሚገኘውን የጠላት ኃይል ዘረፋ እንዳይፈፅም እና ንብረት እንዳያወድም ህብረተሰቡ ተደራጅቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ መንግሥት ጥብቅ ጥሪ ያቀርባል።

እንዳሁም እየሸሸ ያለው ጠላት እጁን እንዲሠጥ የማይሰጥ ከሆነ ህብረተሰቡ ተደራጅቶ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ መንግሥት ያስገነዝባል። (ቲክቫህ እና ኢፕድ)

ከዚህ ጋር በተያያዘ ከሞቱት መካከል አንዱ ት ህነጎች የሚተማመኑብትና የሚያመልኩት አብርሃ ተስፋየ ወይም ድንኩል የተባለው ይገኝበታል ይባላል።

ሌላው በቅዳሜ ምሽት ለእሁድ አጥቢያ ከሌሊቱ ፯ ሰዓት ላይ በመቀሌ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት ፮ የትህነግ ሰዎች እንደሞቱ እየተነገረ ነው። ኬኒያዊው የደኀንነት መረጃ ባለቤት ካፒቴን ኮሊንስ ዋንዴሪ እንዳስታወቀው ሰዎቹ ምናልባትም ከፍተኛ ባለሥልጣናት ናቸው። ደብረጽዮን ገብረሚካኤልም በአካባቢው ነበር ተብሎ እንደሚታመን ጨምሮ ገልጾዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, terrorism, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    November 24, 2021 05:41 pm at 5:41 pm

    እኮ በል ጉልጉሎች ረጋ በሉ። ወያኔ እኮ የራሱን ሞት ቀድሞ የሚያሰወራ ቡድን ነው። የደብረጽዪን እኮ ራሳቸው አንድ ጋ እጃቸውና ሌላው ሰውነታቸው ሌላ ጋ ተቀበሩ ተብሎ ባለፈው ሲዘባረቅ ሰምተናል። ግን የሆነው ያ አይደለም። የእጃቸውን ግለብ አውልቀው እንደገና ሲያስፈራሩን በትግራይ ቴሌቪዝን አይተናል። ወያኔ እባብ ነው። አንገቱን ስትቆርጠው ሌላው ሰውነቱ ቆሞ ለመራመድ ይሞክራል። እግራቸው ሲቆረጥ ከፍታ ላይ ሆነው ይፋለማሉ። ወሬው የተረጋገጠ ከሆነ እሰየው ፈጣሪ ከምድረ ገጽ ያጥፋቸው እንላለን። ግን አሜሪካና ሌሎች ሃገሮች በሳተላይት ድጋፍ የሚያደርጉለት የወያኔ ጥርቅም እንዲህ በቀላሉ በአንድ ሥፍራ ተሰብስቦ ለሞት ይበቃል ብሎ መገመት ከባድ ነው። የአሜሪካ ሴራ ጥልቅ ነው። እልፍ ጊዜ በሰላምና ዲሞክራሲ ስም ወደ አፍሪቃ ብሎም ወደ ኢትዮጵያ የሚመላለሱት እነዚህ ሙቶች በዋሽንግተን ዲሲ ጊዜአዊ መንግስት ካቋቋሙ በህዋላ ነው በሰውና በሃገር ላይ የሚቀልድት። ኬኒያታን በአብይ ላይ ጫና እንዲያደርግ የወተወቱትና በሙሉ ክብር በዋይት ሃውስ ተቀብለው ያስተናገድት አሜሪካኖች የመከሩት የኢትዮጵያ ጉዳይ አልቋል። አዲስ አበባ ሊገቡ 30 ኪ. ሜትር ቀራቸው፤ እኛና መሰሎቻችን ሰዎቻችን እያወጣን ነው በማለት ሲያዋክቡት ወይ ፍንክች ባለማለቱ መፍትሄ አጥተው አሜሪካኖች ሌላ ዘፈን ይዘው ብቅ ብለዋል።
    አሁን ደግሞ ለይቶላቸው የኢትዮጵያ የአየር ሰማይ ላይ መብረር ዋስትና የለውም እያሉ እያናፈሱ ይባስ ብለው በአዲስ አበባና በከተሞች ጥቃት በአሸባሪዎች ሊደርስ ይችላል በማለት ወሬውን ይነዙታል። አሸባሪዋ አሜሪካ ናት። መረጃው ካላቸው ይህ ከመሆኑ በፊት ለምን ለመንግስት አካላት አካፍለው ጥበቃና የቀድሞ ማክሸፍ ሥራ እንዲሰራ አያደርጉም? እጃቸው እንዳለበት የሚያስታውቀው ለዚያ ነው።
    አሁን በኢትዪጵያ ላይ አሜሪካ የምታደርገውን ሴራ ለመረዳት ታሪክን መለስ ብሎ በኢራን፤ በኢራቅ፤ በችሌ፤ በፓናማ እና በሌሎችም ሃገራት እንዴት አድርገው ለሃገርና ለወገን የሚያስቡ መሪዎችን በማጥፋት በራሳቸው አሻንጉሊቶች እንደተኳቸው ማየት ይቻላል። የቀድሞ የኢኮኖሚ የስለላ ሰው “The Economic Hit man” በተሰኘው መጽሃፉ ላይ የ 30 ዓመት ድርጊቱን ሲናዘዝ እያነበቡ አለማልቀስ አይቻልም። እጅግ ጭራቃዊ ስራ ነውና የሚሰሩት። ይህም በመሆኑ አሜሪካና ሌሎች የአውሮፓ ሃገሮች ወያኔን የሙጥኝ ቢሉ የሚያስገርም ነገር አይሆንም። ደም አፍሳሽና ሃገር አፍራሽ ህብረት ቢፈጥር እንግዳ ነገር አይደለም። ወያኔ ሸረኛና ተንኮለኛ ነው ይህን ሸሩንና ተንኮሉን የሚወድለት አሜሪካኖችም ተላላኪዎቻቸው መልሰው ስልጣን ላይ ለማውጣት ያልሞከሩት ነገር የለም። ስለዚህ የእነርሱ የሰላምና የዲሞክራሲ ጥሪ የማስመሰያ ካባ ነው። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ በህዋላ አሜሪካ ለሰው ልጆች መብት ቁማ አታውቅም። ለራሷ ጥቅም እንጂ!
    ባጭሩ በዲሲ ያቋቋሙት ቡድን የሽግግር መንግስት መሆኑ ነበር። መሪውም ደም አፍሳሹና የሃገር ሃብትን የሟጠጠው ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ነው። ደርሰንበታል። ይህ ሌባና ደም አፍሳሽ እንኳን ሃገር ቤት ገብቶ መሪ ለመሆን መግባትም አይችልም። የአዲስ አበባ ወጣቶች ደብድበው ይገሉታል። ግፈኛ ሰው ነው። አምባሳደር ሆኖ የሰራቸውን ግፎች በቦታው ሁና የተመለከተች አንዲት ሰው ሥራቸው ሁሉ ስርቆትና ሌብነት ነው በማለት በእንባ በቦታው የተሰራውን አጫውታኛለች። እንግዲህ ይህን ሰው ነው አሜሪካ የሽግግር መንግስቱ መሪ ያደረገችው። ሰው ሰምቶና አይቶ ይፍረድ።
    ግራም ነፈሰ ቀኝ የተባለው ቢባል። የተደረገው ሊደረግ ቢሞከር በጦር ሜዳው ላይ ወያኔ ተቀጥቅጦ ከተረታ ዞረው ተመልሰው እንርዳችሁ ማለታቸው አይቀሬ ነው። ስለሆነም የወታደራዊ የበላይነት ወያኔን ድባቅ መምታት ለአጭር ጊዜም ሆነ ለረጅሙ ትግል ወሳኝ ነው። በጦር ሜዳ ላይ ተሸንፎ ድርድር ላይ የፈለገውን ያገኘ አንድም መንግስት የለም። የህዝባችን አንድነት፤ የመንግስት ጥንካሬ የሚያመጣው ያ ሰላም አሜሪካና አውሮፓ ከሚሰጡን የእጅ አዙር ባርነት ይልቃል። እንበርታ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule